• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኢህአዴግን “አድርባይ” አመራሮች አስግተውታል

March 30, 2013 03:44 am by Editor 1 Comment

ኢህአዴግ አመራሮቹን “አድርባይነት የተጠናወታቸው” ሲል ፈረጀ። የከፍተኛ አመራሮች የግምገማ ውጤት የሆነውን ፍረጃ የሰሙ “የኢህአዴግ አባል ለመሆን አንዱና ዋናው መስፈርት አድርባይነት ነው” በማለት አድርባይነትን የፈጠረውና ያስፋፋው ራሱ ኢህአዴግ፣ በተለይም ህወሃት እንደሆነ አመለከቱ።

በባህር ዳሩ የኢህአዴግ ጉባኤ ላይ ተገኝቶ የነበረ ጋዜጠኛ በምሥጢር የላከው ዜና “አድርባይነት” ኢህአዴግን በሚፈታተን ደረጃ መስፋፋቱ መገለጹ አብዛኞችን የድርጅቱን አባላትን አስገርሟል።

ኢህአዴግን የፈጠረውና ከላይ ሆኖ የሚመራው ህወሃት “ነጻ” አመለካከት የማይወድ፣ የነጻ አስተሳሰብ ባህል የሌለው፣ ራሳቸውን የቻሉ ድርጅቶችን፣ ፓርቲዎችንና ማህበራትን አጥብቆ የሚጠላ፣ ሁሉም ለሱ እያጎበደዱ በሚሰፈርላቸው ቀለብ እንዲኖሩ ሌት ከቀን የሚሰራ መሆኑ እየታወቀ ማንን? ለምንና እንዴት አድርባይ በሚል እንደሚፈርጅ አብዛኞች ግራ መጋባታቸውን የደረሰን ዜና ያመለክታል።

ህወሃት በፈለፈላቸው ድርጅቶችና የአፈና ተቋማቱ አማካኝነት በሂደት የኢትዮጵያን አብዛኛውን ህዝብ “አጎብዳጅ” የማድረግና “አድርባይ” ሆነው የሚኖሩትን ቁጥር ማብዛት ዋናው ስትራቴጂው እንደሆነ እየታወቀ “አድርባይነት” እንዴት ለድርጅቱ በሽታ ሊሆን እንደቻለ ያልገባቸው እንዳሉት “አድርባይነት አስጊ ደረጃ ከደረሰ ህወሃት የለፋበትን ያገኘና በስኬት ጎዳና ላይ ለመሆኑ ማሳያ ነውና ስጋት ሊገባው አይገባም” የሚል የለበጣ አስተያየት መስጠታቸው ተጠቁሟል።

በስብሰባው ላይ በይፋ አስተያየት ከሰጡት መካከል አቶ አባይ ጸሐዬ ይጠቀሳሉ። በህወሃት የመከፋፈል ዘመን ቀደም ሲል ከውህዳኑ ጋር ያበሩ መስለው ሁለት ሳንጃ በመያዝ የተጫወቱት አቶ አባይ አሁን አድርባይ ተብሎ የተፈረጀው የኢህአዴግ አባል በሙሉ ወደ መካከለኛ አመራርነት ከተሸጋገረ አደጋው ከፍተኛ እንደሚሆን ተናግረዋል። ቀደም ሲል አባሉ በተመለመለበት ደረጃ ተግባሩን ሲያከናውን ባግባቡ አለመመዘኑ የአደጋው መነሻ ምክንያት እንደሆነ አመልክተዋል።

ኢህአዴግ አባሎቹ “አድርባይና አጎብዳጅ” እንደሆኑበት የገለጸው ስትራቴጂዎችን የመፈጸም ችግር ስላጋጠመው ነው። በጉባኤው ኢህአዴግን ያስደነገጠው ጉዳይ “አደገ” የተባለው የሰብል ምርት ሪፖርት ጉዳይ በዋናነት የሚጠቀስ ነው። አቶ በረከት በቀጥታ ተጠያቂ ያደረጉት ከፍተኛ ደረጃ ያለውን አመራር ነው። እንደሳቸው አባባል ታላቅ ንቅናቄ ሊፈጥር የሚችል የልማት ሰራዊት ያልተገነባበት ምክንያት ሊገመገም ይገባል።

በአሁኑ ወቅት ሰባት ሚሊዮን የሚጠጉ የተመዘገቡ አባላትን ያቀፈውና የቻይናን ኮሙኒስት ፓርቲ ሞዴል ወርሶ “በመለስ ውርስ ወደፊት” እያለ የሚጓዘው ኢህአዴግ አባላቱ “ፊት እያዩ የሚደፉ” መሆናቸው አደጋ መሆኑ ታምኖ መፍትሄ የተበጀለት ቢሆንም የቁርጠኛነትና በራስ ያለመተማመን ችግሩ ሰፊ ስለሆነ በቀላሉ ሊቀረፍ የሚችል እንዳልሆነ ተመልክቷል።

በተመሳሳይ ጉዳይ ሪፖርተር ባቀረበው ዜና አቶ ስዩም መስፍን “የራሱን የውስጥ ዲሞክራሲያዊ ሕይወት ያላስጠበቀ ካድሬ ወይም አመራር የሕዝቡን መብትና ዲሞክራሲ ሊያስጠብቅ አይችልም። ራሱ ነፃ ያልወጣና እየተሸማቀቀ የሚኖር ካድሬ ወይም አመራር የሕዝብን መብትና ጥቅም አስከብራለሁ ብሎ መንቀሳቀስ አይችልም” በማለት አድርባይነትን የፓርቲው አባላት እንዲታገሉ ማሳሰባቸውን አስነብቧል።

ወ/ሮ አዜብ በኢቲቪ አማካይነት በዚሁ ጉዳይ ሲነገሩ እንደተሰማው ችግሩ የቁርጠኛነት ጉዳይ እንደሆነ ገልጸዋል። “የሚባለው” በማለት የሰሙት መሆኑንን በመግለጽ ወ/ሮ አዜብ እንዳሉት “ለእንጀራና ለምደባ” ሲባል አድርባይነት መንገሱን ገልጸዋል። “ያሉት ክፍተቶች ቀላል አይደሉም” በማለት ማብራሪያቸው የሚያስከትሉት ወ/ሮ አዜብ፣ “ራሳችንን ማጽዳት፣ ግለኝነትን መታገል፣ ኪራይ ሰብሳቢነትን መዋጋት ያስፈልጋል” ካሉ በኋላ አስገራሚ አስተያየት ሰንዝረዋል።

“ቀናነት” እንደሚያስፈልግ በማሳሰብ “ስትራቴጂው አለ። ሲፈጸምም አይተነዋል” አሉ። በዚህ ንግግራቸው ባለቤታቸውን ያስታወሱት ወ/ሮ አዜብ “መቻቻልና አድርባይነት መጥፋት አለበት” የሚል መፈክር አሰምተዋል። በዚህ አላበቁም “እስከመጨረሻው፣ ከሁሉም ነገር ጽድት ብለን፣ በቁርጠኛነት የሚያደናቅፈንን  መቻቻልና አድርባይነት ከመድረክ ላይ መጥለፍ መቻል አለብን” ብለዋል። “መድረክ” ሲሉ የጠሩትን ግን አላብራሩም።

የኢህአዴግ ጉባኤ ሲጠናቀቅ በተለይም የእህል ምርት በሚገባውና በተቀመጠበት ደረጃ ማደጉ ቀርቶ አፈጻጸሙ ደካማ መሆኑ እንዳሰጋው፤ ምናልባትም የከፋ ድርቅ ሊከሰት የሚችልበት ሁኔታ ሊፈጠር ይችላል የሚለው ስጋት ህዝብን እንዳያነሳሳበት መፍራቱን ምንጮች አመልክተዋል።

የመላው ኢትዮጵያዊ ገቢ መጨመር እንዳለበት አቋም ቢያዝም በተለይም ጡረተኞችን፣ የቤት አበል የሚቀበሉ ቤተሰቦችን፣ እጅግ አነስተኛ በሆነ የደሞዝ ጣሪያ የተቀጠሩትንና በቀን ስራ የተሰማሩትን ስለማካተቱ በግልጽ የተባለ ነገር የለም። በኢትዮጵያ በደርግ ጊዜ ቤት ተወርሶባቸው በ30 እና 40 ብር አበል ላለፉት አርባ ዓመታት ተረስተው የኖሩ ዜጎች ቁጥር ቀልል የሚባል አይደለም። እነዚህ ወገኖች ለአፈር ግብር እንዲከፍሉ የሚጠየቁት ከሚያገኙት አበል በላይ መሆኑም ይታወቃል። አንዳንድ ቦታ ተከራዮች ከባለቤቶቹ (በውርስ ንብረታቸው ከተወሰደባቸው) በላይ ተከራይቶ በማከራየት ተጠቃሚ ናቸው። ዜናውን የላከልን እንዳለው ያገባናል የሚሉ ሁሉ አስቀድመው በዚህ ጉዳይ ላይ ከህዝብ ጋር በመነጋገር እንዲሰሩ አሳስበዋል። (ፎቶ: Ethiopian Herald)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. yo says

    March 30, 2013 05:14 am at 5:14 am

    Garbage news

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule