• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ህወሃት/ኢህአዴግ የራሱን ሪፖርት ይፋ ማድረግ ፈርቷል!

November 5, 2016 03:13 am by Editor Leave a Comment

ከሰብዓዊ መብቶች ጋር በምንም ዓይነት መልኩ የማይተዋወቀው፤ መተዋወቅና መግባባትም የማይችለው ህወሃት “የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን” ብሎ ባቋቋመው ጽ/ቤቱ አማካኝነት በሰኔ 2008ዓም “በኦሮምያ ክልል የተቃውሞ እንቅስቃሴ ወቅት በፀጥታ ኃይሎች የተወሰደው እርምጃ አስፈላጊና ተመጣጣኝ ነበር” በማለት ዘገባ ማውጣቱ ይታወሳል፡፡ ይህ በቃል “ለፓርላማው” የቀረበው ሪፖርት እስካሁን ድረስ ይፋ አልተደረገም፡፡ የሂውማን ራይት ዎችም እስካሁን በተደጋጋሚ ኢህአዴግ ሪፖርቱን “እንዲያወጣ” ጥሪ ሲያስተላልፍ ቆይቷል፡፡ ጌታቸው ረዳ ከሂውማን ራይትስ ተመራማሪ ፊሊክስ ሆርን ጋር በአልጃዚራ ላይ በቀረበ ጊዜ ሰብዓዊ መብት ድርጅቱን በመወከል ሚ/ር ሆርን ኢህአዴግ ሪፖርቱን ይፋ እንዲደርግ በይፋ ጠይቀዋል፡፡ አሁን ደግሞ የመብት ድርጅቱ በወርቅነህ ገበየሁ ወልደኪዳን “ነገዎ” በኩል ለህወሃት/ኢህአዴግ በጻፈው ግልጽ ደብዳቤ “የራሱ ፓርላማ ሰዎች ያላነበቡትን ሪፖርት” ይፋ እንዲያደርግ ኢህአዴግን ተገዳድሯል፡፡

ለዓመታት በሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ድርጅት – ሂውማን ራይትስ ዎች – ላይ የስድብ ናዳ ሲያወርድ የነበረው ህወሃት ከሰብዓዊ መብት ድርጅቱ ግልጽ ደብዳቤ ደርሶታል፡፡ የመብት ተሟጋቹ ድርጅት ህወሃት/ኢህአዴግን ለምታደርሱት ወንጀል ያለንን ማስረጃ ይዘን ቤታችሁ ድረስ መምጣት እንችላለን ወይም ከተወካያችሁ ጋር ሌላ አገር ላይ መገናኘት እንችላለን ብሏል፡፡

felix-horne
ፊሊክስ ሆርን ስለኢትዮጵያ ጉዳይ በአውሮጳ ፓርላማ

የሰብዓዊ መብት ድርጅቱ ግልጽ ደብዳቤውን የላከው አሁን ለተሾመው ወርቅነህ ገበየሁ ወልደኪዳን “ነገዎ” ሲሆን የደብዳቤው ሃሳብ ትኩረት ያደረገው ቴድሮስ አድሃኖም ከቀድሞ ሥልጣኑ ከመነሳቱ በፊት ስለ መብት ተሟጋች ድርጅቱ በተለይም በኢትዮጵያ ላይ ምርምር ስለሚያደርጉት ፊሊክስ ሆርን ነው፡፡ በOctober 22, 2016 (ጥቅምት 12፤2009) ስለ ፊሊክስ ሆርን በተለቀቀው ረጅም ጽሁፍ ላይ ህወሃት በተመራማሪው የሚቀርቡትን የጽሁፍ፣ የቪዲዮ መረጃዎችና መግለጫዎችን በሙሉ ኮንኗል፤ ማስረጃ ሳያቀርብም ሃሰት ናቸው ብሏቸዋል፡፡ ከዚህም አልፎ “ሂውማን ራይትስ ዎች በኢትዮጵያ የተውቃውሞ አመጽ እንዲነሳ ያደፋፍራል” በማለት ድርጅቱንም ዘልፏል፡፡

ለዚህ የህወሃት ዘለፋ ምላሽ ይሆን ዘንድ ዛሬ November 4, 2016 (ጥቅምት 25፤2009) ድርጅቱ በላከው ግልጽ ደብዳቤ በቴድሮስ አማካኝነት የተለቀቀውን የህወሃት ክስ ዕርቃኑን አስቀርቶታል፡፡ የመብት ድርጅቱ ሥራውን “በዓለም ዙሪያ በ90 አገራት ውስጥ” እንደሚያከናውን በመጥቀስ በሌሎች አገሮች እንደሚደርገው በኢትዮጵያ ላይ ማንኛውንም አቢይ ሪፖርት ለሕዝብ ይፋ ከማድረጉ በፊት የግኝቶቹን ማጠቃለያ፣ የተሰጡትን የእርምት ሃሳቦችን በተመለከተ አስተያየት በመጠየቅ ኢትዮጵያን በግፍ እየገዛ ላለው ህወሃት ሲያቀርብ እንደኖረ ገልጾዋል፡፡ ሆኖም እስካሁን ድረስ ይህ ነው የሚባል ቀጥተኛ የሆነ ይፋዊ ምላሽ ከህወሃት/ኢህአዴግ እንዳላገኘ በደብዳቤው አውስቷል፡፡

ድርጅቱ ባለው አሠራር መሠረት መረጃ የሚያቀብሉትን ግለሰቦች ማንነት ይፋ እንደማያደርግ የገለጸ ሲሆን ይህ ደግሞ የአሠራር ጉዳይ ብቻ ሳይሆን መረጃ ሰጪዎቹ በህይወታቸው ላይ አደጋ እንደሚደርስ በግልጽ በመናገራቸውና ህይወታቸው ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ መሆኑን አስረድቷል፡፡ የጥቃት hrwሰለባዎችን ብቻ በማነጋገር ዘገባ እንደማያቀርብ የተናገረው ድርጅት ከእነርሱ ከሚገኘው መረጃ በተጨማሪ የራሱን የሆነ ምርመራ እንዴት እንደሚደርግና ዘገባ እንደሚያጠናቅር በየጊዜው በሚወጣው ሪፖርት ላይ በግልጽ እንደሚያሰፍል ተናግሯል፡፡ ሆኖም ግን ማስተካከያዎች ካሉ ዘገባው እንዲሻሻል ማረሚያ መቀበያ ገጽ ከቀድሞ ጀምሮ አዘጋጅቶ ማስቀመጡን አስታውቋል፡፡ ከዚህ ሌላ ግን ህወሃት ለስድስት ወር ባወጀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ምክንያት ለማንኛውም ድርጅት መረጃ ማቀበል እንደ ወንጀል በመታየቱ የመረጃ አቀባዮቻችን ማንነት በምሥጢር እንድንይዝ ያስገድደናል በማለት የመብት ድርጅቱ ህወሃትን በራሱ ህግ አጣብቂኝ ውስጥ ከቶታል፡፡

ካለፈው ህዳር 2008ዓም ጀምሮ በከፍተኛ ሁኔታ እየደረሰ ያለውን የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት አስመልክቶ ዓለምዓቀፋዊ ምርመራ እንዲደረግ የተጠየቀ መሆኑን ያስታወሰው ደብዳቤ በሰኔ 2008ዓም ህወሃት/ኢህአዴግ በራሱ “ፓርላማ” በቃል የተናገረውን ዘገባእስካሁን ይፋ አለማድረጉን በድጋሚ አስረድቷል፡፡ “በኦሮምያ ክልል የተቃውሞ እንቅስቃሴ ወቅት በፀጥታ ኃይሎች የተወሰደው እርምጃ አስፈላጊና ተመጣጣኝ ነበር” በማለት በህወሃት ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን የቀረበው ዘገባ ማንም የጽሁፍ ሪፖርቱ እንዳልደረሰው ሂውማን ራይትስ ዎች አስታውቋል፡፡ የመብት ተሟጋች ድርጅቱ ያነጋገራቸው “የፓርላማ” አባላት የጽሁፍ ሪፖርቱ ያላዩትና ያልደረሳቸው መሆኑን የጠቀሰው ደብዳቤ ሌሎች ተመሳሳይ የመብት ጥሰቶችን የሚዘግቡ ድርጅቶች ከሚያወጡበት የአዘጋገብ ስልት ehrcበተለየ መልኩ በህወሃት/ኢህአዴግ “የተወሰደው እርምጃ አስፈላጊና ተመጣጣኝ” በሚል በዘገባው የተሰጠው የተዛባ ድምዳሜ በዘገባ አቀራረብ ስልት ልዩ እንደሚያደርገው ጠቁሟል፡፡ ስለዚህ ይላል ደብዳቤው፤ “በጽሁፍ የታተመ ዘገባ በእርግጥ ካለ ለሕዝብ ይፋ እንድታደርጉት አጥብቀን እናስገነዝባችኋለን” በማለት ሂውማን ራይትስ ዎች በድጋሚ ህወሃት/ኢህአዴግን እጅግ የሚገዳደር ጥያቄ አቅርቧል፡፡

ዓለምአቀፋዊ ምርመራ እንዲካሄድ አሁንም ጥያቄውን ያቀረበው ድርጅት እንዲህ ዓይነቱ ምርመራ በኤርትራ፣ በቡሩንዲና በደቡብ ሱዳን እንዲካሄድ ድርጅታችን ይፋ ሲያደርግ ህወሃት/ኢህአዴግ በፍጥነት ድጋፍ መስጠቱን በማስታወስ አሁንም የሺዎች ሰዎች ላይ የደረሰው የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ፍትህና ተጠያቂነት እንደሚያስፈልገው በግልጽ አስረድቷል፡፡

በመጨረሻም ይህ በአውሮጳ ኅብረት የሂውማን ራይትስ ዎች ዳይሬክተር የተላከው ደብዳቤ እየተፈጸ ስላለው የመበት ረገጣ በሌላ አነጋገር ህወሃት እየፈጸመ ላለው ወንጀል ያለንን ማስረጃ ይዘን ቤታችሁ ድረስ መምጣት እንችላለን ወይም ከተወካያችሁ ጋር ሌላ አገር ላይ መገናኘት እንችላለን በማለት ደብዳቤው ተግዳሮቱን ይፋ አድርጓል፡፡

በጄኔራልነት ማዕረግ የፖሊስ ኃላፊ በመሆን ከዚያም በፊትም ሆነ በኋላ የሰብዓዊ መብቶችን ሲጨፈላልቅ ለመጣው ወርቅነህ ገበየሁ ወልደኪዳን “ነገዎ” ይህ ደብዳቤ “ሹመት ያዳብር” እጅ መንሻ አይደለም በማለት ቅድመ ግምት አስቀማጮች ለጎልጉል አስታውቀዋል፡፡ እንዲያውም ሂውማን ራይትስ ዎች በዚህ መልኩ ህወሃት/ኢህአዴግን በመገዳደር የላከው ደብዳቤ ግፍ በመፈጸም ለከፍተኛ ሹመት የበቃውን የወርቅነህ ገበየሁ ወልደኪዳን “ነገዎ”ን “ዘንዶ” ቀን ጠብቆ የሚያወጣ “አሣ ጎርጓሪ” ደብዳቤ እንዳይሆን በማለት እነዚሁ አስተያየት ሰጪዎች ለጎልጉል አስረድተዋል፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule