• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኢህአዴግን “አድርባይ” አመራሮች አስግተውታል

March 30, 2013 03:44 am by Editor 1 Comment

ኢህአዴግ አመራሮቹን “አድርባይነት የተጠናወታቸው” ሲል ፈረጀ። የከፍተኛ አመራሮች የግምገማ ውጤት የሆነውን ፍረጃ የሰሙ “የኢህአዴግ አባል ለመሆን አንዱና ዋናው መስፈርት አድርባይነት ነው” በማለት አድርባይነትን የፈጠረውና ያስፋፋው ራሱ ኢህአዴግ፣ በተለይም ህወሃት እንደሆነ አመለከቱ።

በባህር ዳሩ የኢህአዴግ ጉባኤ ላይ ተገኝቶ የነበረ ጋዜጠኛ በምሥጢር የላከው ዜና “አድርባይነት” ኢህአዴግን በሚፈታተን ደረጃ መስፋፋቱ መገለጹ አብዛኞችን የድርጅቱን አባላትን አስገርሟል።

ኢህአዴግን የፈጠረውና ከላይ ሆኖ የሚመራው ህወሃት “ነጻ” አመለካከት የማይወድ፣ የነጻ አስተሳሰብ ባህል የሌለው፣ ራሳቸውን የቻሉ ድርጅቶችን፣ ፓርቲዎችንና ማህበራትን አጥብቆ የሚጠላ፣ ሁሉም ለሱ እያጎበደዱ በሚሰፈርላቸው ቀለብ እንዲኖሩ ሌት ከቀን የሚሰራ መሆኑ እየታወቀ ማንን? ለምንና እንዴት አድርባይ በሚል እንደሚፈርጅ አብዛኞች ግራ መጋባታቸውን የደረሰን ዜና ያመለክታል።

ህወሃት በፈለፈላቸው ድርጅቶችና የአፈና ተቋማቱ አማካኝነት በሂደት የኢትዮጵያን አብዛኛውን ህዝብ “አጎብዳጅ” የማድረግና “አድርባይ” ሆነው የሚኖሩትን ቁጥር ማብዛት ዋናው ስትራቴጂው እንደሆነ እየታወቀ “አድርባይነት” እንዴት ለድርጅቱ በሽታ ሊሆን እንደቻለ ያልገባቸው እንዳሉት “አድርባይነት አስጊ ደረጃ ከደረሰ ህወሃት የለፋበትን ያገኘና በስኬት ጎዳና ላይ ለመሆኑ ማሳያ ነውና ስጋት ሊገባው አይገባም” የሚል የለበጣ አስተያየት መስጠታቸው ተጠቁሟል።

በስብሰባው ላይ በይፋ አስተያየት ከሰጡት መካከል አቶ አባይ ጸሐዬ ይጠቀሳሉ። በህወሃት የመከፋፈል ዘመን ቀደም ሲል ከውህዳኑ ጋር ያበሩ መስለው ሁለት ሳንጃ በመያዝ የተጫወቱት አቶ አባይ አሁን አድርባይ ተብሎ የተፈረጀው የኢህአዴግ አባል በሙሉ ወደ መካከለኛ አመራርነት ከተሸጋገረ አደጋው ከፍተኛ እንደሚሆን ተናግረዋል። ቀደም ሲል አባሉ በተመለመለበት ደረጃ ተግባሩን ሲያከናውን ባግባቡ አለመመዘኑ የአደጋው መነሻ ምክንያት እንደሆነ አመልክተዋል።

ኢህአዴግ አባሎቹ “አድርባይና አጎብዳጅ” እንደሆኑበት የገለጸው ስትራቴጂዎችን የመፈጸም ችግር ስላጋጠመው ነው። በጉባኤው ኢህአዴግን ያስደነገጠው ጉዳይ “አደገ” የተባለው የሰብል ምርት ሪፖርት ጉዳይ በዋናነት የሚጠቀስ ነው። አቶ በረከት በቀጥታ ተጠያቂ ያደረጉት ከፍተኛ ደረጃ ያለውን አመራር ነው። እንደሳቸው አባባል ታላቅ ንቅናቄ ሊፈጥር የሚችል የልማት ሰራዊት ያልተገነባበት ምክንያት ሊገመገም ይገባል።

በአሁኑ ወቅት ሰባት ሚሊዮን የሚጠጉ የተመዘገቡ አባላትን ያቀፈውና የቻይናን ኮሙኒስት ፓርቲ ሞዴል ወርሶ “በመለስ ውርስ ወደፊት” እያለ የሚጓዘው ኢህአዴግ አባላቱ “ፊት እያዩ የሚደፉ” መሆናቸው አደጋ መሆኑ ታምኖ መፍትሄ የተበጀለት ቢሆንም የቁርጠኛነትና በራስ ያለመተማመን ችግሩ ሰፊ ስለሆነ በቀላሉ ሊቀረፍ የሚችል እንዳልሆነ ተመልክቷል።

በተመሳሳይ ጉዳይ ሪፖርተር ባቀረበው ዜና አቶ ስዩም መስፍን “የራሱን የውስጥ ዲሞክራሲያዊ ሕይወት ያላስጠበቀ ካድሬ ወይም አመራር የሕዝቡን መብትና ዲሞክራሲ ሊያስጠብቅ አይችልም። ራሱ ነፃ ያልወጣና እየተሸማቀቀ የሚኖር ካድሬ ወይም አመራር የሕዝብን መብትና ጥቅም አስከብራለሁ ብሎ መንቀሳቀስ አይችልም” በማለት አድርባይነትን የፓርቲው አባላት እንዲታገሉ ማሳሰባቸውን አስነብቧል።

ወ/ሮ አዜብ በኢቲቪ አማካይነት በዚሁ ጉዳይ ሲነገሩ እንደተሰማው ችግሩ የቁርጠኛነት ጉዳይ እንደሆነ ገልጸዋል። “የሚባለው” በማለት የሰሙት መሆኑንን በመግለጽ ወ/ሮ አዜብ እንዳሉት “ለእንጀራና ለምደባ” ሲባል አድርባይነት መንገሱን ገልጸዋል። “ያሉት ክፍተቶች ቀላል አይደሉም” በማለት ማብራሪያቸው የሚያስከትሉት ወ/ሮ አዜብ፣ “ራሳችንን ማጽዳት፣ ግለኝነትን መታገል፣ ኪራይ ሰብሳቢነትን መዋጋት ያስፈልጋል” ካሉ በኋላ አስገራሚ አስተያየት ሰንዝረዋል።

“ቀናነት” እንደሚያስፈልግ በማሳሰብ “ስትራቴጂው አለ። ሲፈጸምም አይተነዋል” አሉ። በዚህ ንግግራቸው ባለቤታቸውን ያስታወሱት ወ/ሮ አዜብ “መቻቻልና አድርባይነት መጥፋት አለበት” የሚል መፈክር አሰምተዋል። በዚህ አላበቁም “እስከመጨረሻው፣ ከሁሉም ነገር ጽድት ብለን፣ በቁርጠኛነት የሚያደናቅፈንን  መቻቻልና አድርባይነት ከመድረክ ላይ መጥለፍ መቻል አለብን” ብለዋል። “መድረክ” ሲሉ የጠሩትን ግን አላብራሩም።

የኢህአዴግ ጉባኤ ሲጠናቀቅ በተለይም የእህል ምርት በሚገባውና በተቀመጠበት ደረጃ ማደጉ ቀርቶ አፈጻጸሙ ደካማ መሆኑ እንዳሰጋው፤ ምናልባትም የከፋ ድርቅ ሊከሰት የሚችልበት ሁኔታ ሊፈጠር ይችላል የሚለው ስጋት ህዝብን እንዳያነሳሳበት መፍራቱን ምንጮች አመልክተዋል።

የመላው ኢትዮጵያዊ ገቢ መጨመር እንዳለበት አቋም ቢያዝም በተለይም ጡረተኞችን፣ የቤት አበል የሚቀበሉ ቤተሰቦችን፣ እጅግ አነስተኛ በሆነ የደሞዝ ጣሪያ የተቀጠሩትንና በቀን ስራ የተሰማሩትን ስለማካተቱ በግልጽ የተባለ ነገር የለም። በኢትዮጵያ በደርግ ጊዜ ቤት ተወርሶባቸው በ30 እና 40 ብር አበል ላለፉት አርባ ዓመታት ተረስተው የኖሩ ዜጎች ቁጥር ቀልል የሚባል አይደለም። እነዚህ ወገኖች ለአፈር ግብር እንዲከፍሉ የሚጠየቁት ከሚያገኙት አበል በላይ መሆኑም ይታወቃል። አንዳንድ ቦታ ተከራዮች ከባለቤቶቹ (በውርስ ንብረታቸው ከተወሰደባቸው) በላይ ተከራይቶ በማከራየት ተጠቃሚ ናቸው። ዜናውን የላከልን እንዳለው ያገባናል የሚሉ ሁሉ አስቀድመው በዚህ ጉዳይ ላይ ከህዝብ ጋር በመነጋገር እንዲሰሩ አሳስበዋል። (ፎቶ: Ethiopian Herald)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. yo says

    March 30, 2013 05:14 am at 5:14 am

    Garbage news

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule