• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኢህአዴግን በጓሮ ድርድር የጠየቀበት ሰነድ ተተረጎመ!

April 18, 2013 06:41 am by Editor 3 Comments

በልማትና ኢንቨስትመንት ስም ኢህአዴግ ለውጪና ለራሱ ሰዎች እየቸበቸበ ያለውን መሬት አስመልክቶ የኦክላንድ ተቋምና የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ በጋራ ያዘጋጁት ጥናታዊ ዘገባ አማርኛ ትርጉም በሳምንቱ መጨረሻ ይፋ ይደረጋል ተባለ። የመሬት ነጠቃ ዜጎችን እያፈናቀለና ውድ የተፈጥሮ ሃብትን እየበላ ነው።

እመራቸዋለሁ ለሚለው ህዝብና አገር ደንታ የሌለው ኢህአዴግ፣ በመረጃ ለሚያጭበረብራቸው ዜጎች የተሟላና የተመጣጠነ ዘገባ እንደሚያቀርብ የተነገረለት ይህ ሰነድ በአማርኛ ተተርጉሞ ይፋ እንደሚሆን የገለጸው የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ የሚዲያና የህዝብ ግንኙነት ዴስክ ነው።

የጋራ ንቅናቄው የህዝብ ግንኙነት ዴስክ በተለይ ለጎልጉል በሰጠው መረጃ በጥናቱ ሰለባዎች፣ የኢህአዴግ ባለስልጣናት፣ ኢንቨስተሮች፣ ጉዳዩ የሚመለከታቸው ክፍሎች፣ የቅርብ ምስክሮች፣ የተለያዩ ከዓለምአቀፍ ተቋማት የተገኙ መረጃዎች፣ መንግስት ራሱ ይፋ ያደረጋቸው መረጃዎችና ለጥናቱ አስፈላጊ የተባሉ አኻዞች ተካተውበታል።

በዚሁ መሰረት ኢህአዴግ በልማትና በኢንቨስትመንት ስም “ጥቅም ላይ ያልዋለ መሬት” በማለት ለንግድ ማቅረቡና፣ ይህም በመደረጉ አገሪቱ ውስጥ ልማት እንደሚስፋፋ የሚሰብከው ስብከት ያለ አንዳች ማስተባበያ እርቃኑን የሚያስቀረው ሪፖርት በዋናነት የተዘጋጀው መረጃ ለጠማው ህዝብ እንደሆነ ዴስኩ አስታውቋል።

አገራቸውን፣ መሬታቸውንና መንግስትን አምነው የሚኖሩ ዜጎችን በገንዘብ በመለወጥ ያፈናቀለውና እያፈናቀለ ያለው ኢህአዴግ፣ ምትክ የሌላቸውን እድሜ ጠገብ የተፈጥሮ ደኖች ጨፍጭፏል፤ አቃጥሏል፤ አውድሟል። ሰፊ መሬት ምድረ በዳ አድርጓል። ያለ አንዳች ምክርና ውይይት ዜጎችን አፈናቅሎ ለመከራ ዳርጓል። ንብረታቸውንና ማሳቸውን እንደ ባዕድ በዶዘር ጠርጎባቸዋል። ለመቃወም በሞከሩ ወገኖች ላይ የባዕድ ወራሪ ሃይል ይፈጽመዋል ተብሎ የማይገመት ወንጀልና መከራ አድርሷል። የጋራ ንቅናቄው የሚዲያ ዴስክ እንዳለው ኢህአዴግ ይህንን ሁሉ ሲፈጽም ጎን ለጎን ዜጎችን በመረጃ እያጭበረበረና እያስራበ በመሆኑ አሁን ይፋ የሚደረገው ሪፖርት ታላቅ ፋይዳ ይኖረዋል።

ለጋሽ ድርጅቶች፣ ዓለም አቀፍ ማህበረሰብና አበዳሪ ድርጅቶች አቋማቸውን እንዲመረምሩ ለማስቻል ሰፊ ስራ እየተሰራ መሆኑንን ያወሳው የጋራ ንቅናቄው “የመሬት ወረራው መቆሚያ የሌለው፣ እንዲያውም በቀጣይነት የሚከናወን በመሆኑ ይፋ የሚደረገው ይህ መረጃ አገር ቤት ገጠር ሳይቀር ዘልቆ እንዲገባ ለማድረግ ዝግጅቱ ተጠናቋል” በማለት አስረድቷል። ይሁን እንጂ መረጃው እንዴት እንደሚሰራጭ ዝርዝር ማብራሪያ አላቀረበም።

ወደፊት ጥናትና ምርምር የሚያካሂዱ ተቋማትም ሆነ ግለሰቦች ሊጠቀሙበት እንዲችሉ ተደርጎ በዝርዝር የቀረበው ይህ ሪፖርት፣ በእንግሊዝኛው ጥቅል ጥናት ውስጥ በሰባት የአፍሪካ አገራት ተከፋፍሎ የተዘጋጀ ሲሆን ወደ አማርኛ በተቀየረው ትርጉም ውስጥ ሙሉ ትኩረት የተደረገው በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ እንደሆነ ተመልክቷል።

congress briefings
አቶ ኦባንግ በም/ቤቱ ውይይት ወቅት ማብራሪያ ሲሰጡ

“በኢንቨስትመንት ስም የሚፈጸም የመሬት ነጠቃ በኢትዮጵያ” በሚል ርዕስ በሦስት ዓቢይ ምዕራፎችና በበርካታ ንዑሳን ክፍሎች ተከፋፍሎ የተዘጋጀው ከ110 ገጽ በላይ የሆነው የአማርኛው ጥናታዊ ሪፖርት “የሰከነው” ትግል ውጤት እንደሆነ የመረጃ ዴስኩ አስታውቋል። በቅርቡ የጋራ ንቅናቄው ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶ ህንድ በመሄድ ያነሳሱት የትግል አብሮነት ስሜት ያነሳሳ ነበር፡፡ ከሁለት ቀናት በፊት ደግሞ ሰኞ ዕለት በአሜሪካው ምክርቤት ለውይይት በመሬት ነጠቃ ጉዳይ ላይ የቀረበውና ከፍተኛ ትኩረት የተሰጠውን ይህንኑ የመሬት ነጠቃ ጉዳይ በምክርቤት ተገኝተው ገለጻ ከሰጡት መካከል አቶ ኦባንግ አንዱና ዋንኛው መሆናቸውን የሚዲያ ክፍሉ ጨምሮ አስታውቋል፡፡ ይህም ለመሆን የቻለውና ጉዳዩ በከፍተኛ ደረጃ ተደማጭነት እያገኘ የመምጣቱ ሁኔታ ከፍተኛ ድል እየሆነ ከመምጣቱ የተነሳ ኢህአዴግ የሚተማመንባቸውንና ከፍተኛ የገንዘብ ምንጭ የሆኑ አገራትንና ተቋማት እጅ የማስጠምዘዝ ሁኔታ ሊያስከትልበት እንደሚችል በመገንዘብ ካድሬዎቹን በየቦታው በማሰማራት ከፍተኛ የውስወሳ ዘመቻ እያካሄደ እንደሚገኝ ለመገንዘብ ተችሏል፡፡ በዚህ ረገድ የጋራ ንቅናቄው እጅግ ከፍተኛ ሥራ ላይ የተጠመደ መሆኑን ጨምሮ ተገልጾዋል፡፡

የጋራ ንቅናቄው አክሎ በሰጠው ማሳሰቢያ አደራም አስተላልፏል። በሳምንቱ መጨረሻ ይፋ የሚደረገው ይህ ጥናታዊ ሪፖርት ምንም እንኳ የጋራ ንቅናቄው ንብረትና የኮፒ ራይት ያለው ቢሆንም “ሪፖርቱን ለማራባትና ለማሰራጨት የሚፈልጉ ሁሉ ለሪፖርቱ ባለቤትና አዘጋጆች ጨዋነት የተሞላው እውቅና ሊሰጡ ይገባል” ሲል ጥሪውን አቅርቧል። በማያያዝም በሚቻላቸው መንገድ ሁሉ ሪፖርቱን ለማራባት ለሚተባበሩ ወገኖች ከወዲሁ ምስጋናውን አቅርቧል። ሪፖርቱ እንዲደርሳቸው ለሚፈልጉ ሁሉ በኢሜል ለመላክ ፈቃደኛ በመሆኑ በሚከተለው አድራሻ media@solidaritymovement.org ጥያቄ ቢያቀርቡ እንደሚተባበር አመልክቷል። የመሬት ነጠቃን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ የሚያካሂደውን እቅድን መሰረት ያደረገ ትግል አጠንክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጧል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Teshale says

    April 19, 2013 04:37 pm at 4:37 pm

    Wonderful job. This is the kind of job that those opposing the government should do. This proactive action will put TPLF government on the defensive. For the most part, those opposing the TPLF government are reacting when it does something. We need to keep TPLF busy defending itself and have no time to brew yet another disaster in Ethiopia and its people. What SMNE is doing on the land issue is clearly a proactive job that is a step ahead of TPLF and forcing it to react than act. Thank you SMNE.

    Reply
  2. gelam says

    April 20, 2013 01:54 am at 1:54 am

    If people want to talk, they always have some thing to say regardless of the rationality of their topic. When the country was in drought and famine, they used to say ‘Green drought’ to mean that the country is poor while having fertile land. And now, when the country started to utilize its resources, they made a U-turn and they are telling us to stop farming our fertile land. for an average Ethiopian, it is not hard to imagine what some outsider groups/individuals/or countries would benefit if the country remains always poor. But for the opposition diaspora and the like, shame on you! study history and politics before you open your mouth.

    – “for the betterment of the country, the feudal system must be removed” …. Derge
    -“for the betterment of the country, the military dictator must be removed”…..Woyane
    -“for the betterment of the country, Woyane must be removed”…..opposition Diaspora.
    -“for the betterment of the ……….”

    When do you think this cycle will have an end?
    In my opinion, it will never end unless we are aware of our outside enemies. Ethiopia’s enemy’s are always enemies. They do not care about the governments. They help a certain group to come to power and the time that group becomes stronger, they train another group in order destroy the former one. In this situation, the countries always remains between RAISE and FALL states.Political game. I think the opposition diaspora are playing a political game without knowing the rules of the game. The rules of the game are in the hand of other masters (the outsiders).

    Reply
  3. andnet berhane says

    May 16, 2013 04:46 pm at 4:46 pm

    አንድን ሕዝብ አንድን ሃገር በመወከል ተጨባችና ተአማኒነት ያለው ተግባርና የትግል ርብርቦሽ በማድረግ ጉዳዩን ለዓለም ሕብረተሰብ በይፋ ወያኔን ማጋለጥ ለደረጉት ታአልቅ አስተዋጽኦ አቶ አቦንጋ ሜቶን እንዲሁም አኢጋን አባላትንና ድርጅጀት እንዲሁም የኦክላንድ ዩኒቨርሲቲ ጥናት ዳይረክተርና የትምሕርቱን ተቋም ታላቅ ምስጋና ይድረሳቸው ።
    የመሬት ነጠቃው ስውርና የሃገርና የሓዝቦችን ኑሮና መሰረት ያናጋ የዘመናችን ፋሽሽታዊ ስራአት ለመሆኑ ለዚህም ተወቃሾች ያለጥናትና በጥቅምና በፖሊሲ መዛባት የሚሰሩትን የምእራብ ሃገራት አመራሮች ጭምር የሚያስወቅስና እሚያስጠይቅ ፡ ከመሆኑ ባሻገር ለወደፊቱ ከዓለም ሕብረተሰብ ተአማኒነት የሚያሳጣ ስራ በመስራት የዓለምን ሰላምና ከመረጋጋት እንደሚያደፈርስ ያለመመልከት በጥቂት እበላ ባዮች ዘራፊ ሃብታሞች ዓለምን ወደከፋ የጦርነት አውድማ የሚያደርስ ደርጊት ካሁኑ ካልቆመ አሳሳቢነቱ ካለንበት ዘመን የከፋ ለመሆኑ ማውወቅ ያስፈልጋል፡ በኢትዮጵያ ያለው የማፈናቀልና የመሬት ዝርፊያ እንዲሁም በሌላው አፍሪካ ሃገራት የተረጋጋ ሰላምና እድገት እንደማያመጣ እየተወቀ በህዝቦችና በሃገሮች የተሰነዘረ የጥፋት ሽብር ለመሆኑ ሁሉም ያገባኛል የሚል በጥብቅ ማውገዝና በዚህ የትግል ሰልፍ ያቅሙን ማበርከት ሃገራዊ ኃላፊነት አለበት፡
    መረት የአንድ ዜጋ መታወቅያው መግላጫው ነው ፡ መንግስት የህዝቦችን ጥቅም ለማስጠበቅ በምርጫና በተሰተው ሃገራዊ መተዳደርያ ሕግ ከሌላው ዓለም ግንኙነት ባማድረግ በመደራደር ለሃገር ጠቃሚና የሕዝብን ኑሮና የእውቀት እጤናና የእርሻን የመገናኛን በመዘርጋት የተሰጠውን አደራ በተግባር ተርጉሞ ኃላፊነቱን መወጣት እንጂ፡ እንድ ኢኅዴግ ሃገርና ሕዝብን መሸጥና መዝረፍ አስነዋሪና ሕገወጥ ስራ በድፍረት መሬት የመንግስት የሚለው ዓለም አቀፍ ወንጀልና (በጅምላ ጭፍጨፍ )ለመሆኑ ሁሉም ዜጋ ጠንቅቆ ማወቅና ይህንን ተግባር ሩቅ ሳይሄድ ለማምከን ጽናታዊ ሞራላዊ አይምራዊ የሆነ ትግል አማራጭ የሌለው በመሆኑ ሁሉም ይተባበር ፡

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm
  • የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት? January 23, 2025 03:41 pm
  • ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ? January 23, 2025 03:04 pm
  • የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተወልደ አስተዳደር ዘመን ለተሠራ ስህተት 425ሺ ዶላር ተቀጣ December 14, 2024 01:44 am
  • በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል November 27, 2024 12:09 pm
  • የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን እንዲያርም ጥብቅ መመሪያ ተሰጠው November 27, 2024 11:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule