• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ህወሃት/ኢህአዴግ የራሱን ሪፖርት ይፋ ማድረግ ፈርቷል!

November 5, 2016 03:13 am by Editor Leave a Comment

ከሰብዓዊ መብቶች ጋር በምንም ዓይነት መልኩ የማይተዋወቀው፤ መተዋወቅና መግባባትም የማይችለው ህወሃት “የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን” ብሎ ባቋቋመው ጽ/ቤቱ አማካኝነት በሰኔ 2008ዓም “በኦሮምያ ክልል የተቃውሞ እንቅስቃሴ ወቅት በፀጥታ ኃይሎች የተወሰደው እርምጃ አስፈላጊና ተመጣጣኝ ነበር” በማለት ዘገባ ማውጣቱ ይታወሳል፡፡ ይህ በቃል “ለፓርላማው” የቀረበው ሪፖርት እስካሁን ድረስ ይፋ አልተደረገም፡፡ የሂውማን ራይት ዎችም እስካሁን በተደጋጋሚ ኢህአዴግ ሪፖርቱን “እንዲያወጣ” ጥሪ ሲያስተላልፍ ቆይቷል፡፡ ጌታቸው ረዳ ከሂውማን ራይትስ ተመራማሪ ፊሊክስ ሆርን ጋር በአልጃዚራ ላይ በቀረበ ጊዜ ሰብዓዊ መብት ድርጅቱን በመወከል ሚ/ር ሆርን ኢህአዴግ ሪፖርቱን ይፋ እንዲደርግ በይፋ ጠይቀዋል፡፡ አሁን ደግሞ የመብት ድርጅቱ በወርቅነህ ገበየሁ ወልደኪዳን “ነገዎ” በኩል ለህወሃት/ኢህአዴግ በጻፈው ግልጽ ደብዳቤ “የራሱ ፓርላማ ሰዎች ያላነበቡትን ሪፖርት” ይፋ እንዲያደርግ ኢህአዴግን ተገዳድሯል፡፡

ለዓመታት በሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ድርጅት – ሂውማን ራይትስ ዎች – ላይ የስድብ ናዳ ሲያወርድ የነበረው ህወሃት ከሰብዓዊ መብት ድርጅቱ ግልጽ ደብዳቤ ደርሶታል፡፡ የመብት ተሟጋቹ ድርጅት ህወሃት/ኢህአዴግን ለምታደርሱት ወንጀል ያለንን ማስረጃ ይዘን ቤታችሁ ድረስ መምጣት እንችላለን ወይም ከተወካያችሁ ጋር ሌላ አገር ላይ መገናኘት እንችላለን ብሏል፡፡

felix-horne
ፊሊክስ ሆርን ስለኢትዮጵያ ጉዳይ በአውሮጳ ፓርላማ

የሰብዓዊ መብት ድርጅቱ ግልጽ ደብዳቤውን የላከው አሁን ለተሾመው ወርቅነህ ገበየሁ ወልደኪዳን “ነገዎ” ሲሆን የደብዳቤው ሃሳብ ትኩረት ያደረገው ቴድሮስ አድሃኖም ከቀድሞ ሥልጣኑ ከመነሳቱ በፊት ስለ መብት ተሟጋች ድርጅቱ በተለይም በኢትዮጵያ ላይ ምርምር ስለሚያደርጉት ፊሊክስ ሆርን ነው፡፡ በOctober 22, 2016 (ጥቅምት 12፤2009) ስለ ፊሊክስ ሆርን በተለቀቀው ረጅም ጽሁፍ ላይ ህወሃት በተመራማሪው የሚቀርቡትን የጽሁፍ፣ የቪዲዮ መረጃዎችና መግለጫዎችን በሙሉ ኮንኗል፤ ማስረጃ ሳያቀርብም ሃሰት ናቸው ብሏቸዋል፡፡ ከዚህም አልፎ “ሂውማን ራይትስ ዎች በኢትዮጵያ የተውቃውሞ አመጽ እንዲነሳ ያደፋፍራል” በማለት ድርጅቱንም ዘልፏል፡፡

ለዚህ የህወሃት ዘለፋ ምላሽ ይሆን ዘንድ ዛሬ November 4, 2016 (ጥቅምት 25፤2009) ድርጅቱ በላከው ግልጽ ደብዳቤ በቴድሮስ አማካኝነት የተለቀቀውን የህወሃት ክስ ዕርቃኑን አስቀርቶታል፡፡ የመብት ድርጅቱ ሥራውን “በዓለም ዙሪያ በ90 አገራት ውስጥ” እንደሚያከናውን በመጥቀስ በሌሎች አገሮች እንደሚደርገው በኢትዮጵያ ላይ ማንኛውንም አቢይ ሪፖርት ለሕዝብ ይፋ ከማድረጉ በፊት የግኝቶቹን ማጠቃለያ፣ የተሰጡትን የእርምት ሃሳቦችን በተመለከተ አስተያየት በመጠየቅ ኢትዮጵያን በግፍ እየገዛ ላለው ህወሃት ሲያቀርብ እንደኖረ ገልጾዋል፡፡ ሆኖም እስካሁን ድረስ ይህ ነው የሚባል ቀጥተኛ የሆነ ይፋዊ ምላሽ ከህወሃት/ኢህአዴግ እንዳላገኘ በደብዳቤው አውስቷል፡፡

ድርጅቱ ባለው አሠራር መሠረት መረጃ የሚያቀብሉትን ግለሰቦች ማንነት ይፋ እንደማያደርግ የገለጸ ሲሆን ይህ ደግሞ የአሠራር ጉዳይ ብቻ ሳይሆን መረጃ ሰጪዎቹ በህይወታቸው ላይ አደጋ እንደሚደርስ በግልጽ በመናገራቸውና ህይወታቸው ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ መሆኑን አስረድቷል፡፡ የጥቃት hrwሰለባዎችን ብቻ በማነጋገር ዘገባ እንደማያቀርብ የተናገረው ድርጅት ከእነርሱ ከሚገኘው መረጃ በተጨማሪ የራሱን የሆነ ምርመራ እንዴት እንደሚደርግና ዘገባ እንደሚያጠናቅር በየጊዜው በሚወጣው ሪፖርት ላይ በግልጽ እንደሚያሰፍል ተናግሯል፡፡ ሆኖም ግን ማስተካከያዎች ካሉ ዘገባው እንዲሻሻል ማረሚያ መቀበያ ገጽ ከቀድሞ ጀምሮ አዘጋጅቶ ማስቀመጡን አስታውቋል፡፡ ከዚህ ሌላ ግን ህወሃት ለስድስት ወር ባወጀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ምክንያት ለማንኛውም ድርጅት መረጃ ማቀበል እንደ ወንጀል በመታየቱ የመረጃ አቀባዮቻችን ማንነት በምሥጢር እንድንይዝ ያስገድደናል በማለት የመብት ድርጅቱ ህወሃትን በራሱ ህግ አጣብቂኝ ውስጥ ከቶታል፡፡

ካለፈው ህዳር 2008ዓም ጀምሮ በከፍተኛ ሁኔታ እየደረሰ ያለውን የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት አስመልክቶ ዓለምዓቀፋዊ ምርመራ እንዲደረግ የተጠየቀ መሆኑን ያስታወሰው ደብዳቤ በሰኔ 2008ዓም ህወሃት/ኢህአዴግ በራሱ “ፓርላማ” በቃል የተናገረውን ዘገባእስካሁን ይፋ አለማድረጉን በድጋሚ አስረድቷል፡፡ “በኦሮምያ ክልል የተቃውሞ እንቅስቃሴ ወቅት በፀጥታ ኃይሎች የተወሰደው እርምጃ አስፈላጊና ተመጣጣኝ ነበር” በማለት በህወሃት ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን የቀረበው ዘገባ ማንም የጽሁፍ ሪፖርቱ እንዳልደረሰው ሂውማን ራይትስ ዎች አስታውቋል፡፡ የመብት ተሟጋች ድርጅቱ ያነጋገራቸው “የፓርላማ” አባላት የጽሁፍ ሪፖርቱ ያላዩትና ያልደረሳቸው መሆኑን የጠቀሰው ደብዳቤ ሌሎች ተመሳሳይ የመብት ጥሰቶችን የሚዘግቡ ድርጅቶች ከሚያወጡበት የአዘጋገብ ስልት ehrcበተለየ መልኩ በህወሃት/ኢህአዴግ “የተወሰደው እርምጃ አስፈላጊና ተመጣጣኝ” በሚል በዘገባው የተሰጠው የተዛባ ድምዳሜ በዘገባ አቀራረብ ስልት ልዩ እንደሚያደርገው ጠቁሟል፡፡ ስለዚህ ይላል ደብዳቤው፤ “በጽሁፍ የታተመ ዘገባ በእርግጥ ካለ ለሕዝብ ይፋ እንድታደርጉት አጥብቀን እናስገነዝባችኋለን” በማለት ሂውማን ራይትስ ዎች በድጋሚ ህወሃት/ኢህአዴግን እጅግ የሚገዳደር ጥያቄ አቅርቧል፡፡

ዓለምአቀፋዊ ምርመራ እንዲካሄድ አሁንም ጥያቄውን ያቀረበው ድርጅት እንዲህ ዓይነቱ ምርመራ በኤርትራ፣ በቡሩንዲና በደቡብ ሱዳን እንዲካሄድ ድርጅታችን ይፋ ሲያደርግ ህወሃት/ኢህአዴግ በፍጥነት ድጋፍ መስጠቱን በማስታወስ አሁንም የሺዎች ሰዎች ላይ የደረሰው የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ፍትህና ተጠያቂነት እንደሚያስፈልገው በግልጽ አስረድቷል፡፡

በመጨረሻም ይህ በአውሮጳ ኅብረት የሂውማን ራይትስ ዎች ዳይሬክተር የተላከው ደብዳቤ እየተፈጸ ስላለው የመበት ረገጣ በሌላ አነጋገር ህወሃት እየፈጸመ ላለው ወንጀል ያለንን ማስረጃ ይዘን ቤታችሁ ድረስ መምጣት እንችላለን ወይም ከተወካያችሁ ጋር ሌላ አገር ላይ መገናኘት እንችላለን በማለት ደብዳቤው ተግዳሮቱን ይፋ አድርጓል፡፡

በጄኔራልነት ማዕረግ የፖሊስ ኃላፊ በመሆን ከዚያም በፊትም ሆነ በኋላ የሰብዓዊ መብቶችን ሲጨፈላልቅ ለመጣው ወርቅነህ ገበየሁ ወልደኪዳን “ነገዎ” ይህ ደብዳቤ “ሹመት ያዳብር” እጅ መንሻ አይደለም በማለት ቅድመ ግምት አስቀማጮች ለጎልጉል አስታውቀዋል፡፡ እንዲያውም ሂውማን ራይትስ ዎች በዚህ መልኩ ህወሃት/ኢህአዴግን በመገዳደር የላከው ደብዳቤ ግፍ በመፈጸም ለከፍተኛ ሹመት የበቃውን የወርቅነህ ገበየሁ ወልደኪዳን “ነገዎ”ን “ዘንዶ” ቀን ጠብቆ የሚያወጣ “አሣ ጎርጓሪ” ደብዳቤ እንዳይሆን በማለት እነዚሁ አስተያየት ሰጪዎች ለጎልጉል አስረድተዋል፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am
  • ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ September 7, 2023 01:40 pm
  • “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል” September 7, 2023 01:31 am
  • ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል August 24, 2023 11:50 pm
  • ጀብደኛው August 24, 2023 10:06 am
  • ጎንደርና ባሕር ዳር ከተሞች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው ተመልሰዋል August 13, 2023 10:55 pm
  • ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች August 13, 2023 10:26 pm
  • ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ August 13, 2023 09:11 pm
  • ወደ ኤርትራ በኮንትሮባንድ የሚሻገሩ ቆሳቁሶች እየተያዙ ነው August 11, 2023 12:52 pm
  • የአማራ ክልል ትልልቅ ከተሞች ተኩስ ዓልባ ሆነው ውለዋል August 10, 2023 04:31 pm
  • “አንድ ሰው ለመግደል ኅንፃውን ማቃጠል” የኢ-ዲሞክራሲና ጽንፈኛ ኃይሎች ቅዠት፤ (ክፍል ሁለት) August 10, 2023 09:44 am
  • “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ August 10, 2023 09:08 am
  • በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ August 9, 2023 11:47 am
  • ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ  August 8, 2023 05:47 pm
  • “ሃሳብ ሲነጥፍ ነፍጥ አንግቤ እዋጋለሁ” የሚሉ አካላት ላይ እርምጃ ይወሰዳል – የመከላከያ ሠራዊት August 1, 2023 09:25 am
  • ደቡብ አፍሪካ የመሸጉ ወንጀለኞች ለሕግ ተላልፈው ሊሰጡ ነው July 31, 2023 09:27 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule