• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በኢንተርኔት መቋረጥ 9 ሚሊዮን ዶላር፣ በሞባይል ኢንተርኔት ደግሞ 200 ሚሊዮን ዶላር ኪሣራ!

December 31, 2016 11:31 pm by Editor Leave a Comment

ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መታወጅና ከዚያ በፊት በነበረው ሁኔታ የኢንተርኔት መቆራረጥና መታገድ በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ላይ ጉዳት ማድረሱ የተጠቀሰ ሲሆን  ባለፈው አንድ ዓመት አገሪቱን 9 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ማሣጣቱን የአሜሪካው ብሩኪንግስ ኢንስቲቲዩት ይፋ ያደረገው ጥናት አመልክቷል። ዴልዮት የተባለው ዓለማቀፍ አማካሪ ተቋም በበኩሉ፤ የሞባይል ኢንተርኔት መዘጋት ሀገሪቱን በቀን 5 መቶ ሺህ ዶላር እያሳጣት ነው ብሏል።

በተለያዩ የሃገሪቱ ክፍሎች ተቃውሞና ግጭቶች መከሰታቸውን ተከትሎ የኢንተርኔት አገልግሎቶች መቆራረጥ፣ ሃገሪቱን በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ ብቻ ከ200 ሚሊዮን ብር በላይ አሳጥቷል ብሏል – ዴልዮት።

የኢንተርኔት አገልግሎት መቃወስ የኢኮኖሚ እድገቱን እንዲቀዛቀዝ አድርጓል ያለው “አፍሪካን ቢዝነስ”፤ ፈጠራዎች እንዳይበረታቱ፣ የገቢ ታክሶች በአግባቡ እንዳይሰበሰቡና ነጋዴዎች በቴክኖሎጂው ላይ ያላቸው እምነት እንዲሸረሸር ማድረጉን … የብሩኪንግ ኢንስቲቲዩት ም/ፕሬዚዳንት ዳረል ዌስትን ጠቅሶ ዘግቧል።

ዘመናዊ የኢኮኖሚ እድገት በኢንተርኔት ላይ ጥገኛ መሆኑን የጠቆመው ሪፖርቱ፤ ኢትዮጵያን ለመሳሰሉ ታዳጊ ሃገራት በአመታዊ ጠቅላላ አገራዊ ምርት እድገታቸው ላይ የ1.35 በመቶ ድርሻ እንዳለው ያመለክታል። የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ከታወጀበት ካለፈው ጥቅምት ወር ጀምሮ በተለይ የሞባይል ዳታ ኢንተርኔት ግንኙነት መቋረጡ፣ በመንግስት ገቢ ላይ ጉዳት ከማድረሱ በተጨማሪ የዕለት ተለት ስራቸው በቀጥታ ከኢንተርኔት ጋር ለተቆራኙ ነጋዴዎችም ከፍተኛ ኪሳራ እያስከተለባቸው እንደቆየ ጠቁሟል።

ከኢንተርኔት አገልግሎት ባሻገር ከፍተኛ ገቢ ከሚያስገኙ የቴክኖሎጂ ውጤቶች አንዱ የሆነው የተለያዩ የተንቀሳቃሽ ስልኮች መተግበሪያ (Application) እየተገደበ መሆኑን ሪፖርቱ ይጠቁማል – ቫይበር፣ ዋትሳፕና ሜሴንጀር የመሳሰሉ የኢንተርኔት የግንኙነት አውታሮች በዚህ መንገድ እየተገደቡ መሆኑን በመጥቀስ።

ባለፈው አመት በኢንተርኔት የኢኮኖሚ ጠቀሜታ ላይ የተደረገው ጥናት፤ በአሜሪካ የኢንተርኔት አገልግሎት በአመት እስከ 966 ቢሊዮን ዶላር ገቢ በማስገኘት፣ ከአጠቃላይ የሃገሪቱ ኢኮኖሚ 6 በመቶ ድርሻ እንዳለው የተጠቆመ ሲሆን ሌሎች ሃገራት ግን ከዚህ ቴክኖሎጂ ማግኘት የሚገባቸውን ከፍተኛ ገቢ አገልግሎቱን በመገደብ እያጡ መሆኑ ተመልክቷል።

የኢንተርኔት አገልግሎትን በመገደብ ከአፍሪካ በቀዳሚነት የተጠቀሰችው ሞሮኮ፤ በአመት 320 ሚሊዮን ዶላር ማጣቷ የተጠቀሰ ሲሆን ኮንጎ 72 ሚሊዮን ዶላር፣ አልጄሪያ 20 ሚሊዮን ዶላር፣ በአመት አጥተዋል ተብሏል። ኢትዮጵያ በበኩሏ፤ ባለፈው 1 ዓመት 9 ሚሊዮን ዶላር ማጣቷን ሪፖርቱ ጠቁሟል።

ከአፍሪካ ሃገራት ደቡብ አፍሪካ፣ ኬንያና ግብፅ የተሻለ የኢንተርኔት አገልግሎት እንዳላቸው የተጠቆመ ሲሆን ኢትዮጵያ፣ ናሚቢያና ደቡብ ሱዳን የኢንተርኔት አገልግሎታቸው ዝቅተኛና አርኪ አለመሆኑ ተመልክቷል። በጉዳዩ ዙሪያ ከመንግስት ኮሙኒኬሽን ፅ/ቤትም ሆነ ከኢትዮ-ቴሌኮም ምላሽ ለማግኘት ያደረግነው ተደጋጋሚ ሙከራ ጉዳዩ የሚመለከታቸው የስራ ኃላፊዎች “ስብሠባ ላይ ናቸው” ተብለን ሳይሳካልን ቀርቷል። (አለማየሁ አንበሴ፣ አዲስ አድማስ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule