• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ኢትዮጵያውያን መሆናቸውን ለማረጋገጥ እንሞክራለን”

April 20, 2015 09:00 am by Editor 5 Comments

እንደ ሚዲያ ወይም እንደ ጋዜጠኛ ሳይሆን እንደ ሰብዓዊ ፍጡር ይህን እንጽፋለን፡፡ እንደ ክርስቲያን ወይም እንደ ሙስሊም ሳይሆን እንደ አንድ ሰው ይህን እንናገራለን፡፡

ሰብዓዊነት ከሙያ በላይ ነው፡፡ ሰብዓዊነት ከሃይማኖት በላይ ነው፡፡ ሰብዓዊነት ከዘር በላይ ነው፡፡ ሰብዓዊነት ከምን ዓይነት መጠሪያ በላይ ነው፡፡

በሊቢያ የሚገኘው የአይሲስ ተወካይ ቡድን 30 ኢትዮጵያውያንን አረደ፤ በጥይት ረሸነ፡፡ የዓለም ዜና ማሰራጫዎች ዘገባውን አቀረቡ፤ ኢትዮጵያውያን መታረዳቸውን አወጁ፤ ዓለም ቪዲዮውን ተመለከተው፤ ዜናውን አነበበው፡፡ እኛም በሃዘንና በእንባ አንብበነዋል፤ ተመልክተነዋል፤ (ፎቶም ሆነ ቪዲዮውን እዚህ ላይ አንለጥፍም)፡፡

ኋይት ሃውስ እንኳን መግለጫ ሰጠ፤ ድርጊቱን ኮነነ፤ ከሰብዓዊነት በታች፤ ዘግናኝ፣ ፍጹም አረመኔያዊ፣ ጨካኝና ስሜት አልባ በማለት አወገዘው፡፡ ኢትዮጵያውያኑ የተገደሉት በሃይማኖታቸው ምክንያት መሆኑን በግልጽ ተናገረ፤ ሆኖም ይህ የአሸባሪዎች ድርጊት የእምነት ተከታዮችን በአንድነት አሸባሪነትን እንዲታገሉ የሚያስተባብራቸው ሊሆን ይገባል በማለት በሃይማኖቶች መካከል ተጨማሪ ግጭትና መከፋፈል እንዳይፈጠር አሳሰበ፡፡

የመስቀል ማተብ ያሰሩ መልካቸው፣ ገጽታቸው፣ ሁለንተናቸው አበሻ መሆናቸውን በሚመሰክረው የ29 ድቂቃ ቪዲዮ ኢትዮጵያውያን ለዕርድ ሲሰለፉ፤ ለጥይት ሲማገዱ ተመልክተናል፡፡ ጎልጉል በቀጥታ ከቤተሰብ ማጣራት ባይችልም ባገኘው መረጃ መሠረት በቪዲዮው ላይ ወንድሟን የተመለከተች አትዮጵያዊት መኖሯን መረጃ ደርሶናል፡፡ ጥልቅ ሃዘናችንን ለወገኖቻችን እንገልጻለን፡፡ ይህ የሃይማኖት ጉዳይ አይደለም ሰብዓዊነት እንጂ!

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ የአይሲስ ተግባር እስልምናን ይወክላል ብሎ አያምንም፡፡ እስልምና ወይም ኢስላም ማለት “ለአላህ ሱብሃነሁ ወተዓላ ትዕዛዝ ሙሉ ለሙሉ እጅ መስጠት” መሆኑን እንዲሁም ሌላው ትርጉሙ “ሰላም ማለት” መሆኑን ሃይማኖቱ በሚያስተምረው ትምህርት መሠረት ይቀበላል። ጽንፈኝነትና አክራሪነት በሁሉም ሃይማኖት ውስጥ የሚንጸባረቅና ከራስ ቅድስና የሚመጣ የተሳሳተ አመለካከት እንደሆነ ጎልጉል ያምናል፡፡

ስለዚህ ይህ የአይሲስ ተግባር የእስልምና ተግባር ተደርጎ መወሰድ የለበትም፤ ይህም ድርጊት ለዘመናት በክፉም በደጉም ተቻችሎና ተከባብሮ የኖረውን የኢትዮጵያን ሕዝብ ሊለያየው አይገባም፡፡ እዚህ ላይ አስተያየት የምትሰጡም ሁሉ በዚህ የተሳሳተና ሁሉን በጭፍን በሚያወግዝ መንፈስ አስተያየት እንዳትሰጡ ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

በህወሃት የሚመራው ኢህአዴግ በእሁድ ምሽት ዜናው ላይ በጣም ተዝናንቶ ጉዳዩን እንደ አንድ ተራ ዜና ከረጅሙ የዜና እወጃው ሰዓት ውስጥ ጥቂት ደቂቃዎችን ሰጥቶታል፡፡ ያውም የቀደመው ሌላ ዜና አለ – “የልማት ዜና!”

በዚህ ብቻ አላበቃም፤ ዜናውን እንደ ሁላችንም በዓለም የዜና ማሰራጫዎች መስማቱን ተናገረ፤ የኢህአዴግ አፈቀላጤ ሬድዋን ኢትዮጵያውያን መሆናቸውን ለማረጋገጥ እንሞክራለን አለ፡፡ ሃይለማርያም ደሳለኝ የተናገረው ነገር የለም፤ የዜናው ቀዳሚ የሆነው ሙላቱ ተሾመ ያለው ነገር የለም፡፡ “የፌስቡኩ ፍንዳታ” ቴድሮስ አድሃኖም አይሲስን ደውሎ ለመጠየቅ ያሰበ ይመስል “ድርጊቱን እያጣራነው ነው” ብሏል፡፡ ከጥቂት ቀናት በፊት በለቀቀው መልዕክት “ወያኔ ነኝ” ብሎ ነበር፡፡ እውነተኛ “ወያኔ ነው”! የህወሃትና ኢህአዴግ ደጋፊዎችና አሽቃባጮች “ታዲያ ምን ማለት ነበረበት?” ብላችሁ ባትጠይቁ መልካም ነው፡፡

ዜጎቻቸው በአይሲስ የተገደሉባቸው አገራት የአይሲስን ምሽጎች ደብድበዋል፤ በተገደሉባቸው ዜጎች ልክ ወይም የበለጠ ጥቃት በአይሲስ ላይ አድርሰዋል፡፡ የሞቱባቸውን ዜጎች ህይወት ለመመለስ ባይችሉም የዜጋቸውን ጥቃት የሚከላከል መንግሥት መኖሩን አስመስክረዋል፡፡ ባለቤትና መሪ የሌላት ኢትዮጵያስ? ሳይጠሩት አቤት ብሎ ሶማሊያን ያተራመሰው በህወሃት የሚመራው ኢህአዴግስ ምን ሊያደርግ ነው ያሰበው? ሃይለማርያም፣ ሙላቱ፣ ሬድዋን፣ ቴድሮስ፣ በረከት፣ አባይ፣ . . . ወያኔዎች ሁላችሁም አይሲስ የገደላቸው “ኢትዮጵያውያን መሆናቸውን አጣርታችሁ” ስታበቁ ምን ልታደርጉ ነው ያሰባችሁት? “ቦንድ ልትሰበስቡ” ወይስ “ኢህአዴግን ምረጡ” ዘመቻችሁን ልትቀጥሉ? የፈለጋችሁትን ልታደርጉ ትችላላችሁ፡፡ የሃዘን ቀን ልታውጁ ትችላላችሁ፤ ዲስኩር ልትነፉም ትችላላችሁ፤ ባንዲራ የምትሉትን “ጨርቅ” ዝቅ አድርጋችሁ ልታውለበልቡ ትችላላችሁ፤ … የምታደርጉት ነገር በሙሉ ግን በቁም ያለነውን እንደ አይሲስ ካረዳችሁን በኋላ የምታደርጉት በመሆኑ እንደ ምንም አንቆጥረውም፡፡ በጣም ዘግይታችኋል፡፡ ምክንያቱም ሃዘናችሁንና የሃዘን መግለጫችሁን ሳንሰማ እኛ ሞተናል፤ ታርደናል፡፡

ስለዚህ እንደ ቴድሮስ አድሃኖም “ወያኔ ነን” የምትሉ፣ የወያኔ ደጋፊዎች፣ ካድሬዎች፣ ተላላኪዎች፣ የጥቅም ተጋሪዎችና ልክስክሶች ስሉሱ እስኪዞርባችሁ “መጪው ጊዜ ከኢህአዴግ ጋር ብሩህ ነው፤ ሥራ ላይ ነን” ማለታችሁን ቀጥሉ፡፡

ከላይ እንዳልነው እንደ ሚዲያ ወይም እንደ ጋዜጠኛ ሳይሆን ሰብዓዊ ፍጡር ነው ይህን የምንጽፈውና እኛም በፈጣሪ እናምናለን፡፡ ፍርድን የሚሰጥ ቅን ፈራጅ፤ ሁሉንም የሚመለከት፤ የሚመረምር፤ ዕንባን የሚያብስ፤ የበቀል በትሩን ከዘረጋ የማይመለስ ፈጣሪ አለ፡፡ ፕ/ር መስፍን እንዳሉት “የኢትዮጵያ ደሀዎች እንባ የእግዚአብሔርን ሰማይ አጨቀየው”፤ እንባ ብቻ አይደለም ደምም ተጨምሯል፡፡ እጅግ ርኅሩህ፣ እጅግ መሃሪ የሆነው ፈጣሪ ጊዜ የተሰጣችሁ “ህዳሴ፣ ውዳሴ፣ …” እያላችሁ ከበሮ እየደለቃችሁ እንድትዘፍኑ ሳይሆን ወደ ኅሊናችሁ እንድትመለሱ ነው፡፡

አበቃን!!


ይህ የ“ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ®” አቋም ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Editorial Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Bombu says

    April 20, 2015 07:09 pm at 7:09 pm

    እጅ እንዳሰጥ

    እናጣራ በሚል ፈሊጥ
    በዜጋ ሞት በመለጠጥ
    የሚኩራሩ ገዢዎችህ
    ፍርዳቸውን እንዲያሳይህ
    ቀኑ ይድረስ ይብቃ በለን
    በፈጣሪ እምነት አለን»

    እንዲያበቃ መዋከቡ
    በጨካኞች መከበቡ
    ብቻ ታገል እጅ እንዳሰጥ
    በፈቃድህ መሪ እስክትመርጥ

    ከዛች ምድር ከአገሩ
    እድል ሆኖ መፈጠሩ
    ወይ ወገኔ ያገሬ ስው
    ሞት ባንተ ለይ ሰንቴ ይቅናው

    እንዲያበቃ መዋከቡ
    በጨካኞች መከበቡ
    ብቻ ታገል እጅ እንዳሰጥ
    በፈቃድህ መሪ እስክትመርጥ

    አዎ እንደሰው ሰባዊነት
    መቆጠሩ እንደ ፍጥረት
    አነሰብህ ባሁን ጊዜ
    ሕልውናህ ሆነ አባዜ

    ባገሩ ላይ ሰርቶ አዳሪ
    መሆን ቀርቶ ቀን ቆጥሪ
    ጣርና ሞት እንደጥላ
    ሲከተልህ ቀን ላይ ላይሞላ

    እንዲያበቃ መዋከቡ
    በጨካኞች መከበቡ
    ብቻ ታገል እጅ እንዳሰጥ
    በፈቃድህ መሪ እስክትመርጥ

    ባገሩ ላይ በሁካታ
    በሕግ ፊት ፍትሕ ጥፍታ
    በትርምስ በግርግር
    ቢቸግረው ሰርቶ ማደር
    ምርጫው ሆነ መበታተን
    ለጠላቶች ሲሳይ መሆን

    እንዲያበቃ መዋከቡ
    በጨካኞች መከበቡ
    ብቻ ታገል እጅ እንዳሰጥ
    በፈቃድህ መሪ እስክትመርጥ

    አቆራርጦ ዘሎ ድንበር
    እግሬ አውጪኝ የትም መብረር
    ወዶ ገባ ለጠላቱ
    እስኪመስል የሰው ከንቱ

    እንዲያበቃ መዋከቡ
    በጨካኞች መከበቡ
    ብቻ ታገል እጅ እንዳሰጥ
    በፈቃድህ መሪ እስክትመርጥ

    ውድ ጎልጉሎች ጥሩ ፅሁፍ ነው ያቀረባችሁት› ለዚች አጭር ግጥም ተስማሚ ነው ያላችሁትን አርዕሥት የመስጠት መብት ሰጥቻለሁ »

    Reply
    • Editor says

      April 21, 2015 04:31 am at 4:31 am

      የዘወትር ተሳታፊያችን Bombu

      ለላኩልን ግጥም ከልብ እናመሰግናለን – “እጅ እንዳሰጥ” ብለን ርዕስ ሰጥተነዋል:; እርስዎም የሚስማሙ ይመስለናል::

      ከአክብሮት ምስጋና ጋር

      አርታኢ/Editor
      ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ/Golgul: the Internet Newspaper
      http://www.goolgule.com
      editor@goolgule.com

      Reply
  2. Mulugeta says

    April 20, 2015 07:49 pm at 7:49 pm

    Do you call yourself journalist ? I don’t think so but you can be activist,shame yourself.

    Reply
  3. wuroye says

    April 21, 2015 03:29 pm at 3:29 pm

    Woyane masterminded and spent millions of dollars to kidnap Andy the giant in the name of terrorism. They imprison and torture journalists who chose to exercise their God-given freedom of expression. When an actual terror hits our fellow citizens in Yemen, South Africa & Libya, these thugs played chicken. TPLF’s full-time job is espionage on Ethiopians, they don’t have any foreign policy. It is embarrassing to have theselunatics in the shoe of Menilik and Haile Selassie Who won a lot of respect around the world. It is a shame.

    Reply
  4. Daniel G/ says

    April 22, 2015 12:11 am at 12:11 am

    መሞት መተኛት ማንቀላፋት
    እስከመቼም ባለመንቃት
    የእኛ የአፍሪካዊያን ዕድል ከሆነ ዘመን ተቆጥሯል ፡ስለዚህ ዝም ብለን እንተኛ የምንተኛው እንቅልፍ ግን የማይጠገብ ዕንቅልፍ ነው
    ሞትንም ቢሆን ዝም ብለን እንሙት የምንሞተው ሞት ግን እንደእስካሁኑ የውርደት ሞት ነው፡፡፡
    ምክንያቱም አህጉራችን የሕዝብ ብዛት እንጂ ከቶም ሰው የላትምና ፡ የታደልነውም ሆድ እጂ ልብ አደለም ስለዚህ ማሰብና ማመዛዘን ተሳነን
    የእንቅልፍና የሞት ምንጭ የሆኑትን ተጋፍጦ ጦሩን ከጦሩ ተጋትሮ ወግቶ ድል መምታት እስኪነቀል ከስሩ የአንድ ሕዝብ አላማ መሆንነበረበት

    መቼ? እንዴት?ኬት ?ወዴት?

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule