አንደኛዋ ባለቤታቸው ሶስት ጊዜ ቀዶ ጥገና አድርጋለች። ሌላኛዋ ባለቤታቸው ከአንድ ልጇ ጋር ሁሉም እስር ላይ ናቸው። እመጫትም ከእርጥብ ልጇ ጋር ታስራለች። እነዚህ ማሳያ እንጂ በኮንሶ ከእስር የተረፉ ተሰደዋል። በወረዳው ያሉት 43 ትምህርት ቤቶች እስር ቤቶችና የወታደሮች ካምፕ ሆነዋል። ወደ አጎራባች ቀበሌ ወይም ጫካ የመሸጉ ሰዎች ህይወታቸውን የሚገፉት በመከራ ነው። ይህ ሁሉ ምሬት ሲሰማ ክልሉ ምንም ነገር እንደሌለ ነው የሚናገረው – ኮንሶ ግን ፍጹም ግፍ የሚፈጸምባት ሆናለች!
ህዳር 27 ቀን 2016 ቪኦኤ ያናገራቸው ሁለት የኮንሶ ነዋሪዎች “ኮንሶዎች የሚኖሩት በሌላዋ ኢትዮጵያ ነው” ይላሉ። በኮንሶ መተንፈስ አይቻልም። መቃወም አይፈቀድም። ጥያቄ ማቅረብ ክልክል ነው። የሚማርበትን ዩኒቨርሲቲና የራሱን ስም ለጥንቃቄ ሲል በመደበቅ አጭር ቃለ ምልልስ ያደረገው የኮንሶ ተወላጅ “የሚረዳኝ የለምና ትምህርት አቁሜያለሁ። በኮንሶ የሚሆነውን ለመናገር ቃል የለኝም። መግለጽም አልችልም። ተጨንቄያለሁ…” በማለት ተናግሯል።
“እህቴ ታስራለች፤ አባቴ ታስሯል፤ አጎቶቼ ታስረዋል፤ ኑሯችን ዝቅተኛ በመሆኑ የሚረዱኝ እናቶቼና አባቶቼ ሁሉም እስር ላይ ናቸው” የሚለው የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ጨክኖ ወደ ዩኒቨርሲቲው እንዳይሄድ የሰጋበትን ሌላም ምክንያት ተናግሯል። ጋዜጠኛዋ ለምን ወደ ትምህርቱ እንደማይመለስ ጠይቃው “የኮንሶ ልጆች እየታደኑ ይታሰራሉ” ሲል ነው የመለሰላት።
በኮንሶ አገልግሎት የለም። ሰራተኞች ደሞዝ ቆሞባቸዋል። ማሳ ላይ የሚገኙ ይታሰራሉ። አንድ የህክምና ጣቢያ ሲቀር ሁሉም ተዘግተዋል። ትምህርት ቤቶች ስራ አቁመዋል። የቻለ ተሰድዶ አገር ለቋል። የጨከኑም ጫካ ናቸው። አቅም ያጡ እስረኞች ሆነዋል። በኮንሶ ህይወት እንዲህ ሆናለች። ለዚህም ነው “የምንኖረው ሌላዋ ኢትዮጵያ ውስጥ ነው” የሚሉት።
ግፍ እየተንተከተከባት ካለችው ኢትዮጵያ በየአቅጣጫው የሚሰማው ምሬት ነው። የዩኒቨርሲቲው ተማሪም ያለው ይህንኑ ነው። “ለምን ሰውን እንደዚህ ያሰቃዩታል፤ ያማርሩታል?” በኮንሶ የሚደርሰውን በደል ይፋ ለማድረግ የመገናኛ ችግር መኖሩን ያስታወቀው ይህ ተማሪ ጫካ ውስጥ የመስተጋብር (ኔትወርክ) ችግር መኖሩ፣ ስልክን ቻርጅ ለማድረግ ኤሌክትሪክ መጥፋቱ፣ አብዛኛው ህዝብ ሸሽቶ ጫካ መኖሩ የግንኙነት መረቡን በጥሶታል።
“ራስን በራስ የማስተዳደር ጥያቄን ለምን አነሳችሁ” በሚል ህዝብ የመረጣቸውን የአካባቢው ተወላጆች በማሰር የተጀመረው የኮንሶ ችግር ቅጥ ያጣ ስለመሆኑ መረጃ መውጣት ከጀመረ ቢቆይም አስተዳዳሪ ነን የሚሉት ክፍሎች መፍትሔ ሊፈለጉ አልቻሉም ወይም አልፈለጉም። አሁን የሚፈራው ድርቅ የከፋ ጉዳት እንዳያደርስ ነው። ቪኦኤ ያነጋገራቸው ሁለት ወገኖች እንዳሉት ያረሰ፣ የዘራ የለም። ሰብል የለም። ምን ሊበላ ይሆን?
የክልሉ ቃል አቀባይ ምላሽ እንዲሰጡ ቢደወልላቸው ሊገኙ አልቻሉም። የክልሉ የፖሊስ ኮሚሽነርም በተመሳሳይ ስልካቸውን አይመልሱም። ሃይለማሪያም ደሳለኝ “ያልተመለሰ የማንነት ጥያቄ የለም” ሲል የኮንሶን ጉዳይ ማጣጣሉ አይዘነጋም።
በኢትዮጵያዊነታቸው ስለማይደራደሩት ኮንሶዎች ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ መስከረም 6፤ 2009 (September 16, 2016) “ህወሃቶች – ምንድነው የሚፈልጉት? ደም አይጠግቡም?” በሚል ርዕስ ባወጣው ዜና የኮንሶን ሕይወት በተመለከተ ከዓይን እማኞች በማግኘት ያተመው መረጃ እንዲህ ይነበባል፤
“እኔ እስከማውቀው ድረስ የመንግስት ኃላፊነት ህግን ማስከበር፣ ሰላምን ማስፈን እንዲሁም ግጭት ሲፈጠር እንደ ገለልተኛ ሆኖ ለየትኛውም ወገን ሳያዳላ የማረጋጋት ሥራን መስራት ነው። አሁን አሁን በኢትዮጵያ እየሆነ ያለው ግን ከዚህ የተቃረነ መሆኑ ባያጠያይቅም በኮንሶ ምድር ከጳጉሜ 5 ጀምሮ እስካሁኑ ደቂቃና ሰከንድ ድረስ እየሆነ ያለው ግን እጅግ የሚዘገንን ከአንድ መንግስት ቀርቶ በሀገር ጠላት ላይ እንኳን ለመፈፀም የሚከብድ የአንድን ብሔር ዘር ማጥፋትን ኢላማ ያደረገ ዘመቻ በፈደራል ፖሊስና በደቡብ ክልል ልዩ ሃይል ቅንጅት በኮንሶ ህዝብ ላይ እየተካሔደ ይገኛል።
“እንደሚታወቀው የኮንሶ ህዝብ ከሰገን ዞን ወጥቶ ራሱን በራስ ማስተዳደር ይችል ዘንድ ራሱን ችሎ በዞን ለመደራጀት ከዓመት በፊት ኮሚቴ አዋቅሮ ደረጃ በደረጃ ጉዳዩ ለሚመለከታቸው መንግስታዊና መንግስታዊ ላልሆኑ ተቋማት እንዲሁም የኢህአዴግ እህት ድርጅቶችና ለውጭ ኤምባሲዎች ጭምር ማሳወቁ ይታወቃል።
“ይህ ጥያቄ ከዓመት በፊት ቀርቦለት የቃል መልስ ለመስጠት እንኳን ዓመት ሙሉ የፈጀበት የደቡብ ክልል መጀመሪያውኑ ጥያቄውን ተቀብሎ በህገ መንግስቱ መሰረት ከመመለስ ይልቅ ጥያቄውን በጉልበት እንደሚቀለብስ በተደጋጋሚ እየዛተ “ኮንሶ የሲኒ ውስጥ ማዕበል ነው፤ በአንድ ዘር ማጥፋት ይቻላል” ምናምን በማለት ለዓመታት ያቀደውን እቅድ አሁን ተግባር ላይ በማዋል ላይ ይገኛል።
“ዕቅዳቸውን ከግብ ለማድረስም በመጀመሪያ ከፌዴራል መንግስት ፍቃድ በማግኘት ጳጉሜ 5 ቀን 2008 አንድ የሰገን ዞን ተላላኪ አቶ ከተማ ካሽለ ከአጋሮቹ በምሥጢር የሰማውን የደቡብ ክልል የኮንሶ ብሔርን ከምድረ ገፅ የመገርሰስ ጥማት የፈደራል መንግስት መፍቀዱ ብቻ ሳይሆን አጋርነቱን እንደገለፀላቸው በመተማመን ሀላኮ (ታራ ማንጋሻ) የሚባል መንደር ማምሻውን ሄዶ እናቃጥላችሁሃለን፣ እንጨርሳችኋለን፣ በታቀደው መሰረት ዘራችሁን ከምድር ላይ እናጠፋለን በማለት ከደነፋ በኋላ ወዲያው ተሰወረ። ይህን የሰማው ሰላማዊ ህዝብ ውሸቱን ነው በማለት ተዘናግቶ እንዳለውም ምሽት ላይ ከሻላሎ በኩል ኮንሶን በከዱ ከሃዲዎች አማካኝነት መተረየስ ተጥምዶ ተኩስ ተከፈተባቸው። የሀላኮ ህዝብም ተደናግጦ ልጆችን ወደ ኋላ እያሸሹ መከላከል ጀመሩ ጠብ ጫሪዎቹም ከህዝቡ ጋር እስከ ሌሊቱ 8፡00 ተዋጉ በዚህ ሁሉ ግን ህይወት ሳይጠፋ ህዝቡ 3 ቀበሌዎችን አልፎ ቢያባርራቸውም ከ3 ቤት ቃጠሎ ውጪ ምንም ጉዳት በንብረትም ሆነ በሰው አካል ላይ ሳይደርሱ ወደ ቤታቸው ተመለሱ።
“በ01/01/2009 የመጀመሪያ ንድፋቸውን ያሳኩት የሰገን ዞንና የደቡብ ክልል አመራሮች ኮንሶ ጦርነት ቀስቅሷል በማለት በርካታ ልዩ ሃይልና የፌዴራል ፖሊሶችን ወደ ሰገን ዞን አስገቡ። ከዚያም ማታ ላይ ወደ ሻላሎ ስራዊቱን አስገብተው የኮንሶ ገሃዲ የሻላሎ ነዋሪዎች በሻላሎ ውስጥ ያሉትንና የኮንሶ ጥያቄን የሚደግፉትን ቤቶች በፌዴራልና ልዩ ኃይል ታግዘው ሙሉ በሙሉ አቃጠሉ።
“ምሽት ላይ ቤቱን ካስቃጠሉ በኋላ ሰራዊቱ ወደ ሰገን ከተማ ሲመለስ ገሃዲዎቹ ብቻቸውን አቅም እንደለላቸው ቢያውቁም በታዘዙት መሰረት በሀላኮ መንደር ላይ ዳግም ተኩስ ከፈቱ። ህዝቡም ተነስቶ ገጠማቸውና በምሽቱ እንደገና ብዙ ቤቶች ተቃጠሉ።
“በ02/01/09፤ በዚህ ዕለት የሰገን ዞንና የደቡብ ክልል ኮንሶን ለማጥፋት ወሳኝ ምዕራፍ ላይ እንደደረሱ በመተማመን የዞኑን የበላይ አመራሮች ወደ ሀዌሳ ሲያስኮበልሉ የበታች አመራሮችን በምስጢር ቤተሰቦቻቸውን እንዲያስጠነቅቁ መልዕክት አስተላለፉና ቁጥሩን ለመገመት የሚከብድ አጋዚን በመንገድ ላይ ሌላው ህዝብ አይቶ ይሸበራል በማለት መሰለኝ ወታደሩን በሶስት አቅጣጫ ከፋፍለው ግማሹን በፕለን በጅንካ፣ ግማሹን በአርባምንጭ እንዲሁም ግማሹን በያቭሎ በኩል በማስገባት አይሎታን ከበቧት። ከሰዓት በኋላ ከተማ ገለቦ የሚባል የሰገን ዞን አመራር (አሁን አርባምንጭ ኤፍ ኤም ላይ መረጃ እንዲያቀባብል በዞኑ የተቀመጠ) ወደ እፋዮ መንደር ለቤተሰቦቹ ስልክ ደውሎ የዘር ማጥፋት ጭፍጨፋው ዛሬ ማታ ስለምከናወን ሸሽታችሁ አሁኑኑ አካባቢውን ልቀቁ ሲላቸው ዕለቱ የሙስሊም በዓል የሚከበርበት ስለነበር ደግሞ በዓል ባይሆንም መንግስት የገዛ ህዝቡ ላይ እንዲህ ዓይነት Genocide ያውጃል ብሎ ስለማያስብ ውሸቱን ነው ብለው ዝም አሉ።
“ይህን ተከትሎ ነው እንግዲህ ማታ በሞያለ በኩል የገባው የአጋዚ ሃይል በብርብርና ሻራንካ በኩል ገብቶ በጋማ ዳራ ከፍብሎ አንተና ያለበት አካባቢ ህዝቡን ከበው በከባድ መሳሪያ ታግዘው የውትድርና ብቃታቸውን ለማሳየት በቁም ህብረተሰቡ ላይ ተኩስ የከፈቱት። ህዝቡ ፌዴራል ሊያገላግላል እንጅ አይፈጀንም የሚል እምነት ስለነበራቸው ተኩስ አቁመው ቢያፈገፍጉም የአጋዚ የጥይት እሩምታን የሚያቆም አልተገኘም እንዲሁም ወዲያው 6 ሰው ገድለው ሬሳ እንኳን ለመውሰድ በከባድ መሳሪያ የታገዘው የአጋዚ ሃይል ፋታ ስላልሰጣቸው የአንዱን ሬሳ ብቻ እንደምንም ወስደው ካልጠበቁት ጥቃት ሰው ህይወቱን ለማትረፍ እየፈረጠጠ ስለነበር ከዚያ በኋላ የሞቱ ሰዎች ስንት እንደሆኑ እንኳን ከፈጣሪ በቀር ማንም በማያውቀው ሁኔታ ለሊቱን ሙሉ ህዝቡን እየጨፈጨፉ አደሩ።
“03/01/2009፤ ይህ በእንዲህ እንዳለ በሀላኮ በኩል ምንም ተኩስ ሳይሰማ በሰላም ያደረ ህዝብ ጠዋት በማለዳ ከየት በኩል እንደመጡ እንኳን ህዝቡ ሳያውቅ በአርባምንጭ በኩል የገባው የአጋዚ ሃይል የሀላኮን መንደር ከብቦ የጥይት እሩምታ ሲለቁባቸው ከእንቅልፍ ገና በደንብ ያልነቃው ህዝብ ፈዴራሎች ስለሆኑ አይነኩንም ብለው ሲሸሹ አከታትለው በማጥቃት ህዝቡን አሳድደው ከኋላ ባስከተሉት ልዩ ሀይል ቤቶቻቸውን እያቃጠሉ እነሱ ከፊት እያሳደዱ ብታምኑም ባታምኑም አሁን የሀላኮና የጎጫ መንደሮችን ሙሉ በሙሉ አመድ አድርገው መሮጥ ያልቻሉ ህፃናትና አዛውንቶች ጨፍጭፈው ጨርሰዋል ከዛን ወደ ሉልቱ ቀበሌ በመጓዝ ላይ ይገኛሉ።
“አሁን ህዝቡ እንዳለ ሸሽቶ ስለሆነ ከዚህ ድርጊት የሚመልሳቸው ማንም የለም። ከኮንሶ ያለው ህዝብ እንኳን መጥቶ እንዳይከላከል ተዋጊው አጋዚ ከመሆኑ ባሻገር በጅንካ በኩል የገባው ሃይል ከተማውን ከብቦ መንገድ ዘግቷል።
“እንግዲህ ከተጠየቀ ዓመታትን ያስቆጠረው የኮንሶ ህዝብ ሰላማዊ ዴሞክራሲያዊና ህገ መንግስታዊ ራስን በራስ የማስተዳደር ጥያቄ በፅሑፍ ከቀረበ ከዓመት በላይ ዕድሜ ቢሆነውም ዛሬ መልሱ የ ኮንሶን ዘር ከምድረ ገፅ የማጥፋት ዘመቻን በደቡብ ክልልና በአጋዚ ቅንጅት ሆኗል። የሚገርመው ISIS እንኳን ለማጥፋት ዘመቻ ሲደረግ ልክ አለው፤ ዛሬ ግን የኮንሶን ህዝብ በሀገር ጠላት ላይ እንኳን በማይፈፀም የዘር ማጥፋት ዘመቻ ህዝቡን የሚታደግ ከፈጣሪ በቀር ያለ አይመስልም።
“በመጨረሻም ቤተሰቦቼን የጨረሱ አርመኔዎች እኔንም ይምሩኛል የምልበት እምነት የለኝም ከዚህ በኋላ የምኖረው ህይወት የራሴ አይደለም እኔም ዛሬ ሞቻልለሁ። ቢሆንም ግን ይህን በእንባ እየታጠብኩ የፃፍኩትን የምታነቡ ወገኖች ሁሉ በፀሎት ከጎናችን በመሆንና ይህን ግፍ ለዓለም ሚዲያዎች በማሳወቅ እንድትረዱን በነበረኝ ኢትዮጵያዊ ወንድምነት እማፀናችኋለሁ።”
ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡
abahirut says
We real thank world media, which truly reports what is happening on innocent konso nations by SNNPR in Ethiopia.in speakin the truth, konso people have no 3rd parties who obseve and realy report what is realy happening on them. SNNPR Government hides the reality from the outside world,by preparing false reports. but the truth will reveal one day!!! actualy we konso people realy thank those journalsts stand beside of our voice. until now,
no school!!
no healthy center
no salary
no any governmental institution.
multitude daily put in to jail/prison
cruely, mass are hitten by SNNPR soldiers
only little children and females are staying in home.
what can i tell about konso and what can i leave?
ImageMan says
Please give credit to images/photos used, decsribe what the images show and date them etc.. the abc’s of journalisme. But your are more worried about others publishing your story without giveong credit but you yourselves didn’t do that. Abesha stubborness and suspicious nature is typically manifested by you repeatedly ignoring this criticism. Grow up and handle it with maturity – after all you made all these efforts so don’t get childish. Even if you don’t know the details of the image say the web source or unknown source date and place but you still suspicious that anyone that critisize you is a woyane ….
Editor says
ImageMan,
You are criticizing us so many times with some gibberish names stating the same thing again and again. We have said it before and we say it now as well. Known sources are credited as far as pictures or anything. If you know the source, since you don’t have any but regurgitating the same blame and discrediting tactics, if you really mean what you are saying, if you really care about journalism, if you are a real man, stop this nonsense and man up. Publish the sources of the pictures right here in the comments field and we will acknowledge it.
You said, “But your are more worried about others publishing your story without giveong credit but you yourselves didn’t do that” – absolute nonsense! We are not worried about anything – we are just stating the fact. Look around and see how our articles and news are publishing without giving us any credit whatsoever.
“Even if you don’t know the details of the image say the web source or unknown source date and place” – You absolutely have no clue about journalism – may be you know only the word which you even cannot spell it correctly. You want us to give credit for someone just because the picture is published there – what a garbage idea!
“you still suspicious that anyone that critisize you is a woyane” – as you have claimed it so shall it be. The woyanes who are publishing their comments on our webpage will laugh at you for making such an allegation against us.
Here is our final word for you – we have explained it to you here in the comments field and in emails what our stand is. If you come up with the same nonsensical garbage, you will find your comment where it belongs.
Editor
Editor says
Read this comment – who is this replying publicly?
And read this, this and this kind of responses as well – it will give you some lesson explaining the difference between logical criticism and garbage talk.
We are stating this again as we have done it in the past to let the public know.
Editor
abahirut says
oh! i am 100% watching someone’s hand to feed me daily food! in addition I am in ethiopian university attending class, in speaking the truth, idon’t have someone to suport me in order to graduate, still now, i get some help from university supporting club.
i expose the act of SNNPR on konso to the public and apperciates those who stands beside the innocent nations/race of human.
i get this chance because i am in university and uses public computers for posting some realities.
i don’t have my own one/ any machine.
i am sorry , i don’t have any idea to say that……
ImageMa says
Yo! Editor man!,
That summarises it. If you were a news paper editor you will be fired on the spot or your sales figures nose dives all the way to zero.
I don’t know what you don’t understand. You put a picture in a news story – you must have got it from somewhere unless you are ‘create’ the image as you type the store. So it is simple – say where the picture is from, who is in it, when and where it was taken and by who.
The rest of your banter I ignore. If you haven’t got it so far the reason I use none existing emails is to force you, like now, reply publicly here and have no interest corresponding with you.
ImageMan says
Editor,
Don’t hide behind your ‘editorial’ power and selectively filter ImageMan’s comments. Ones ‘garbage’ is another’s truth! Man up and let it be seen and read! On presenting ‘news stories’ to the public you are dictatorial as banda woyanes in refusing public comments! Again Grow up!
Editor says
If what we said doesn’t fit you well, write an article about all you have been saying and also about Golgul and send it out to everyone, including us – we will publish it, provided that it is written following this.
Now, can you just leave us alone, please?
Editor
ImageMan says
Editor Hoy,
Reply to what is said and don’t ask anything else. Are you begging to be left alone? LOL