• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የጃዋር ትልቁ የመጫወቻ ካርድ ተቃጠለ – መቀሌ ለለማ የተጋገረውን ኬክ ኦዴፓ ቆረሰው

December 23, 2019 11:18 pm by Editor 3 Comments

ጃዋር የሬዲዮ ፈቃድ ተከለከለ – አበደንን እያስተዋወቀ ነው

ከአጋሮቹና አቻዎቹ ጋር እኩል ረድፍ ገብቶ ወደ ብልጽግና ፓርቲ ራሱን በመቀየር ለመጪው ምርጫ ዝግጅት እያደረገ የሚገኘውን የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ኦዴፓን ለመሰንጠቅ በፌዴራሊስቶች ስም መቀሌ የተጋገረውን ኬክ የብልጽግና ፓርቲ እንደቆረሰው ተሰማ። ጃዋር መሃመድ አሁን ካሉት ሁለት የቴሌቪዥንና አንድ የሬዲዮ ስርጭት ጣቢያ በተጨማሪ ለመክፈት ያሰበው ሬዲዮ ፈቃድ መከለከሉ ታወቀ።

ራሱን በተገንጣይ ስም እየጠራ “የኢትዮጵያ ጉዳይ ያሳስበኛል” በሚል “የፌደራሊስት ኃይሎች” ብሎ ራሱ የሰየማቸውን ለቃቅሞ መቀሌ ላይ ትህነግ የጋገረውን ኬክ ይቆርሳሉ ተብሎ የታሰበው አቶ ለማ መገርሳ ነበሩ። ለዚሁም ዝግጅት መንደረደሪያ አቶ ለማ በኦሮሚያ ይቋቋማል የተባለውን የኦሮሞ ፓርቲዎች ኅብረት እንዲመሩ ቅድመ ዝግጅቱ ተጠናቆ ነበር። ለዚሁ ይመስላል አቶ ለማ በአሜሪካን ድምጽ የብልጽግናን ፓርቲ እንደማይደግፉና ከሕዝብ ጋር መክረው አቋማቸውን ይፋ እንደሚያደርጉ ይፋ ያደረጉት።

ጃዋር አስቀድሞ የሚያውቀው የአቶ ለማ የቪኦኤ መግለጫ ኤዲት ለማደረግ እንኳን ጊዜ ሳያገኝ “ታፈነ፣ እንዳይተላለፍ ተደረገ” በሚል አየሩን አጣበበ። ይሁን እንጂ የአሜሪካ ድምጽ ዜናውን አመጣጥኖ ይፋ ካደረገው በኋላ እነ ጃዋር የሚመሯቸው የሚዲያ ተቋማት ዜናውን አጡዘው በሎሬት ዶ/ር ዐቢይና አቶ ለማ መገርሳ መካከል ልዩነት መፈጠሩ ኦዲፒን እንደሚፈረካከሰው አስተጋቡ። የትህነግ አራጋቢዎችም ዜናውን ተቀባበሉት። እንደ አንድ ትልቅ ድል አድርገው ወሰዱት። 

አቶ ለማ “ተሰሚነት አጥቻለሁ” በሚል የብልጽግናን ፓርቲ እንደሚሰናበቱ ባሳወቁ ማግስት አሜሪካ ለሥራ ተጓዙ። ጉብኝቱ በአሜሪካና ኢትዮጵያ መካከል በየዓመቱ የሚካሄድ ስብሰባ አካል የነበረ ቢሆንም ለአቶ ለማ ግን ከዚህ በፊት ለሌሎች ተደርጎ በማያውቅ ሁኔታ ከአንድ መሪ የማይተናነስ አቀባበል ተደረገላቸው።

ሆኖም አቶ ለማ ለቪኦኤ ሰጡ የተባለው ቃለምልልስ ከተሰማ በኋላ ኦዲፒ ልዩነት መኖሩ የዴሞክራሲው ማሳያ አንዱ ገጽታ መሆኑንን፤ ይህ አካሄድ ከዚህ ቀደም ትህነግ ይነዳው በነበረው ኢህአዴግ ውስጥ እንደማይታሰብ በማስታወቅ የተለሳለሰ መልስ በመስጠት ነባር አመራሮቹን ለፖለቲካ ሥራ አሰማራ። 

ሶስት መቶ ስልሳ ዲግሪ ዞሮ በውል በማይታወቅ ዓላማ፣ አንድ እግራቸው ከመንግሥት ጋር በሆኑ ሃብታም ግንበኛችና የቀድሞ ከፍተኛ ባለሥልጣን የሚደጎመው የእነ ኤርሚያስ፣ ሃብታሙና ርዕዮት ዓለሙ ዩትዩብ ከትህነግ ፍልፍል ሚዲያዎች ባልተናነሰ የተከሰተው ልዩነት ብልጽግናን እንደሚበላው በእርግጠኝነት አወጁ።

እሁድ ዕለት ኦዴፓ ይፋ ያደረገው ዜና እንዳስታወቀው አቶ ለማ መገርሳ እንዲቆርሱት የተዘጋጀው ኬክ ተቆርሷል። ድርጅቱን ገልጾ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደዘገበው አቶ ለማ መገርሳ ከብልጽግና ፓርቲ ጋር አብረው ለመሥራት ቃላቸውን አድሰዋል።

አባ ገዳዎችና በአቶ አባ ዱላ የሚመራው የድርጅቱ የቀድሞ አመራሮች በብልጽግና ፓርቲና በአቶ ለማ መካከል ያለውን ልዩነት በመሸምገል ስምምነት ማወረዳቸው ይፋ ሆኗል። ልዩነቱን ሲያጦዝ የነበረው ጃዋር መሐመድ የሚያስተዳድራቸው የሚዲያ ተቋማት ስምምነቱን አስመልክቶ ይህ እስከታተመ ድረስ ያሉት ነገር የለም። ዛፍ ለምን ውሃ ጠጣ፣ ከተማ ለመን ጸዳ፣ ሰብል ለምን ታጨደ፣ … እያሉ የሚነተከተኩት የትህነግ ጭፍራ ሚዲያና ሎሌውችም ያሉት ነገር የለም። የሚሉት ይጠፋቸዋል ተብሎ ግን አይጠበቅም።

የአቶ ለማና የዶ/ር ዐቢይ ተስማምቶ ለመሥራት መወሰናቸው እንዳስደሰታቸው ብዙዎች ስሜታቸውን በስፋት በማኅበራዊ ገጾች እየገለጹ ነው። አቶ ለማም በቅርቡ ሰፊ መግለጫ እንደሚሰጡ ይጠበቃል። ዜናው ግን ጃዋር ኦዴፓን ለመናድ በየተራ ሊጠቀምባቸው ካሰባቸው የሤራ ካርዶች መካከል አንዱ እንደተቃጠለ የሚይሳይ መሆኑንን ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ ተናግረዋል።

በሌላ ዜና ጃዋር አዲስ የሬዲዮ ስርጭት ለመክፈት ያቀረበውን ጥያቄ የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን እንዳገደው የጎልጉል የአዲስ አበባ ምንጮች አመልክተዋል። የዜናው አቀባዮች እንዳሉት ጃዋር ያቀረበው ጥያቄ ለምን እንደታገደ ምንጮቹ በዝርዝር ማሳወቅ አልፈለጉም። ቀደም ባሉት ወራቶች ጃዋር ለኦኤምኤን መንግሥት የሃምሳ ሚሊዮን ብር ድጎማ እንዲሰጥ ያቀረበው ጥያቄ ውድቅ መደረጉ የሚታወስ ነው።

የአቶ ለማን መመለስ አስመልክቶ ኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት የሚከተለውን ዘግቧል፤ 

አቶ ለማ መገርሳ በመደመር ፍልስፍናና በፓርቲዎች ውህደት ላይ የነበረቸውን ልዩነት አጥብበው የሕዝቡን ትግል ወደ ቀጣይ ምዕራፍ ለማሻገር መስማማታቸው ተገለጸ።

አቶ ለማ መገርሳ ከዚህ ቀደም በመደመር ፍልስፍናና በፓርቲዎች ውህደት ላይ ያላቸውን ልዩነት በኦሮሞ ባህል መሠረት ስምምነት ከተደረገ በኋላ ልዩነታቸውን አጥበው ከዚህ በኋላ በጠንካራ አንድነት በጋራ በመስራት የህዝቡን ድል ወደ አዲስ ምዕራፍ ለማሸጋገር ከስምምነት ተደርሷል።

ይህ ስምምነት የተደረሰው የቀድሞ የODP ስራ አስፈጻሚዎችና ነባር አመራሮች በጋራ ባደረጉት ውይይት ነው።

ፓርቲው የዴሞክራሲ ሥርዓትንና በኦሮሞ ባህል መሠረት ውስጣዊ ችግሩን እና የሕዝቡን ጥያቄ ለመመለስ ጠንክሮ እንደሚሠራ ተገልጿል።

በፖለቲካ ሂደት ውስጥ በተለይ ደግሞ ሪፎርም በሚደረግበት ወቅት የሀሳብ ልዩነቶች መኖራቸው የተለመደ መሆኑ ነው የተጠቆመው።

የሀሳብ ልዩነት መኖር በራሱ ችግር እንዳልሆነ የተገለጸ ሲሆን፣ ትልቁ ነገር የሀሳብ ልዩነትን በዴሞክራሲያዊ መንገድ ለመፍታት ዝግጁ መሆን ነው መባሉን ከኦሮሚያ ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

ጎልጉል ከአንድ የኦዲፒ አባል ያገኘው መረጃ እንደሚጠቁመው የመደመር ርዕዮትም ሆነ የብልጽግና መመሪያ ከቀድሞው ጠርናፊ የኢህአዴግ አሠራር፣ ከዴሞክራሲያዊ ማዕከላዊነትም ሆነ አብዮታዊ ዴሞክራሲ ፍጹም የተለየ መሆኑ መናገራቸውን ነው። አመራር አባሉ እንዳሉት አቶ ለማ በቪኦኤ የተናገሩት የሃሳብ ልዩነት ለአገራችን ጠላቶችና አፍራሽ ሃሳብ አራማጆች የሚዲያ ፍጆታ የዋለውና አንዳዶችም የተቀበሉት በፓርቲያችን ውስጥ እየጀመርን ያለነውን ግልጽ አሠራር ካለመረዳታቸው የተነሳ ነው። በሁለቱ ጓዶቻችን መካከል የተካሄደው ዕርቅና የአቶ ለማ በብልጽግና መቀጠል ለእኛ ያልተጠበቀ ባይሆንም አገር እናድናለን እያሉ አገራችንን እየበጠበጡ ላሉትና ከእነርሱ ጋር ባልተቀደሰ ፍቅር ውስጥ ለሚገኙት ትልቅ መርዶ እንደሆነባቸው ለማወቅ ችለናል በማለት አመራር አባሉ ሃሳባቸውን ሰጥተዋል።    


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Politics Tagged With: Full Width Top, jawar, jawar massacre, Middle Column, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. wabi-birat says

    December 25, 2019 04:00 pm at 4:00 pm

    ጎልጉል

    1) እስቲ ይህቺን አንቀፃችሁን እንደገና አንብቧት
    “ሶስት መቶ ስልሳ ዲግሪ ዞሮ በውል በማይታወቅ ዓላማ፣ አንድ እግራቸው ከመንግሥት ጋር በሆኑ ሃብታም ግንበኛችና የቀድሞ ከፍተኛ ባለሥልጣን የሚደጎመው የእነ ኤርሚያስ፣ ሃብታሙና ርዕዮት ዓለሙ ዩትዩብ ከትህነግ ፍልፍል ሚዲያዎች ባልተናነሰ የተከሰተው ልዩነት ብልጽግናን እንደሚበላው በእርግጠኝነት አወጁ።”
    እንደ የእናንተን “ዜና” ለማስረገጥ ያልተረጋገጠ፤ ማስረጃ የሌለው ተራ የስም ማጥፋት ውንጀላ?

    2) ከየት የመጣ አማርኛ ነው “ኬክ መቁረስ”? ነው ተገቢ የአማርኛ አገላለጽ ጠፍቶ ነው?

    3) ይህችስ አገላለፅ
    “በሌላ ዜና ጃዋር አዲስ የሬዲዮ ስርጭት ለመክፈት ያቀረበውን ጥያቄ የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን እንዳገደው የጎልጉል የአዲስ አበባ ምንጮች አመልክተዋል። የዜናው አቀባዮች እንዳሉት ጃዋር . . ”
    ይሄ ጓደኛና ዘመድ ጋ እየደወልን የምናገኘውን ወሬ ነው የጎልጉል “የአዲስ አበባ ምንጮች የምትሉት?” ነው የዜና መረብና የዜና አቀባይ አላችሁ?

    4) ይህስ “የአቶ ለማን መመለስ አስመልክቶ ኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት የሚከተለውን ዘግቧል፤ ”
    ዋሾውና የመንግሥት ፕሮፓጋንዳ መንዣው “ኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት”ን ዋቢ አደረጋችሁ?

    ጎልጉል በየ”ዜና”ችሁ እንደሚታየው ተደምራችኋል፤ ረጋ በሉ እባካችሁ! ትችቴም ለእናንተው መሻሻል ነው እና ቡራ ከረዩ እትበሉ፤

    Reply
  2. Tom says

    December 26, 2019 08:55 am at 8:55 am

    Every thing is a dramatic game.The Synagogue is striving to save its established system in Etiiopia.Read http://www.antichristconspiracy.com http://www.realjewnews.com

    Reply
  3. Tesfa says

    December 27, 2019 10:20 pm at 10:20 pm

    Ethiopia badly needs rule of law now. Justice for the innocent massacred Ethiopians because Jawar Mohamed. There is ample evidence in our had regarding J.M Truth be told, he need to beheld put behind the bar for his crime, than his talk of running for an office.

    Many Oromos are now awakened to the fact J.M is about one thing and one thing only.He wants to carve his own plate,if he can as he is a hired gun for Alsisi.Please listen to the following message by Dr.Chala of Harvard University.

    1-https://www.youtube.com/watch?v=FhzHpY12siY

    2-https://www.youtube.com/watch?v=bcAVuqK9LbM

    Reply

Leave a Reply to wabi-birat Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በሆሩ ጉዱሩ ወለጋ ዞን የጉደኔ ጫላ ሲበሬ ቀበሌ ነዋሪዎች በኦነግ ሸኔ ላይ ጀብዱ ፈፀሙ August 11, 2022 03:04 pm
  • በኢትዮጵያ ግብርና ላይ ግብጽ ለዓመታት የፈጸመችው ሤራ August 10, 2022 10:58 am
  • የስሪ ላንካው “FamilyCracy” – ከመዓቱ እስከ ተውኔቱ August 8, 2022 09:45 am
  • “አበበ እንጂ መቼ ሞተ!”          July 19, 2022 04:57 pm
  • ሸኔ አመራሮቹንና ጠንካራ ይዞታዎቹን እያጣ ነው July 19, 2022 01:55 am
  • የወልቃይት አማራ የተሰቃየባቸው የትህነግ 15 ድብቅ እስር ቤቶች! July 18, 2022 03:13 pm
  • ገቢ የማያስገኙ የዜና ርዕሶች July 17, 2022 05:36 pm
  • “ዛሬ ‘ኃያል ነን’ የሚሉ ሀገራት ኢትዮጵያ ላይ በሚዲያ /በመረጃ/፣ በዲፕሎማሲ፣ በሳይበር እና በተልእኮ የተቀነባበረ ‘ግራጫ ጦርነት’ እያካሄዱባት ነው” ጠ/ሚ ዐቢይ July 7, 2022 10:03 am
  • የኦሮሞ ልሂቃንና ፖለቲከኞች በአማራ ተወላጆች ላይ እየደረሰ ያለውን “የዘር ማጥፋት” ወንጀል እንዲያወግዙት አብን ጠየቀ July 6, 2022 01:38 pm
  • “አማራን ኦሮሚያ ውስጥ የመግደል እና የመጨፍጨፍ እቅድ የኦነግ ሳይሆን የኦሮሚያ ብልጽግና ነው” አቶ ሃንጋሳ July 6, 2022 01:53 am
  • “በኢትዮጵያዊያን የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ በመግባት ሀገሪቱን ማተራመስ አለብን” አይማን አብድልአዚዝ ግብጻዊው ፖለቲከኛ July 5, 2022 12:57 pm
  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule