• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሌሊሴ ተፈታች! ቀጥሎስ?

August 13, 2013 06:48 am by Editor 3 Comments

ላለፉት 5 ዓመታት ያህል ከልጆቿና ባለቤቷ ተለይታ በእስር ስትማቅቅ የነበረችው ሌሊሴ ወዳጆ መፈታቷ በርካታ ኢትዮጵያውያንን ማስደሰቱ ተጠቆመ፡፡

የጋዜጠኛ ሌሊሴን መፈታት አስመልክቶ Ayyaantuu News Online ለንባብ ባበቃው ዜና እንዳመለከተው በስደት አውስትራሊያ ከሚኖረው ከባለቤቷና ከልጆቿ ጋር ተቀላቅላለች፤ ድረገጹ ዜናውን በምስል በማስደገፍም አቅርቦታል፡፡

በጋዜጠኝነት ሲያገለግል የነበረው ባለቤቷ ዳቢሣ ዋቅጂራ አገር ጥሎ መሰደዱን ተከትሎ በማታውቀው ምክንያት የኦነግ አባል ነሽ በማለት ኢህአዴግ 10ዓመት ያለ አመክሮ ፈርዶ ወኽኒ እንዳወረዳት ይታወሳል፡፡ ይህንን ህዝብን ያበሳጨና ያስቆጣ ጉዳይ ሌሊሴ ከታሰረችበት ጊዜ ጀምሮ አምነስቲ ኢንተርናሽናልና ዓለምአቀፉ የጋዜጠኞች መብት ጥበቃ ድርጅት (CPJ) ጨምሮ በርካታ ኢትዮጵያውያን ሲያወግዙትና እንድትፈታ ሲሟገቱ መቆየታቸው ይታወሳል፡፡

“በኢትዮጵያ የፖለቲካ እስረኛ የለም” በማለት ጠ/ሚ/ር ሃይለማርያም ደሳለኝ የተናገሩትን ተከትሎ ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ታህሳስ 24፤2005ዓም (January 2, 2013) በዘገበበት ወቅት፤ ጋዜጠኛ ሌሊሴ ወዳጆን የሰው ልጆችን ኅሊና ከሚፈታተኑት የማኅበራዊ ጉዳዮች ጋር በማያያዝ የግምባር ዜና አድርጓት እንደነበር ይታወሳል፡፡

ከአብራኳ የወጡትን ልጆቿን የማሳደግ ወግ የተነፈገችው እናት ከ3 ልጆቿ ጋር ሆና የሚያሳየውን ምስሏ አስደግፎ ጎልጉል በወቅቱ ሲዘግብ ጠ/ሚ/ር ሃይለማርያም ለተናገሩት ቅጥፈት ማጣፊያ በማድረግ ነበር፡፡

ከኦነግ ጋር ግንኙንት አለሽ ተብላ ከ3 ለጆችዋ ተነጥላ 10 ዓመት ጽኑ እስራት የተፈረደባት ሌሊሴ ወዳጆ
ከኦነግ ጋር ግንኙንት አለሽ ተብላ ከ3 ለጆችዋ ተነጥላ 10 ዓመት ጽኑ እስራት የተፈረደባት ሌሊሴ ወዳጆ

በእስር ቤት ታጉረው ከሚገኙት በርካታ የኢትዮጵያ ውድ ልጆች መካከል አንዷ ስለሆነችውና ስለአጠቃላይ የግፍ ቀንበር የተጫነባቸው ወገኖች በወቅቱ ለጎልጉል አስተያየት የሰጡት የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶ የአቶ ሃይለማርያምን ንግግር “በእውነቱ ይህ ፍጹም ቅጥፈት የተሞላበትና አጸያፊ ነው፤ እነዚህ እስረኞች እኮ በቁጥር የሚታወቁ ብቻ ሳይሆኑ ስም፣ ቤተሰብ፣ ልጅ፣ ዘመድ፣ ወዘተ አላቸው፡፡ እናውቃቸዋለን፤ ዓለም ያውቃቸዋል፤ እንግዲህ ጠ/ሚ/ሩ ለእነዚህ ልጆችና ቤተዘመዶች ነው አባታችሁ/እናታችሁ/ዘመዳችሁ ወንጀለኛ አሸባሪ ነው እንጂ የፖለቲካ እስረኛ አይደለም እያሉ ነው ያሉት፤ … ይህ ሥነምግባር የጎደለው ንግግር ነው” በማለት ዕርቃኑን አስቀርተውት ነበር፡፡

“ሌሊሴ ከዚህ ቀጥሎስ?” በሚል በህይወት የተፈተነችበትን የእስርቤት ቆይታዋና በተመሳሳይ ሁኔታ በእስር የሚማቅቁትን ኢትዮጵያዊ ወገኖቿን አስመልክቶ የሚደርስባቸውን ከአንደበቷ ለመስማት የሚጠብቁ ወገኖች እንደሚሉት ከሆነ “ሌሊሴ ጭንቀቷን ለተጨነቀላት የኢትዮጵያ ህዝብ የመፈታቷን ዜናና የእስር ቤት ቆይታዋን ከራሷ አንደበት እንሰማለን” ብለው እንደሚጠብቁ ይናገራሉ፡፡

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ለባለቤቷ፣ ለልጆቿ፣ ለቤተሰቦቿና ከእስር እንድትፈታ እንደየእምነታቸው ለጸለዩና ለተጨነቁ በሙሉ በጋዜጠኛ ሌሊሴ ወዳጆ መፈታት እንኳን ደስ አላችሁ ይላል፡፡

ከዚህ ጋር በተያያዘ በየእስርቤቱ የሚማቅቁትን የቤተሰብ አውራና የአገር ተረካቢዎች፣ የፖለቲካ መሪዎች፣ ጋዜጠኞች፣ የድምጻችን ይሰማ አስተባባሪዎች እና ሌሎች ንጹሃን ዜጎች መንግሥት እስርቤት አጉሮ ዕርምና ቂም ራሱ ላይ ከሚከምር ተመሳሳይ እርምጃ በመውሰድ ችግሩን ቢያስተነፍስና ወደ ዕርቅ ቢመጣ የተሻለ እንደሆነ የአገር ጉዳይ የሚያሳስባቸው የመብት ተሟጋቾች ምክራቸው ይሰጣሉ፡፡ (ፎቶዎቹ የተወሰዱተ ከ Ayyaantuu News Online)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. koster says

    August 13, 2013 07:38 am at 7:38 am

    I hope she is not mentally castrated and terrorized not to speak out. We should always stand for truth and justice and say no to woyane ethnic fascists, ethnic cleansing and state terrorism in Ethiopia. A free and democratc Ethiopia is good for all except woyane Killers and looters who are afraid to face justice when there will be rule of law in Ethiopia.

    Reply
  2. aradaw says

    August 13, 2013 07:59 pm at 7:59 pm

    It is a pleasure to see smiling faces on the family. It is a matter of time and justice will be served to those who terrorize and torture innocent people. They have taken away so many years from the mother not to be with her family and nurture her kids. Why these kids have to go through this. The never ending cruelties of TPLF (ህዋሳት)

    Reply
  3. Truneh says

    August 16, 2013 03:16 am at 3:16 am

    ተራራውን ደልዳላ ሜዳ፣ ድቅድቁን ጨለማ ብርሃን የሚያደርግ፥ እንደ እግዚአብሄር ያለ ማነው?
    እንዲያ ለዓመታት ባለቤትሽንና ዓንችን ያስቆዘመውን ኃይለኛ ክፉ ሰው መለስ ዜናዊን ወደጉድጓድ ዓወርዶ ዓንችን በከፍታ ስፍራ ላይ በክብር ያራመደ እግዚአብሔር ምስጋና ይድረሰው::
    ወይዘሮ ሌሊሴ ወዳጆ፥ እንኳን ደስ ያለሽ የእኔ እህት፥ ከቆንጆ ልጆችሽ፣ ከምትወጅውና ከሚወድሽ ባለቤትሽ ጋር በሰላም ስለተቀላቀልሽ በግፍ መታሰርሽን ያወቀ ኢትዮጵያዊ ሁሉ እጅግ ተደስቷል፥

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule