• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ባቡር

February 4, 2015 08:39 am by Editor 1 Comment

ትናንትና (እሁድ) የከተማ መለስተኛ የባቡር መጓጓዣ አገልግሎት ተጠናቆ ለአገልግሎት ተመረቀ፡፡ አሄሄሄ! ውስጡን ለቄስ! አሉ፡፡ ይሄ የባቡር ሥራ ብቻ ሳይሆን በወያኔ እጅ የሚሠራ ሥራ ሁሉ ከፍተኛ ብቻ ሳይሆን እጅግ አደገኛና አሳሳቢ የጥራት ችግር እንዳለባቸው በግልጽ የሚታይ ጉዳይ ነው፡፡ ቢሊዮኖች ዶላር (ብልፎች ዶላር) ልብ በሉ ቢሊዮን (ብልፍ) ነው ያልኩት ሚሊየን (አእላፋት) አይደለም ፈሶበት ቴሌ ላይ የተሠራውን ሥራ እና ውጤቱን ዐይተናል፣ መብራት ኃይል ላይም አሁንም እንዲሁ በቢሊዮኖች (ብልፎች) ዶላር ወቶበት ከህንድ እንዲገባ ያደረጉት ትራንስፎርመር (ማስተላለፊያ) በሙስና ምክንያት ከጥራት ደረጃ በታች እንዲሠራ የተደረገ በመሆኑ በተገጠመ ቁጥር እየተቃጠለ ምን ዓይነት ችግር ላይ እንዳለን ለቀባሪ ማርዳት ነው፡፡ በዚህ በባቡር ሥራው ላይም የጅብነታቸው ጅብነት የሸክላ ሀዲድ ዘርግተው ገደል እየከተቱ ሊጨርሱን ከማለቁ በፊት የበሉትን ገንዘብ ሲከፋፈሉ ቅር ያለው ነበር መሰለኝ አንዱ የዘረጉት ሀዲድ የሸክላ ሀዲድ መሆኑን በማጋለጡ እንደገና እያነሡ አሁን በትክክለኛው የብረት ሀዲድ ቀየርን፤ ይሄንን ያደረጉትንም አባረርን አሉ፡፡ ሲሉ ሰማን እንጅ በትክክልም የሸክላው ሀዲድ ተነሥቶ በትክክለኛው የብረት ሀዲድ ስለመቀየሩ ያረጋገጥነው ነገር የለም፡፡ መቸስ ሰው አስቀርበው?

እነዚህ ሥራዎች የሚወጣባቸው በብድርና በእርዳታ የተገኘ ገንዘብ ዓለማቀፋዊ ደረጃውን በጠበቀ መልኩ ሊያሠራ የሚያስችል ቢሆንም ከሙሰኞቻችን ባለሥልጣናት ጅብነት የተነሣ 10 በመቶውን እንኳን እንዲሠራበት ስለማይፈቅዱ እንዲህ እንዲህ ዓይነቶች ከባባድ የጥራት ችግሮች ይከሰታሉ፡፡ ባጠቃላይ በዚህ አገዛዝ የሚሠራ ሥራ ሁሉ ወይ ገንዘቡ አልዳነ ባለ ዕዳ ሆነን ወይ ብድሩ መጥቶም ደረጃውን የጠበቀ ሥራ ተሠርቶበት ተጠቃሚ የማንሆንበት ሁኔታ ስለ ሆነ ያለው ነገር በዚህ የገማ አገዛዝ እጅ ምንም ነገር ባይሠራ ሽ ጊዜ ተመራጭ ነው፡፡ እስኪ አስቡት ለእነኝህ የማይረቡ ብላሽ ቆልኮሌ ሥራዎች ሀገሪቱ በትውልደ ትውልድ ተከፍሎ የማያልቅ ዕዳ ውስጥ እየሰጠመች እኮ ነው!

እንግዲህ ያው በሸክላ ሀዲድ እየተጓዝን ለማለቅ እንኳን አደረሰን ልበል ይሆን? ባለሥልጣኖቻችንም በዚህ ስንት ጉድ በታየበት የባቡር ሥራ ምረቃ ላይ “ቢያንስ በአዲስነቱ ምንም አይል” ብለው ነው መሰለኝ በድፍረት ሲጓዙበት ሳይ በጣም ነበር የገረሙኝ፡፡

ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!!!

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    February 7, 2015 07:01 am at 7:01 am

    “ስኳር ቀምሶ የማያውቅ ገበሬ ስኳር እንዳመረውና እንዳማረረው የሱኳር ፋብሪካ ቁጥር ሲቆጥር ሞተ”አባይ ፀሐይ የስኳር ሚኒስትሩ የሃይማኖት ጉዳይ ላይ ተወጥረው ነበር…
    “ጤፍ ቀምሶ የማያውቀው ብሔር ብሔረሰብ ከመጠን በላይ መብላት በመጀመሩ ዕድገቱን አቀጨጨው ሲያንገሸግሸው በከተማ ጤፍ ሲወደድ በጎረቤት ሀገራት ጤፍ እረክሶ ሰው የብረት እጥረቱን አሟላበት…”
    ” የኢትዮጵያ መብራትና ኅይል ባለሥልጣን….” በሻማና ጧፍ ኮርፖሬሽን’ ከተቀየረ ጀምሮ የአካባቢው ሥልጣን አስተባቂ ወዳጅ ሀገሮች መብራት በቀላል ዋጋ ሲሸጥላቸው ውሃ በነፃ ሲቸራቸው የኢትዮጵያ ህዝብ ከዳቦ ሰልፍ ወደ ውሃ ጀርካን ሠልፍ ተሸጋገረ…
    ” መካከለኛ ገቢ ካላቸው ሀገሮች ጎን ለመሠለፍ የዩኒቨርስቲ እንጂ ብቁ የተማረ ኅይል የማይፈልቅበት ጥሩ አጫፈሪ ካድሬ ሆድ-አደር ፣ አደር-ባይ መፈልፈያ ወታቦ ሆኖ ያልተማረ እየመራው የተማረ ያለደሞዝ እየተባረረ ዘልቋል…
    “ይህ ሙስና መር ኢኮኖሚ…በብድርና በልመና የሞላው ካዝና በቀለበትና በአሳላጭ በፈጣን መንገድ ለመክበር የሚደረገው ፉክክር…በልቶ እያባላ የሚያኖራቸው መካከለኛና ከፍተኛ ትቅማጥቅመኞች አነስተኛና ትቃቅኖችን በባርኔጣ ከልለው..በካኒተራ አስውበው..በአንገት ልብስ አፍነው…ያስጨፍሯቸዋል..ዕድገትና ውድቀትን እንዴት ያውቁታል?
    “ትምህርት፣ ጤና ፣ፍትህ፣ የኑሮ መሻሻል፣የመናገር መፃፍ ነፃነት ገና በልመና ሲሆን የምረጡኝ አስገድዶ ማሳመን የተለመደው ተግባርና ‘አውራው ፓርቲ’ አለኝ በሚለው የአምስት ዓመቱ የትዳር(ኮንትራት) ባለፈው ቅንጅትን መንታ ሲያደርግ ዘንድሮ ከምርጫው ጫጉላ ላይ …ሜንጫ ቦንድን ዋስ እድርጎ… መኢአድን እና አንድነት ፓርቲን ጥንድ የማድረጉ ጉዳይ “አውራው ፓርቲ ምንኛ የተዋጣለት አጥቂ ቢሆን ነው!?
    ** እንግዲህ እናንት በሻቢያህወአት የተፈጠራችሁ በኢህአዴግ ጥላ ሥር ብቻ ለመኖር በመፈቃቀድና በመፈቃቀር ቃል ገብታችኋል! ለእኛ በእኛ ብቻ የምትኖሩ መሆናችሁን አምናችኋል! ትናንት ያልነበራችሁ እኛ ስንፈጥራችሁ ማንነታችሁን አታውቁም ቀድሞ በባዶ እግራችሁ ትሄዱ ነበር አሁን ባቡር አይተው የማያውቁ መሳፈር ጀምረዋል…በጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የህወአት ጉዳይ አስፈፃሚ አቶ ኀይለመለስ ደስአለኝ….”
    http://www.youtube.com/watch?v=aU0vyc6X57A

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule