• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የተዘቀዘቀ መስቀል?!

January 23, 2024 11:43 pm by Editor 1 Comment

“አርቲስት ቴዲ አፍሮ የጥምቀት በዓልን ወደ አደባባይ ወጥቶ ማክበሩን የሚያሳይ ፎቶ ተለቋል” ሲሉ ነው በርካቶች ባሰራጩት አስተያየት “ነገሩ ምንድን ነው?” ሲሉ ግራ በመጋባት ማብራሪያ የጠየቁ ቢበዙም፣ ሌሎች ተመሳሳይ ድርጊት ፈጽመው የነበሩ አካላት ላይ ውግዘት መድረሱን ያስታወሱም አልታጡም።

የሚያደርገውን በማወቅ፣ ጊዜና ሰዓት በማስላት በሚያከናውናቸው ተግባሮቹ ስኬት የለኩት “ቴዲ ሳያውቅ ይህን ለበሰ ለማለት ያስቸግራል” ሲሉም ተድምጠዋል።

የዲዛይን ችሎታ አካታ እንዳያዘች የሚነገርላት ባለቤቱ አምለሰት ሙጬ በጥንቃቄ እንደምትሞሽረው የሚያውቁ “ይህን እንደ ስህተት መቀበል ያዳግታል” ሲሉ አስቸኳይ ማብራሪያ እንደሚሹ አመልክተዋል።

ፎቶውን በማጋራት ሰፋ ያለ አስተያት ከጻፉት መካከል ቶማስ ጃጃው በቴሌግራም ገጹ “እንደ ማንኛውም በብርሃነ ጥምቀቱ እንደሚያምን ክርስቲያን በዓሉን በማክበሩ ከማንም በላይ የበዓሉ በረከት ተካፋይ የሚያደርገው ደስተኛው ራሱ የሚሆን መሆኑ ቢታወቅም፣ በሙዚቃው ዓለም ተፅዕኖ ፈጣሪ ከሆኑት አርቲስቶች አንዱ እንደመሆኑ የጥምቀት በዓልን በአደባባይ ተገኝቶ ታቦታቱን በእልልታ በጭብጨባና በዝማሬ እያጀቡ ከሸኙት ታዋቂ ሰዎች መካከል እንደመታየቱ የእሱ አድናቂ የእምነቱ ተከታይ የሆኑ ብዙዎችን እንደተለመደው ሊያስደስት የመቻሉ ጉዳይ አያጠራጥርም” ሲል አስተያየቱን በጥቅል እውነት ይጀምራል።

ያክልና “በእውነቱ እኔም ጥምቀትን ከሕዝበ ክርስቲያኑ ጋር ተገኝቶ ማክበር በመቻሉ ጊዜውን በመልካም ቦታ አሳልፏል ብዬ አምናለሁና ደስ ይለኛል። ነገር ግን ቴዲ አፍሮ ለጥምቀት በዓል ለብሶት የወጣው ልብስ ላይ የመስቀል ምልክቱ የተዘቀዘቀ በመሆኑ ጥምቀትን ሲያከብር ተመልክቶ ደስ ይላል ያለ የእምነቱ ተከታይ የእሱ አድናቂዎች ጭምር እንኳን ቢሆን የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይና በጥምቀት በዓል ላይ ለብሶት የታየ ስለሆነ ብለው ጉዳዩን በቀላሉ ሊመለከቱት ይችላሉ ብዬ መደምደም አይቻለኝም” ብሎ መከራከሪያውን ያቀርባል።

“በተዘቀዘቀው መስቀል ግራ የሚጋቡበትና ሊቆጡበት የሚችሉ የእምነቱ ተከታዮች ሊኖሩ እንደሚችሉ ነው የማስበው” የሚል ፍርድ የሰጠው ቶማስ፣ ሲያስረዳ “ምክንያቱም የቴዲ አፍሮ አድናቂ የሆኑት የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሀይማኖት ተከታዮች ‘መስቀል ሃይላችን ነው፣ መስቀል ቤዛችን ነው’ የሚሉ ከመሆናቸው በተጨማሪ፣ ከዚህ በፊት የመስቀል ምልክቱን እንደ ቴዲ አፍሮ ዘቅዝቆ ለበሰ የተባለ ሰውን አንዴ ‘666’ ሌላ ጊዜ ‘ደግሞ ፀረ-ኦርቶዶክስ’ የሚል ዘመቻ ተከፍቶበት እንደነበር የሚታወቅ ነውና”

የቶማስ አመላካችና ንፅፅራዊ አስተያየት የሙግት ሃሳቡን ሲያጸና “እርግጥ ነው ቴዲ አፍሮ የተዘቀዘቀ የመስቀል ምልክት ያለበትን ልብስ ራሱ ያሰራው፣ ሱቅ ላይ የገዛው፣ ወይም በስጦታ የተሰጠው፣ የመስቀሉን ሁኔታ ያላስተዋለው ጉዳይ ነው ሊባል ይችል ይሆናል” የሚል ግምት ያስቀድምና “የታዋቂ ለዛውም እንደ ቴዲ አፍሮ ላሉት ለአለባበሳቸው፣ ለአነጋገራቸውና ለአረማመዳቸው ከፍተኛ ትኩረት ይሰጣሉ፤ ነገሮችን በጥንቃቄ ይከታተላሉ ተብሎ የሚነገርላቸው ሰዎች ሺዎች በሚሰበሰቡበትና በሚገኙበት በጥምቀት ለሚለበስ ልብስ ልዩ ትኩረት በሚሰጥበት አደባባይ የተዘቀዘቀ መስቀል ያለበት ልብስ ያለማስተዋል የተለበሰ አድርጎ ለመቁጠር እንዴት እንደሚቻል አላውቅም” በሚል ድርጊቱ ሆን ብሎ የተደረገ የሚመስልበትን ማሳያ ያመላክታል።

“የመስቀሉ መዘቅዘቅ ችግር የለበትም ከተባለ” ይላል ጸሃፊው “ከዚህ ቀደም መስቀል ዘቅዝቀው ለብሰዋል በሚል የተሰጡ ትርጉሞች የተደረጉ ውግዘቶች ዋጋ ያጣሉ እንደማለት ይሆናል” ሲል ቴዲ አፍሮን ለእይታና ለግምገማ አንገዋሎ አቅርቦታል።

ጉዳዩ ውሎ አድሮ የሚያስነሳውና የሚከተለው አስተያየት ምን እንደሚሆን ከወዲሁ መገመት ቢያስቸግርም፣ “በጥቁር ልበሱ” ዘመቻ ወቅት የመሪነቱን ተግባር ከሚወጡ አስተባባሪዎች መካከል አንዷ የሆነችው ባለቤቱ አምለሰት ሙጬ “ነገሩን ታቃናዋለች” የሚል አስተያየት የሰጡ ጥቂቶች ታይተዋል። ይህ እስከተባለ ድረስ ቴድሮስ ካሳሁን በግሉ ያለው ነገር የለም። (ኢትዮ12)

ከዚህ በፊት የተዘቀዘቀ መስቀል ለበሰ በሚል ከፍተኛ ተቃውሞ ተሰነዘረበት ዮናታን አክሊሉ ተሰፍቶ የተሰጠውና ሳያስተውል ማድረጉን በማመን ይቅርታ መጠየቁ ይታወሳል። ለቅድስት ቤተክርስቲያን፣ ለምዕመናን፣ ለአድናቂዎቹ ከሁሉም በላይ ለመስቀሉ ክብር ሲል ይህንን መሰል ምላሽ ከቴዲ አፍሮ ባለመሰማቱ ያሳዘናቸው በየማኅበራዊ ሚዲያ ቀሬታቸውን ሲያሰሙ ተስተውለዋል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Right Column, Social Tagged With: Inverted Cross, teddy afro, Yonatan Aklilu

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    February 5, 2024 12:41 pm at 12:41 pm

    አይ ሃበሻ ነገር ስንቆረጥም ጥርሳችን አለቀ። ተዘቀዘቀ አልተዘቀዘቀ መስቀሉ እኮ ለሚያምኑት እንጂ ላላመነው ምንም ትርጉም የለውም። ግን ያለ እኛ ሃይማኖት መንግስተ ሰማያት መግቢያ የለም የሚሉ ወስላቶች በሞሉበት ምድር ይህ ወሬ ተብሎ መወራቱ የቱን ያህል እምነቱ እንደተጣረሰ ያሳያል። ሲጀመር ሃይማኖት የማዘናጊያና ሰውን የመጨቆኛ መሳሪያ ነው። ጥቂት ብልጦች መስቀልና መጽሃፍ ቅድስ እያሳዪ የስንቱን ቤት እንዳራቆቱ፤ የስንቱን ሃገር እንዳፈረሱ ታሪክ ዘግቦ የያዘው ጉዳይ ነው። በተለይ ደግሞ አሁን በዘርና በቋንቋ ተከፍላ በክልል የተተለተለችው ሃገራችን በእነዚህ ጠምባራ ፓለቲከኞች የተነሳ በቋንቋዬ ካልተቀደሰ ወይም ካልተሰበከ አልሰማም በማለት በሃገርና በውጭ ሰውን ሲያዋክቡና የተለመደውን እሬት ፓለቲካቸውን በሃይማኖት ስም ሲያስፋፉ ማየት ያማል።
    እውነተኛ ሃይማኖት የሰዎችን እንበለ ፍርድ አይቶና ሰምቶ ይሟገታል። በመንግስትም ሆነ በሌሎች ታጣቂዎች እጅ ለሚደርስባቸው በደል ድምጽ ይሆናል። ካለው ያካፍላል። ሳይኖረው በሃሳብና በምክር ይረዳል። ዝም ብሎ የእምነት ጠበቃ ለመሆን ያለ የሌለውን ወሬ እየነዙ ሰውና ሰውን ህዝብና ህዝብን የሚያጋጩ የእምነት ሰዎች ነን የሚሉ ሁሉ መንገድ የሳቱ ወስላቶች ናቸው። ጠመጠመ፤ ወንጌላዊ፤ ነብይ፤ ፓስተር፤ ሃጂ ተባለ ተግባር የሌለው እንባቸው በግፍ የተነሳ ለሚፈስ ደጋፊ ለሌላቸው ያልቆመ እምነት በአፍንጫዬ ይውጣ።
    እዚህ ግባ የማይባልን ነገር ከተቀበረበት እየቆፈሩ እያወጡ ደረት ማስደቃቱና እግዚኦ ማህረነ ማሰኘቱ መቆም አለበት። ሰው በተሰጠው ጭንቅላት አስቦና ተሳስቦ መኖር መቻል አለበት። በዚህም በዚያም እያሳበቡ ሰውን አፍኖ መያዝና የማሰቢያ ብልሃቱን መቀማት ወንጀል ነው። ለእኛ የሰማይ ቤትን እያሳዩ ከስራችን ስንቱን ዘረፉ? ስንቱን በሌለ ቤቱ ጾም አዳሪ አደረጉት። እኔ መስቀሉ በቲሽርት ላይ ሆነ በሌላ ነገር ላይ ተዘቀዘቀ ተንጋደደ የመነጋገሪያ ነጥብ ሊሆን አይገባም ባይ ነኝ። እንዲሁ ለትንኝን እንደማጽዳት ይቆጠራል። ጽዳቱ ቀርቶ ሞቷ እንዲሉ። አየን እኮ በአንገታቸው ላይ መስቀል ያንጠለጠሉ፤ አልፎ ተርፎም ማተብ ያሰሩ በቀን አምስት ጊዜ የሚሰግድ አይደሉ እንዴ በሰሜን እናቶችን የደፈሩት፤ መነኩሴዎችን የገደሉት፤ እንስሳትና እጽዋትን የጨፈጨፉት። በወለጋ ቤት ዘግተው ሰውን ወደ ገደል የሰደድት አውሬዎች መሪ ሚሽን ውስጥ ያደጉ አይደሉምን? በአርሲ ያ ሁሉ ሲጨፈጨፍና ወደ ገደል ሲጣል ሃይማኖተኛ ነን በሚሉ ሰዎች የዘር ጥላቻ አልነበረምን? ውጊያው ከእነዚህ አውሬዎች ጋር እንጂ ከሸሚዝ መስቀል መዘቅዘቅና መንጋደድ ጋር አይደለም። ጥያቄው ባንተ ልብ ውስጥ ያለው መስቀል ተዘቅዝቆ ይሆን? እሱን ስጋልኝ። በቃኝ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule