• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አገር ውስጥ እየኖሩ መሞት፣ በስደት ጉዞ መሞት፣ በስደት እየኖሩ መሞት!

December 13, 2014 03:21 am by Editor Leave a Comment

* አገር ውስጥ “ባርነት”፤ ከአገር ተሰድዶ “ባርነት”

ከጥቂት ቀናት በፊት በአገራቸው መኖር ያቃታቸው 70 ኢትዮጵያዊያን ቀይ ባህርን በጀልባ አቋርጠው ወደ የመን ሲያመሩ በደረሰ አደጋ ሁሉም መሞታቸው ተገልጾዋል። ኢህአዴግ እነዚህ በእርግጥ ኢትዮጵያውያን ለመሆናቸው ማስረጃ እንደሌለውና “እያጣራ” መሆኑን በቃል አቀባዩ በኩል ተናግሯል፡፡

በዚህ ዓይነት ሁኔታ ከአገራቸው እየተሰደዱ ለባህር፣ ለአውሬ፣ … የተዳረጉት ወገኖቻችን ብዛት ተቆጥሮ አያልቅም፡፡ ይህንን ሁሉ አልፈው ወዳሰቡት የደረሱት ደግሞ በስደት የሚኖሩባቸው በተለይ የአረብ አገራት ይህ ነው የማይባል ሰቆቃ ይደርስባቸዋል፡፡ ይህንን ሁሉ የሚሰማው ወገን አሁንም በየኤምባሲው ቪዛ ለማስመታት በተገኘው ቀዳዳ ከአገሩ ለመውጣት ይጥራል፡፡ በዚህ በኩል ያልተሳካለት ድንበር በማቋረጥ አስጨናቂውንና አስፈሪውን ጉዞ ይጀምራል፡፡

“አገር እየለማች” ነው ለሚለው ኢህአዴግ ይህ ምንም ዓይነት ምላሽ የሚሰጥበት ባይሆንም አሁንም “ለጊዜው የምጠብሰው ትልቅ አሣ አለና ጊዜ የለኝም” በማለት መስማት የተሳነው መሆኑን ይናገራል፡፡ አሽቃባጭ ካድሬዎቹም በየማኅበራዊ ድረገጾችና መገናኛ ብዙሃን “መጪው ጊዜ ከኢህአዴግ ጋር ብሩህ ነው” ይሉናል፡፡

በእንደዚህ ዓይነት ሁኔታ የስደት ህይወት ለመምራት እየወሰኑ የሚሄዱት ወገኖቻችን ከሚያስቡበት አገር ሲደርሱ ስለሚሆነው ሰሞኑን የወጣው የ2014 “የባርነት መለኪያ ዘገባ” በዘመናዊ ባርነት ውስጥ የሚገኙት ኢትዮጵያውያን ቁጥር 390ሺህ እንደሚገመት ተናግሯል፡፡ (የጎረቤት ኬኒያ 65ሺህ እንኳን አልደረሰም)

ከአረመኔ የባህር ላይ አስተላላፊዎች ያመለጡት ወይም “በልማት እየተመነደገች” ካለችው አገራቸው ኑሮን ማሸነፍ እያቃታቸው ወደ አረብ አገራት “በቪዛ” የሚወጡት በ“Global Slavery Index” መለኪያ መሠረት ለዘመናዊ ባርነት የሚጋዙ ናቸው፡፡

አገር ውስጥ ያለው “ዘመናዊ ባርያ” ኑሮን ማሸነፍ ያቃተውና የሰው ልጅ ሊሰራው የማይገባውን ሥራ የሚሠራ እንደሆነ ዘገባው ጠቆሟል፡፡ ከገጠር ወደ ከተማ የሚሰደደውና እዚያም በኑሮ ስቃይ ውስጥ የሚገባው ወላጅ ልጆቹን ለጎዳና ተዳዳሪነት፣ ለልመናና ለወሲብ ንግድ አሳልፎ ይሰጣል፡፡ ወደ ት/ቤት መላክ የሚገባቸው ህጻናት ሊሠሩት ቀርቶ ሊያስቡት የማይገባ እጅግ ዘግናኝና ሰቅጣጭ ሥራዎችን እንዲሰሩ ይገደዳሉ፡፡refugees and their boat

በአፍሪካ ቀዳሚውን ሥፍራ የያዘው የመርካቶ አካባቢ የመሸታና የሴተኛ አዳሪ ቤቶች ክምችት እንደሆነ የጠቆመው ዘገባ የዘመናዊ ባርነቱን ሁኔታ ይዘረዝራል፡፡ በዚህ ሁኔታ ከአገር ውስጥ “ዘመናዊ ባርነት” ያመለጡት ወደ አረብ አገራት “ለውጭ አገር ዘመናዊ ባርነት” ገንዘባቸውን እየከፈሉ ራሳቸውን በፈቃደኝነት ይሰጣሉ፡፡

በዚህ የባርነት ንግድ ያልጠገበው ኢህአዴግ በቅርቡ በሳውዲ የሆነውን የወገን ሰቆቃ ቸል በማለት የተቋተረጠበትን ገቢ እንደገና ለመጀመር “ሕግ እያረቀቀ” መሆኑ ተሰምቷል፡፡ ባርነቱን በመቀጠል ሽያጩን ለማጧጧፍና ትርፉን ለማጋበስ ረቀቅ ባለ ሁኔታ ዝግጅቱን አድርጓል፡፡ ባለሥልጣናቱም የአረቡን አገራት ጎብኝተው “በባርነት ንግዱ” ላይ ተስማምተው መጥተዋል፡፡ ይህንን “መልካም ዜና” የሰሙት “ተስፈኛ ዘመናዊ ባሪዎችም” ዓይናቸውን ጨፍነው ወደ ጭለማው ለመግባትና ህይወታቸውን ለባርነት አሳልፈው ለመስጠት ሙሉ ዝግጅት እያደረጉ ነው፡፡ እስከዚያው ለመጠበቅ ያልቻሉትና “ከአገር ውስጥ ዘመናዊ ባርነት” ሞትን የመረጡት አሁንም ድንበር እያቋረጡ ወደ ባህር ይጓዛሉ፡፡

ባለፉት የመጋቢትና የሚያዚያ ወራት ቁጥራቸው ከመቶ የሚያልፍ በተመሳሳይ አደጋ ሰጥመዋል፤ ለቀብር ሳይበቁ በውሃ ተበልተዋል፡፡ ያገራቸው “ህዳሴና ልማት” ሊያኖራቸው ያልቻለው አውሮጳን አልመው እስከዚያው የአረቢያ ምድርን ተስፋ አድርገው በምድርና በባህር የሚሰደዱት ኢትዮጵያውያን ቁጥር እየጨመረ ከመሄድ በቀር የመቀነስ ሁኔታ አይታይበትም፡፡ አውሮጳን ሳያልሙ “ለዘመናዊ ባርነት” ወደ አረቢያ የሚሰደዱት ምንም ተስፋ በሌለበት ሁኔታ እንኳን ከእነርሱ በፊት ሄደው የተሳካላቸውን ሰዎች በማሰብ እነርሱም ከእነዚያ መካከል እንደሚሆኑ በመገመት ጉዞ ያደርጋሉ፡፡ ከደረቁ ምድር ገና ለመሳፈር ሲነሱ ለባህር ወንበዴዎች ገንዘባቸውን ይከፍላሉ፤ ከዚያም ሲያልፍ የአካል ክፍላቸውን እያወጡ ይሸጣሉ፤ እዚያው በኢንፌክሽን ይሞታሉ፤ ከዚህ ያመለጡትና “ባርነትን” ተስፋ ያደረጉት ደረቅ ምድር ሳይደርሱ በባህር ይሰጥማሉ፡፡ ከዚህ ሁሉ የተረፉት ጥቂቶች ከባህርና ከአጓጓዥ አውሬዎች አምልጠው “ለዘመናዊ ባርነት ብቁ” ይሆናሉ፡፡ በባርነት “ያተረፉትን” ገንዘብ ወዳገራቸው ይልካሉ፤ ያገራቸውን “ኢኮኖሚ በድርብ አኻዝ” ያሳድጋሉ፤ “በልማቱ መስክ” ይሳተፋሉ፤ … “መጪው ጊዜ ከኢህአዴግ ጋር ብሩህ ነው!”


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am
  • ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ September 7, 2023 01:40 pm
  • “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል” September 7, 2023 01:31 am
  • ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል August 24, 2023 11:50 pm
  • ጀብደኛው August 24, 2023 10:06 am
  • ጎንደርና ባሕር ዳር ከተሞች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው ተመልሰዋል August 13, 2023 10:55 pm
  • ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች August 13, 2023 10:26 pm
  • ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ August 13, 2023 09:11 pm
  • ወደ ኤርትራ በኮንትሮባንድ የሚሻገሩ ቆሳቁሶች እየተያዙ ነው August 11, 2023 12:52 pm
  • የአማራ ክልል ትልልቅ ከተሞች ተኩስ ዓልባ ሆነው ውለዋል August 10, 2023 04:31 pm
  • “አንድ ሰው ለመግደል ኅንፃውን ማቃጠል” የኢ-ዲሞክራሲና ጽንፈኛ ኃይሎች ቅዠት፤ (ክፍል ሁለት) August 10, 2023 09:44 am
  • “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ August 10, 2023 09:08 am
  • በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ August 9, 2023 11:47 am
  • ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ  August 8, 2023 05:47 pm
  • “ሃሳብ ሲነጥፍ ነፍጥ አንግቤ እዋጋለሁ” የሚሉ አካላት ላይ እርምጃ ይወሰዳል – የመከላከያ ሠራዊት August 1, 2023 09:25 am
  • ደቡብ አፍሪካ የመሸጉ ወንጀለኞች ለሕግ ተላልፈው ሊሰጡ ነው July 31, 2023 09:27 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule