• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የመረጃ መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ (ኢንሳ) በከፍተኛ ሥልጣንና ጉልበት በድጋሚ ሊቋቋም ነው

November 4, 2013 04:58 pm by Editor Leave a Comment

ባለፉት በርካታ ዓመታት በሥራ ላይ የሚገኘውን የመረጃ መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ ከፍተኛ ኃላፊነትና ጉልበት የሚሰጥና በድጋሚ እንዲቋቋም የሚያደርግ ረቂቅ አዋጅ ለፓርላማ ቀረበ፡፡

በፓርላማው ቋሚ ኮሚቴዎች ተጨማሪ ውይይት እየተደረገበት የሚገኘው ይህ ረቂቅ አዋጅ፣ በቀጣዮቹ ጥቂት ሳምንታት ይፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ረቂቅ አዋጁ ከፀደቀ በኋላ ኤጀንሲው በድጋሚ የሚዋቀር ሲሆን የአገሪቱ የፋይናንስ ተቋማትን፣ ብሔራዊ የኤሌክትሪክ ኃይል መረብን፣ በግንባታ ላይ የሚገኘውን አገራዊ የባቡር ትራንስፖርት መረብን፣ ወታደራዊ የኮምፒዩተር ሥርዓትንና ሌሎች ኮምፒዩተራይዝድ የሆኑ መሠረተ ልማቶችን በኮምፒዩተር አማካይነት ከሚቃጡ ጥቃቶች የመጠበቅ ኃላፊነት ይኖረዋል፡፡

የረቂቅ አዋጁ አባሪ ሰነድ ሆኖ የቀረበው ማብራሪያ እንደሚያስረዳው፣ በአገሪቱ በሚታየው የኢኮኖሚ ዕድገት ሳቢያ በርካታ የአገሪቱ እንቅስቃሴዎችና አገልግሎቶች የኮምፒዩተርና የኮምፒዩተር መረብ ጥገኛ መሆናቸው፣ እንዲሁም የዓለም ነባራዊ ሁኔታ አዋጁ እንዲዘጋጅና ኤጀንሲውን በድጋሚ እንዲቋቋም ለማድረግ ምክንያቶች ናቸው፡፡

የአገሪቱ የኤሌክትሪክ ኃይል፣ የባቡር፣ የአቪዬሽን፣ የውኃ አቅርቦትና ሌሎች ኮምፒዩተራይዝድ በሆኑ ሥርዓቶች እየተመሩ መሆኑን በአብነት ያነሳል፡፡ በምሳሌነትም የአገሪቱ የኃይድሮ ኤሌክትሪክ ማመንጫ፣ ማስፋፊያና ማሠራጫ ሥርዓቱ በኮምፒዩተራይዝድ ሥርዓት የሚመራ በመሆኑ፣ በዚህ ሥርዓት ላይ የሚደረግ የኮምፒዩተር ጥቃት የአገሪቱን የኃይል አቅርቦት ከማቋረጡም በተጨማሪ፣ ኃይል አመንጪ ግድቦች ውስጥ የተጠራቀመ ውኃ ፍሰቱ እንዲዛባ በማድረግ መሠረተ ልማቱ ሙሉ በሙሉ እንዲወድም ሊያደርግ እንደሚችል ይገልጻል፡፡

በተመሳሳይ በአገሪቱ እየተገነባ ያለው የባቡር ትራንስፖርት በኮምፒዩተር ሥርዓት ቁጥጥር የሚደረግበት በመሆኑ፣ በዚህ ሥርዓት ላይ ጥቃት በማድረስ ባቡሮች ከመስመራቸው ውጪ እንዲንቀሳቀሱና አደጋ እንዲደርስባቸው ምክንያት ሊሆን ይችላል በማለት ያስረዳል፡፡

በመሆኑም ኤጀንሲውን በድጋሚ በማዋቀር ሰፊ የደኅንነት ኃላፊነቶችን እንዲወጣ ማድረግ ተገቢ መሆኑን ይገልጻል፡፡ ይህንን ኃላፊነት ኤጀንሲው እንዲወጣ በኤጀንሲው ሥር ብሔራዊ የኮምፒዩተር ድንገተኛ አደጋ ምላሽ መስጫ ማዕከል እንዲቋቋም የሚያስችል አንቀጽ በረቂቅ አዋጁ ተካቷል፡፡ ማዕከሉ ሊደርሱ የሚችሉ ጥቃቶችን ለመለየት፣ ጥቃቶችን ቀድሞ በመተንተን ለማወቅ፣ ጥቃት ሲከሰት በብቃት መግታት ወይም መጠነ ሰፊ ጉዳት ሳያስከትል መቆጣጠርና ሌሎችንም ተግባራት የሚያከናውን ይሆናል፡፡

ኤጀንሲው ይህንን ኃላፊነቱን በአግባቡ ለመወጣት እንዲያስችለው የደኅንነት ኦዲት ማድረግ የሚያስችል ሥልጣን በረቂቁ ተካቷል፡፡ የደኅንነት ኦዲት ማለት ኮምፒዩተርን መሠረት ባደረገ ቁልፍ መሠረተ ልማት ላይ ተጋላጭነትን ለማወቅ የዘልቆ ገብ ፍተሻ ተግባራትን ማከናወንና አገራዊ የኢንፎርሜሽን ፖሊሲና ስታንዳርድን መሠረት በማድረግ፣ የተቋማቱን የኢንፎርሜሽን ደኅንነት ሥርዓት በመገምገም የእርምት ዕርምጃ እንዲወስዱ ማድረግ የሚል ትርጓሜ በረቂቁ ተሰጥቶታል፡፡

ኢንፎርሜሽን (መረጃን) መሠረት ባደረጉ ቁልፍ መሠረተ ልማቶች ወይም ሥርዓቶች ላይ እንዲሁም በዜጎች ሥነ ልቦና ላይ የሚሰነዘሩ የሳይበርና የኤሌክትሮማግኔቲክ ጥቃቶችን ለመከላከል አስፈላጊ አፀፋዊ ዕርምጃ የመውሰድ ኃላፊነት ይኖረዋል፡፡ የሳይበርና የኤሌክትሮማግኔቲክ ጥቃቶች የሚባሉት የኢንተርኔት ሬዲዮ ወይም ቴሌቪዥን፣ የቴሌቪዥንና የሬዲዮ አገልግሎቶች፣ የማኅበራዊ ሚዲያዎች (ማለትም ፌስቡክን የመሳሰሉ)፣ ዌብሳይቶች፣ ብሎጐችንና የመሳሰሉትን በመጠቀም የሚተላለፍ መሆኑን የአዋጁ ማብራሪያ ያትታል፡፡

በእነዚህ የመገናኛ አውታሮች የሚተላለፉ መረጃዎች ለማኅበራዊ፣ ለፖለቲካዊና ለኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ያላቸው ፋይዳ ግዙፍ ቢሆንም በተቃራኒው ለጦርነት ቅስቀሳ፣ የአገርን ገጽታ ለማጉደፍ፣ ፀረ ልማት ፕሮፓጋንዳዎችንና ኢኮኖሚያዊ ትንበያ (ስፔኩሌሽን) ማሠራጨት መጠቀሚያ ሊሆኑ እንደሚችሉ ማብራሪያው ይገልጻል፡፡ በመሆኑም የአዋጁን መፅደቅ ተከትሎ የተጠቀሱትን ጉዳት ያላቸውን መረጃዎች ኤጀንሲው የማክሸፍ ሕጋዊ ሥልጣን አለው፡፡

ኢንፎርሜሽንና ኮምፒዩተርን መሠረት ያደረጉ ቁልፍ መሠረተ ልማቶች ደኅንነትን ለማረጋገጥ ሲባል ከፍርድ ቤት ትዕዛዝ በማውጣት የጥቃት ሰለባ ወይም መነሻ ናቸው ተብለው በተጠረጠሩ ኮምፒዩተሮች ወይም መሠረተ ልማቶች ላይ አስፈላጊውን ምርመራ ማካሄድ፣ ሌላው በረቂቅ አዋጁ የተካተተ የኤጀንሲው የወደፊት ኃላፊነት ነው፡፡ (ምንጭ፡ ሪፖርተር)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Politics Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule