• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ባቡር

February 4, 2015 08:39 am by Editor 1 Comment

ትናንትና (እሁድ) የከተማ መለስተኛ የባቡር መጓጓዣ አገልግሎት ተጠናቆ ለአገልግሎት ተመረቀ፡፡ አሄሄሄ! ውስጡን ለቄስ! አሉ፡፡ ይሄ የባቡር ሥራ ብቻ ሳይሆን በወያኔ እጅ የሚሠራ ሥራ ሁሉ ከፍተኛ ብቻ ሳይሆን እጅግ አደገኛና አሳሳቢ የጥራት ችግር እንዳለባቸው በግልጽ የሚታይ ጉዳይ ነው፡፡ ቢሊዮኖች ዶላር (ብልፎች ዶላር) ልብ በሉ ቢሊዮን (ብልፍ) ነው ያልኩት ሚሊየን (አእላፋት) አይደለም ፈሶበት ቴሌ ላይ የተሠራውን ሥራ እና ውጤቱን ዐይተናል፣ መብራት ኃይል ላይም አሁንም እንዲሁ በቢሊዮኖች (ብልፎች) ዶላር ወቶበት ከህንድ እንዲገባ ያደረጉት ትራንስፎርመር (ማስተላለፊያ) በሙስና ምክንያት ከጥራት ደረጃ በታች እንዲሠራ የተደረገ በመሆኑ በተገጠመ ቁጥር እየተቃጠለ ምን ዓይነት ችግር ላይ እንዳለን ለቀባሪ ማርዳት ነው፡፡ በዚህ በባቡር ሥራው ላይም የጅብነታቸው ጅብነት የሸክላ ሀዲድ ዘርግተው ገደል እየከተቱ ሊጨርሱን ከማለቁ በፊት የበሉትን ገንዘብ ሲከፋፈሉ ቅር ያለው ነበር መሰለኝ አንዱ የዘረጉት ሀዲድ የሸክላ ሀዲድ መሆኑን በማጋለጡ እንደገና እያነሡ አሁን በትክክለኛው የብረት ሀዲድ ቀየርን፤ ይሄንን ያደረጉትንም አባረርን አሉ፡፡ ሲሉ ሰማን እንጅ በትክክልም የሸክላው ሀዲድ ተነሥቶ በትክክለኛው የብረት ሀዲድ ስለመቀየሩ ያረጋገጥነው ነገር የለም፡፡ መቸስ ሰው አስቀርበው?

እነዚህ ሥራዎች የሚወጣባቸው በብድርና በእርዳታ የተገኘ ገንዘብ ዓለማቀፋዊ ደረጃውን በጠበቀ መልኩ ሊያሠራ የሚያስችል ቢሆንም ከሙሰኞቻችን ባለሥልጣናት ጅብነት የተነሣ 10 በመቶውን እንኳን እንዲሠራበት ስለማይፈቅዱ እንዲህ እንዲህ ዓይነቶች ከባባድ የጥራት ችግሮች ይከሰታሉ፡፡ ባጠቃላይ በዚህ አገዛዝ የሚሠራ ሥራ ሁሉ ወይ ገንዘቡ አልዳነ ባለ ዕዳ ሆነን ወይ ብድሩ መጥቶም ደረጃውን የጠበቀ ሥራ ተሠርቶበት ተጠቃሚ የማንሆንበት ሁኔታ ስለ ሆነ ያለው ነገር በዚህ የገማ አገዛዝ እጅ ምንም ነገር ባይሠራ ሽ ጊዜ ተመራጭ ነው፡፡ እስኪ አስቡት ለእነኝህ የማይረቡ ብላሽ ቆልኮሌ ሥራዎች ሀገሪቱ በትውልደ ትውልድ ተከፍሎ የማያልቅ ዕዳ ውስጥ እየሰጠመች እኮ ነው!

እንግዲህ ያው በሸክላ ሀዲድ እየተጓዝን ለማለቅ እንኳን አደረሰን ልበል ይሆን? ባለሥልጣኖቻችንም በዚህ ስንት ጉድ በታየበት የባቡር ሥራ ምረቃ ላይ “ቢያንስ በአዲስነቱ ምንም አይል” ብለው ነው መሰለኝ በድፍረት ሲጓዙበት ሳይ በጣም ነበር የገረሙኝ፡፡

ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!!!

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    February 7, 2015 07:01 am at 7:01 am

    “ስኳር ቀምሶ የማያውቅ ገበሬ ስኳር እንዳመረውና እንዳማረረው የሱኳር ፋብሪካ ቁጥር ሲቆጥር ሞተ”አባይ ፀሐይ የስኳር ሚኒስትሩ የሃይማኖት ጉዳይ ላይ ተወጥረው ነበር…
    “ጤፍ ቀምሶ የማያውቀው ብሔር ብሔረሰብ ከመጠን በላይ መብላት በመጀመሩ ዕድገቱን አቀጨጨው ሲያንገሸግሸው በከተማ ጤፍ ሲወደድ በጎረቤት ሀገራት ጤፍ እረክሶ ሰው የብረት እጥረቱን አሟላበት…”
    ” የኢትዮጵያ መብራትና ኅይል ባለሥልጣን….” በሻማና ጧፍ ኮርፖሬሽን’ ከተቀየረ ጀምሮ የአካባቢው ሥልጣን አስተባቂ ወዳጅ ሀገሮች መብራት በቀላል ዋጋ ሲሸጥላቸው ውሃ በነፃ ሲቸራቸው የኢትዮጵያ ህዝብ ከዳቦ ሰልፍ ወደ ውሃ ጀርካን ሠልፍ ተሸጋገረ…
    ” መካከለኛ ገቢ ካላቸው ሀገሮች ጎን ለመሠለፍ የዩኒቨርስቲ እንጂ ብቁ የተማረ ኅይል የማይፈልቅበት ጥሩ አጫፈሪ ካድሬ ሆድ-አደር ፣ አደር-ባይ መፈልፈያ ወታቦ ሆኖ ያልተማረ እየመራው የተማረ ያለደሞዝ እየተባረረ ዘልቋል…
    “ይህ ሙስና መር ኢኮኖሚ…በብድርና በልመና የሞላው ካዝና በቀለበትና በአሳላጭ በፈጣን መንገድ ለመክበር የሚደረገው ፉክክር…በልቶ እያባላ የሚያኖራቸው መካከለኛና ከፍተኛ ትቅማጥቅመኞች አነስተኛና ትቃቅኖችን በባርኔጣ ከልለው..በካኒተራ አስውበው..በአንገት ልብስ አፍነው…ያስጨፍሯቸዋል..ዕድገትና ውድቀትን እንዴት ያውቁታል?
    “ትምህርት፣ ጤና ፣ፍትህ፣ የኑሮ መሻሻል፣የመናገር መፃፍ ነፃነት ገና በልመና ሲሆን የምረጡኝ አስገድዶ ማሳመን የተለመደው ተግባርና ‘አውራው ፓርቲ’ አለኝ በሚለው የአምስት ዓመቱ የትዳር(ኮንትራት) ባለፈው ቅንጅትን መንታ ሲያደርግ ዘንድሮ ከምርጫው ጫጉላ ላይ …ሜንጫ ቦንድን ዋስ እድርጎ… መኢአድን እና አንድነት ፓርቲን ጥንድ የማድረጉ ጉዳይ “አውራው ፓርቲ ምንኛ የተዋጣለት አጥቂ ቢሆን ነው!?
    ** እንግዲህ እናንት በሻቢያህወአት የተፈጠራችሁ በኢህአዴግ ጥላ ሥር ብቻ ለመኖር በመፈቃቀድና በመፈቃቀር ቃል ገብታችኋል! ለእኛ በእኛ ብቻ የምትኖሩ መሆናችሁን አምናችኋል! ትናንት ያልነበራችሁ እኛ ስንፈጥራችሁ ማንነታችሁን አታውቁም ቀድሞ በባዶ እግራችሁ ትሄዱ ነበር አሁን ባቡር አይተው የማያውቁ መሳፈር ጀምረዋል…በጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የህወአት ጉዳይ አስፈፃሚ አቶ ኀይለመለስ ደስአለኝ….”
    http://www.youtube.com/watch?v=aU0vyc6X57A

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule