• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በጎደሬ ወረዳ የዘር ግጭት ተነሳ፤ መከላከያ ገብቷል

September 15, 2014 02:11 am by Editor Leave a Comment

በጋምቤላ ዞን በጎደሬ ወረዳ ነጋዴዎችና ሰፋሪዎች ከአካባቢው ተወላጅ የመዠንገር ጎሳ አባላት ጋር ተጋጩ። በግጭቱ ከ17 ሰባት በላይ ሰዎች ተገድለዋል። በግጭቱ የመዠንገር ዞን አስተዳዳሪና የጎደሬ ወረዳ ዳኛ ከነቤተሰቦቻቸው የግጭቱ ሰለባ መሆናቸው ታውቋል። ግጭቱን ለማብረድ የመከላከያ ሠራዊት የገባ ሲሆን፣ የጋምቤላ ክልል ልዩ ኃይል ግጭቱን ለማብረድ በጉዞ ላይ እንዳለ በተሰጠ መመሪያ እንዲመለስ ተደርጓል።

ስማቸው እንዳይገለጽ የፈሩ የአካባቢው ነዋሪዎች ለጎልጉል እንደገለጹት በወረዳው በመሬት ባለቤትነትና በመሬት ይገባኛል ጥያቄ ከመሀል አገር በመጡ ሰፋሪዎችና ነጋዴዎች መካከል አለመግባባት ከተፈጠረ ዓመታትን አስቆጥሯል። የፌዴራል አገዛዙም ሆነ የክልሉ አመራሮች ችግሩ ሳይሰፋ ሰላማዊ መፍትሄ ባለማፈላለጋቸው ችግሩ ሊካረር ችሏል። ኢህአዴግ የሚከተለው በዘር ከፋፍሎ የመግዛት ፖሊሲ ለችግሩ መባባስ በዋንኛነት ተጠቃሽ ነው።

ባለፈው ሃሙስ በአንድ የመሃል አገር ሰፋሪና የአካባቢው ተወላጅ በሆነ አርሶ አደር መካከል ድንገተኛ ጸብ ተነስቶ ነበር። በጸቡ የመዠንግር ጎሳ አባል የሆነው አርሶ አደር ህይወት አለፈ። በጎሳ አባላቸው መገደል የተበሳጩ ዘመዶች ውሎ ሳያድር በወሰዱት የበቀል ርምጃ አንድ ሰፋሪ የመሃል አገር ሰው ህይወት አለፈ። እንደ ዜናው አቀባዮች ከሆነ በዚሁ በመሬት ጉዳይ በተከሰተው የሁለት ግለሰቦች ህልፈት ተከትሎ ችግሩ ተካረረ።

በተመሳሳይ ቀን ማምሻው ላይ ከመሃል አገር የመጡት ሰፋሪዎች የዞኑን አስተዳዳሪ፣ ባለቤታቸውንና ሁለት ልጆቻቸውን መኖሪያ ቤታቸው በመሄድ በስለት ገደሉ። በተመሳሳይ አንድ የጎደሬ ወረዳ አስተዳዳሪ ከባለቤታቸውና ከልጃቸው ጋር ተገደሉ። በደቦ የተጀመረው የስለት ግድያ እየሰፋ የሟቾችን ቁጥር 17 እንዳደረሰውና በስለት የቆሰሉ ሰዎች ቁጥር ከ40 በላይ መሆኑን በስልክ የገለጹት ያካባቢው ነዋሪዎች “አሁን ፍርሃቻ አለ። ቤት ለቤት የተካሄደው ግድያ የት ጋር ያቆማል? የመከላከያ ሠራዊት ሚናም ግልጽ አይደለም” ብለዋል።

goderieየጋምቤላ ዞን ልዩ ኃይል ግጭቱን ለማብረድ እየገሰገሰ ባለበት ወቅት ከአዲስ አበባ በተሰጠ ትዕዛዝ ወደ ጋምቤላ እንዲመለሱ መደረጉን ያመለከቱት እኚሁ ክፍሎች፣ “የጋምቤላ ልዩ ኃይል ግጭቱ ያለበት ቦታ ሲደርስ በራሱ ክልል ሰዎች ላይ መጤዎች ጉዳት ማድረሳቸውን ሲመለከት ከመከላከያ ሠራዊት ጋር ግጭት ሊፈጠር ይችላል” በሚል ስጋት የልዩ ኃይሉ ወደ ጋምቤላ የተመለሰበትን ምክንያት ነዋሪዎቹ ተናግረዋል።

በገጀራና በተለያዩ የስለት መሳሪያዎች የተካሄደው ግድያ የሚዘገንን እንደነበር፣ ቀን ጠብቆ ተጎጂው አካል ከመበቀል ወደኋላ እንደማይል፣ በስለታማ ቁሶች የሚከናወነው ግድያ ሊሰፋ እንደሚችል ስጋታቸውን አክለው የገለጹት ነዋሪዎች ኢህአዴግ ሰላማዊ መፍትሄ ሊፈልግ እንደሚገባ ከወዲሁ ጠይቀዋል። በጋምቤላ ክልል በሳንቲም የሚቸበቸበውና የተፈጥሮ ደን እያወደመ ያለው ኢንቨስትመንት የተወሳሰበ ችግር ማስከተሉ አይዘነጋም። በዚሁ ሳቢያ በርካታ ንጹሃን ህይወታቸው ማለፉ የሚታወስ ነው። ክልሉን ከላይ ሆነው የሚመሩት አቶ አዲሱ ለገሰ መሆናቸው ይታወቃል።

የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶ ጉዳዩን አስመልክቶ ከኦስሎ ለጎልጉል አስተያየት ሲሰጡ “ባሰቃቂ ሁኔታ ህይወታቸው ላለፈ ወገኖች የሰላም ረፍት ይሁን፣ ፍትህ በልጅ ልጆቻችሁ ትፈርድላችኋለች፣ ፍትህ ሩቅ አይሆንም” በማለት ነበር የጀመሩት። አያይዘውም “ምንም እንኳ ባል ፖለቲከኛ ቢሆን ሚስትና ልጆች ምን አደረጉ? ህጻናትና ሴቶች በማያውቁት ጉዳይ ለምን ሰላባ ይሆናሉ? ቀደም ሲል አብረው የሚኖሩ ሰዎች ዛሬ ለምን ይጋጫሉ?” ሲሉ ችግሩ ሁሉ የሚመነጨው ኢህአዴግ ከሚከተለው ጎሳን መሰረት ያደረገ የከፋፍለህ ግዛው መርህ አንደሆነ ገልጸዋል።

“መመሪያ ሰጪው፣ ገዳዩ፣ አስገዳዩ፣ ቆሞ ተመልካቹ፣ … ሁሉም ከፍትህ አደባባይ አያመልጡም” ያሉት አቶ ኦባንግ “ዘርን እየለየ የሚከናወን ግድያ “ጄኖሳይድ” ነው። አኙዋኮች ላይ በጅምላ ከተከናወነው ጭፍጨፋ ለይተን አናየውም” ሲሉ በጉዳዩ ክፉኛ ማዘናቸውን አመልክተዋል።

የሚመሩት ድርጅት ጉዳዩን በቅርብ እየተከታተለና አስፈላጊ ነው የሚለውን ስራ እያከናወነ እንደሆነ ያመለከቱት አቶ ኦባንግ፣ ሁሉም ያካባቢው ነዋሪዎች ሰፋሪም ሆነ የቀዬው ተወላጆች እንደቀድሞ በፍቅር ሊኖሩ የሚያስችላቸውን እሴቶች እንዲጠብቁ መክረዋል። በተለያዩ ያገሪቱ ክፍሎች ጎሳን እየለየ የሚካሄደው ግድያና ማፈናቀል እየሰፋ እንጂ እየቀነሰ ባለመሆኑ ስጋቱ ከፍተኛ እንደሆነም ገልጸዋል። በዚህ ከቀጠለና ህወሃት የቀበራቸው የጎሳ ፈንጂዎች ሲነዱ እሳቱ ሁሉንም ስለማይምር ሁሉም ዜጎች ጥንቃቄ እንዲወስዱ አሳስበዋል። ኢህአዴግም ችግሮችን ከማስፋት ይልቅ የሚቃለሉበትን አግባብ ለራሱ ሲል ሊከተል እንደሚገባ ጠቁመዋል። ጎልጉል የዞኑንና የወረዳውን አስተዳደር ለማነጋገር ያደረገው ጥረት አልተሳካም። ይሁን እንጂ የክልሉ ፖሊስ ዝርዝር መግለጫ ባይሰጥም የተባለው ቀውስ ስለመፈጠሩ አልካደም።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule