• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ባቡር

February 4, 2015 08:39 am by Editor 1 Comment

ትናንትና (እሁድ) የከተማ መለስተኛ የባቡር መጓጓዣ አገልግሎት ተጠናቆ ለአገልግሎት ተመረቀ፡፡ አሄሄሄ! ውስጡን ለቄስ! አሉ፡፡ ይሄ የባቡር ሥራ ብቻ ሳይሆን በወያኔ እጅ የሚሠራ ሥራ ሁሉ ከፍተኛ ብቻ ሳይሆን እጅግ አደገኛና አሳሳቢ የጥራት ችግር እንዳለባቸው በግልጽ የሚታይ ጉዳይ ነው፡፡ ቢሊዮኖች ዶላር (ብልፎች ዶላር) ልብ በሉ ቢሊዮን (ብልፍ) ነው ያልኩት ሚሊየን (አእላፋት) አይደለም ፈሶበት ቴሌ ላይ የተሠራውን ሥራ እና ውጤቱን ዐይተናል፣ መብራት ኃይል ላይም አሁንም እንዲሁ በቢሊዮኖች (ብልፎች) ዶላር ወቶበት ከህንድ እንዲገባ ያደረጉት ትራንስፎርመር (ማስተላለፊያ) በሙስና ምክንያት ከጥራት ደረጃ በታች እንዲሠራ የተደረገ በመሆኑ በተገጠመ ቁጥር እየተቃጠለ ምን ዓይነት ችግር ላይ እንዳለን ለቀባሪ ማርዳት ነው፡፡ በዚህ በባቡር ሥራው ላይም የጅብነታቸው ጅብነት የሸክላ ሀዲድ ዘርግተው ገደል እየከተቱ ሊጨርሱን ከማለቁ በፊት የበሉትን ገንዘብ ሲከፋፈሉ ቅር ያለው ነበር መሰለኝ አንዱ የዘረጉት ሀዲድ የሸክላ ሀዲድ መሆኑን በማጋለጡ እንደገና እያነሡ አሁን በትክክለኛው የብረት ሀዲድ ቀየርን፤ ይሄንን ያደረጉትንም አባረርን አሉ፡፡ ሲሉ ሰማን እንጅ በትክክልም የሸክላው ሀዲድ ተነሥቶ በትክክለኛው የብረት ሀዲድ ስለመቀየሩ ያረጋገጥነው ነገር የለም፡፡ መቸስ ሰው አስቀርበው?

እነዚህ ሥራዎች የሚወጣባቸው በብድርና በእርዳታ የተገኘ ገንዘብ ዓለማቀፋዊ ደረጃውን በጠበቀ መልኩ ሊያሠራ የሚያስችል ቢሆንም ከሙሰኞቻችን ባለሥልጣናት ጅብነት የተነሣ 10 በመቶውን እንኳን እንዲሠራበት ስለማይፈቅዱ እንዲህ እንዲህ ዓይነቶች ከባባድ የጥራት ችግሮች ይከሰታሉ፡፡ ባጠቃላይ በዚህ አገዛዝ የሚሠራ ሥራ ሁሉ ወይ ገንዘቡ አልዳነ ባለ ዕዳ ሆነን ወይ ብድሩ መጥቶም ደረጃውን የጠበቀ ሥራ ተሠርቶበት ተጠቃሚ የማንሆንበት ሁኔታ ስለ ሆነ ያለው ነገር በዚህ የገማ አገዛዝ እጅ ምንም ነገር ባይሠራ ሽ ጊዜ ተመራጭ ነው፡፡ እስኪ አስቡት ለእነኝህ የማይረቡ ብላሽ ቆልኮሌ ሥራዎች ሀገሪቱ በትውልደ ትውልድ ተከፍሎ የማያልቅ ዕዳ ውስጥ እየሰጠመች እኮ ነው!

እንግዲህ ያው በሸክላ ሀዲድ እየተጓዝን ለማለቅ እንኳን አደረሰን ልበል ይሆን? ባለሥልጣኖቻችንም በዚህ ስንት ጉድ በታየበት የባቡር ሥራ ምረቃ ላይ “ቢያንስ በአዲስነቱ ምንም አይል” ብለው ነው መሰለኝ በድፍረት ሲጓዙበት ሳይ በጣም ነበር የገረሙኝ፡፡

ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!!!

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    February 7, 2015 07:01 am at 7:01 am

    “ስኳር ቀምሶ የማያውቅ ገበሬ ስኳር እንዳመረውና እንዳማረረው የሱኳር ፋብሪካ ቁጥር ሲቆጥር ሞተ”አባይ ፀሐይ የስኳር ሚኒስትሩ የሃይማኖት ጉዳይ ላይ ተወጥረው ነበር…
    “ጤፍ ቀምሶ የማያውቀው ብሔር ብሔረሰብ ከመጠን በላይ መብላት በመጀመሩ ዕድገቱን አቀጨጨው ሲያንገሸግሸው በከተማ ጤፍ ሲወደድ በጎረቤት ሀገራት ጤፍ እረክሶ ሰው የብረት እጥረቱን አሟላበት…”
    ” የኢትዮጵያ መብራትና ኅይል ባለሥልጣን….” በሻማና ጧፍ ኮርፖሬሽን’ ከተቀየረ ጀምሮ የአካባቢው ሥልጣን አስተባቂ ወዳጅ ሀገሮች መብራት በቀላል ዋጋ ሲሸጥላቸው ውሃ በነፃ ሲቸራቸው የኢትዮጵያ ህዝብ ከዳቦ ሰልፍ ወደ ውሃ ጀርካን ሠልፍ ተሸጋገረ…
    ” መካከለኛ ገቢ ካላቸው ሀገሮች ጎን ለመሠለፍ የዩኒቨርስቲ እንጂ ብቁ የተማረ ኅይል የማይፈልቅበት ጥሩ አጫፈሪ ካድሬ ሆድ-አደር ፣ አደር-ባይ መፈልፈያ ወታቦ ሆኖ ያልተማረ እየመራው የተማረ ያለደሞዝ እየተባረረ ዘልቋል…
    “ይህ ሙስና መር ኢኮኖሚ…በብድርና በልመና የሞላው ካዝና በቀለበትና በአሳላጭ በፈጣን መንገድ ለመክበር የሚደረገው ፉክክር…በልቶ እያባላ የሚያኖራቸው መካከለኛና ከፍተኛ ትቅማጥቅመኞች አነስተኛና ትቃቅኖችን በባርኔጣ ከልለው..በካኒተራ አስውበው..በአንገት ልብስ አፍነው…ያስጨፍሯቸዋል..ዕድገትና ውድቀትን እንዴት ያውቁታል?
    “ትምህርት፣ ጤና ፣ፍትህ፣ የኑሮ መሻሻል፣የመናገር መፃፍ ነፃነት ገና በልመና ሲሆን የምረጡኝ አስገድዶ ማሳመን የተለመደው ተግባርና ‘አውራው ፓርቲ’ አለኝ በሚለው የአምስት ዓመቱ የትዳር(ኮንትራት) ባለፈው ቅንጅትን መንታ ሲያደርግ ዘንድሮ ከምርጫው ጫጉላ ላይ …ሜንጫ ቦንድን ዋስ እድርጎ… መኢአድን እና አንድነት ፓርቲን ጥንድ የማድረጉ ጉዳይ “አውራው ፓርቲ ምንኛ የተዋጣለት አጥቂ ቢሆን ነው!?
    ** እንግዲህ እናንት በሻቢያህወአት የተፈጠራችሁ በኢህአዴግ ጥላ ሥር ብቻ ለመኖር በመፈቃቀድና በመፈቃቀር ቃል ገብታችኋል! ለእኛ በእኛ ብቻ የምትኖሩ መሆናችሁን አምናችኋል! ትናንት ያልነበራችሁ እኛ ስንፈጥራችሁ ማንነታችሁን አታውቁም ቀድሞ በባዶ እግራችሁ ትሄዱ ነበር አሁን ባቡር አይተው የማያውቁ መሳፈር ጀምረዋል…በጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የህወአት ጉዳይ አስፈፃሚ አቶ ኀይለመለስ ደስአለኝ….”
    http://www.youtube.com/watch?v=aU0vyc6X57A

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule