• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሌሊሴ ተፈታች! ቀጥሎስ?

August 13, 2013 06:48 am by Editor 3 Comments

ላለፉት 5 ዓመታት ያህል ከልጆቿና ባለቤቷ ተለይታ በእስር ስትማቅቅ የነበረችው ሌሊሴ ወዳጆ መፈታቷ በርካታ ኢትዮጵያውያንን ማስደሰቱ ተጠቆመ፡፡

የጋዜጠኛ ሌሊሴን መፈታት አስመልክቶ Ayyaantuu News Online ለንባብ ባበቃው ዜና እንዳመለከተው በስደት አውስትራሊያ ከሚኖረው ከባለቤቷና ከልጆቿ ጋር ተቀላቅላለች፤ ድረገጹ ዜናውን በምስል በማስደገፍም አቅርቦታል፡፡

በጋዜጠኝነት ሲያገለግል የነበረው ባለቤቷ ዳቢሣ ዋቅጂራ አገር ጥሎ መሰደዱን ተከትሎ በማታውቀው ምክንያት የኦነግ አባል ነሽ በማለት ኢህአዴግ 10ዓመት ያለ አመክሮ ፈርዶ ወኽኒ እንዳወረዳት ይታወሳል፡፡ ይህንን ህዝብን ያበሳጨና ያስቆጣ ጉዳይ ሌሊሴ ከታሰረችበት ጊዜ ጀምሮ አምነስቲ ኢንተርናሽናልና ዓለምአቀፉ የጋዜጠኞች መብት ጥበቃ ድርጅት (CPJ) ጨምሮ በርካታ ኢትዮጵያውያን ሲያወግዙትና እንድትፈታ ሲሟገቱ መቆየታቸው ይታወሳል፡፡

“በኢትዮጵያ የፖለቲካ እስረኛ የለም” በማለት ጠ/ሚ/ር ሃይለማርያም ደሳለኝ የተናገሩትን ተከትሎ ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ታህሳስ 24፤2005ዓም (January 2, 2013) በዘገበበት ወቅት፤ ጋዜጠኛ ሌሊሴ ወዳጆን የሰው ልጆችን ኅሊና ከሚፈታተኑት የማኅበራዊ ጉዳዮች ጋር በማያያዝ የግምባር ዜና አድርጓት እንደነበር ይታወሳል፡፡

ከአብራኳ የወጡትን ልጆቿን የማሳደግ ወግ የተነፈገችው እናት ከ3 ልጆቿ ጋር ሆና የሚያሳየውን ምስሏ አስደግፎ ጎልጉል በወቅቱ ሲዘግብ ጠ/ሚ/ር ሃይለማርያም ለተናገሩት ቅጥፈት ማጣፊያ በማድረግ ነበር፡፡

ከኦነግ ጋር ግንኙንት አለሽ ተብላ ከ3 ለጆችዋ ተነጥላ 10 ዓመት ጽኑ እስራት የተፈረደባት ሌሊሴ ወዳጆ
ከኦነግ ጋር ግንኙንት አለሽ ተብላ ከ3 ለጆችዋ ተነጥላ 10 ዓመት ጽኑ እስራት የተፈረደባት ሌሊሴ ወዳጆ

በእስር ቤት ታጉረው ከሚገኙት በርካታ የኢትዮጵያ ውድ ልጆች መካከል አንዷ ስለሆነችውና ስለአጠቃላይ የግፍ ቀንበር የተጫነባቸው ወገኖች በወቅቱ ለጎልጉል አስተያየት የሰጡት የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶ የአቶ ሃይለማርያምን ንግግር “በእውነቱ ይህ ፍጹም ቅጥፈት የተሞላበትና አጸያፊ ነው፤ እነዚህ እስረኞች እኮ በቁጥር የሚታወቁ ብቻ ሳይሆኑ ስም፣ ቤተሰብ፣ ልጅ፣ ዘመድ፣ ወዘተ አላቸው፡፡ እናውቃቸዋለን፤ ዓለም ያውቃቸዋል፤ እንግዲህ ጠ/ሚ/ሩ ለእነዚህ ልጆችና ቤተዘመዶች ነው አባታችሁ/እናታችሁ/ዘመዳችሁ ወንጀለኛ አሸባሪ ነው እንጂ የፖለቲካ እስረኛ አይደለም እያሉ ነው ያሉት፤ … ይህ ሥነምግባር የጎደለው ንግግር ነው” በማለት ዕርቃኑን አስቀርተውት ነበር፡፡

“ሌሊሴ ከዚህ ቀጥሎስ?” በሚል በህይወት የተፈተነችበትን የእስርቤት ቆይታዋና በተመሳሳይ ሁኔታ በእስር የሚማቅቁትን ኢትዮጵያዊ ወገኖቿን አስመልክቶ የሚደርስባቸውን ከአንደበቷ ለመስማት የሚጠብቁ ወገኖች እንደሚሉት ከሆነ “ሌሊሴ ጭንቀቷን ለተጨነቀላት የኢትዮጵያ ህዝብ የመፈታቷን ዜናና የእስር ቤት ቆይታዋን ከራሷ አንደበት እንሰማለን” ብለው እንደሚጠብቁ ይናገራሉ፡፡

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ለባለቤቷ፣ ለልጆቿ፣ ለቤተሰቦቿና ከእስር እንድትፈታ እንደየእምነታቸው ለጸለዩና ለተጨነቁ በሙሉ በጋዜጠኛ ሌሊሴ ወዳጆ መፈታት እንኳን ደስ አላችሁ ይላል፡፡

ከዚህ ጋር በተያያዘ በየእስርቤቱ የሚማቅቁትን የቤተሰብ አውራና የአገር ተረካቢዎች፣ የፖለቲካ መሪዎች፣ ጋዜጠኞች፣ የድምጻችን ይሰማ አስተባባሪዎች እና ሌሎች ንጹሃን ዜጎች መንግሥት እስርቤት አጉሮ ዕርምና ቂም ራሱ ላይ ከሚከምር ተመሳሳይ እርምጃ በመውሰድ ችግሩን ቢያስተነፍስና ወደ ዕርቅ ቢመጣ የተሻለ እንደሆነ የአገር ጉዳይ የሚያሳስባቸው የመብት ተሟጋቾች ምክራቸው ይሰጣሉ፡፡ (ፎቶዎቹ የተወሰዱተ ከ Ayyaantuu News Online)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. koster says

    August 13, 2013 07:38 am at 7:38 am

    I hope she is not mentally castrated and terrorized not to speak out. We should always stand for truth and justice and say no to woyane ethnic fascists, ethnic cleansing and state terrorism in Ethiopia. A free and democratc Ethiopia is good for all except woyane Killers and looters who are afraid to face justice when there will be rule of law in Ethiopia.

    Reply
  2. aradaw says

    August 13, 2013 07:59 pm at 7:59 pm

    It is a pleasure to see smiling faces on the family. It is a matter of time and justice will be served to those who terrorize and torture innocent people. They have taken away so many years from the mother not to be with her family and nurture her kids. Why these kids have to go through this. The never ending cruelties of TPLF (ህዋሳት)

    Reply
  3. Truneh says

    August 16, 2013 03:16 am at 3:16 am

    ተራራውን ደልዳላ ሜዳ፣ ድቅድቁን ጨለማ ብርሃን የሚያደርግ፥ እንደ እግዚአብሄር ያለ ማነው?
    እንዲያ ለዓመታት ባለቤትሽንና ዓንችን ያስቆዘመውን ኃይለኛ ክፉ ሰው መለስ ዜናዊን ወደጉድጓድ ዓወርዶ ዓንችን በከፍታ ስፍራ ላይ በክብር ያራመደ እግዚአብሔር ምስጋና ይድረሰው::
    ወይዘሮ ሌሊሴ ወዳጆ፥ እንኳን ደስ ያለሽ የእኔ እህት፥ ከቆንጆ ልጆችሽ፣ ከምትወጅውና ከሚወድሽ ባለቤትሽ ጋር በሰላም ስለተቀላቀልሽ በግፍ መታሰርሽን ያወቀ ኢትዮጵያዊ ሁሉ እጅግ ተደስቷል፥

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule