• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የጋምቤላ ክልል በህንድና በሳዑዲ ኩባንያዎች ላይ ዕርምጃ እንዲወሰድ ጠየቀ

December 11, 2013 05:10 am by Editor Leave a Comment

የጋምቤላ ክልላዊ መንግሥት ሦስት የውጭ አገር ኩባንያዎች ከፍተኛ ችግር ታይቶባቸዋል፣ የፕሮጀክት አፈጻጸማቸውም ደካማ ነው በሚል የፌዴራል መንግሥት ዕርምጃ እንዲወስድ ጠየቀ፡፡

የክልሉ መንግሥት በቅርቡ ለግብርና ሚኒስቴር፣ በግልባጭ ደግሞ ለጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት በጻፈው ደብዳቤ የህንድ ኩባንያዎች የሆኑትን ካሩቱሪንና ቬርደንታ ሃርቨስት፣ እንዲሁም የሼክ መሐመድ አል አሙዲ ኩባንያ የሆነው ሳዑዲ ስታር የእርምትና የማስተካከያ ዕርምጃ እንዲወሰድባቸው ጠይቋል፡፡

በጋምቤላ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ጋትሉዋክ ቱት ኮት ተፈርሞ የወጣው ደብዳቤ እንደሚያመለክተው፣ የክልሉ መንግሥት በነዋሪዎች አስተያየት ላይ ተመርኩዞ የራሱን ግምገማ አካሂዷል፡፡ ክልሉ ባካሄደው ግምገማ በተለይ እነዚህ ሦስት የውጭ አገር ኩባንያዎች ከፍተኛ ችግር እንደታየባቸውና የፕሮጀክት አፈጻጸማቸውም ደካማ መሆኑን አረጋግጧል፡፡

ከእነዚህ ኩባንያዎች መካከል ካሩቱሪ አግሮ ኢንዱስትሪ ተጠቃሽ ነው፡፡ ካሩቱሪ በ2000 ዓ.ም. በኑዌር ዞንና በኢታንግ ልዩ ወረዳ አንድ መቶ ሺሕ ሔክታር መሬት ወስዷል፡፡ ኩባንያው ከወሰደው መሬት ውስጥ 25 ሺሕ ሔክታር መሬት ላይ ምንጣሮ አካሂዷል፡፡ ነገር ግን ከመነጠረው መሬት ታርሶ በዘር የተሸፈነው ስምንት ሺሕ ሔክታር መሬት ነው፡፡ ከዚህ ውስጥ በ7,750 ሔክታር በቆሎ፣ በ250 ሔክታር ሸንኮራ አገዳ አልምቷል፡፡ ነገር ግን ኩባንያው ሥራ ከጀመረ አምስት ዓመት ቢሆነውም እስካሁን ከሙከራ የዘለለ ለገበያ የቀረበ ምርት አለመኖሩ በክልሉ ተጠቅሷል፡፡

የክልሉ ፕሬዚዳንት ደብዳቤ እንደሚያስረዳው፣ ኩባንያው በቢዝነስ ፕላኑ ለአካባቢው ኅብረተሰብ ማኅበራዊ አገልግሎት የሚውሉ ግንባታዎችን እንደሚገነባ ቢገልጽም፣ ግንባታው ካለመካሄዱም በላይ የመሬት ግብርም በወቅቱ አልተከፈለም፡፡

ኩባንያው የባሮ ወንዝ ወደ ማሳው እንዳይገባ በወንዙ ዳር የሠራቸው ግድቦች በአካባቢው ኅብረተሰብ ላይ ከፍተኛ ጎርፍ አደጋና ከፍተኛ የንብረትና እርሻ ውድመት አስከትለዋል ብሏል፡፡

በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠው የህንዱ ኩባንያ ቬርዳንታ ሃርቨስት አግሮ ኢንዱስትሪ ነው፡፡ ይህ ኩባንያ በ2000 ዓ.ም. በክልሉ ማጃንግ ዞን ጎደሬ ወረዳ 3,012 ሔክታር መሬት ተረክቧል፡፡ ‹‹ድርጅቱ ከመነሻው መሬቱን ሲረከብ ሻይ ቅጠል ለማልማት ቢሆንም፣ የእርሻ ሥራውን እያከናወነ የሚገኘው በአካባቢው ከፍተኛ የሆነ ጥቅጥቅ ደንና ወንዞችና ጅረቶች በሚገኙበት ሥፍራ በመሆኑ፣ ብዙ ደን እየወደመና ወንዞችና ጅረቶችም እየደረቁ መሆናቸው እየተስተዋለ ነው፤›› ሲል ክልሉ ለፌዴራል መንግሥት የጻፈው ደብዳቤ ያመለክታል፡፡

‹‹ድርጅቱ ከቆመለት ዓላማ በተቃራኒ ከአካባቢው ደን ጣውላ በማምረት ሲያጓጉዝ በተጨባጭ ተይዟል፤›› ሲል ደብዳቤው ጨምሮ ያስረዳል፡፡

ክልሉ ለፌዴራል መንግሥት የጻፈው ይህ ደብዳቤ ያንፀባረቃቸው ሐሳቦች ከዚህ በፊት በነበሩት ጊዜያት የካዳቸው እንደነበሩ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ወገኖች ያስታውሳሉ፡፡ ይህ ኩባንያ የአካባቢው ነዋሪዎችና የአካባቢ ተቆርቋሪዎች እየሄደበት ያለው መንገድ አግባብ አለመሆኑን በተደጋጋሚ ሲገልጹ፣ የቀድሞው ፕሬዚዳንት አቶ ግርማ ወልደ ጊዮርጊስ ታህሳስ 2003 ዓ.ም. ለግብርና ሚኒስትሩ አቶ ተፈራ ደርበው በጻፉት ደብዳቤ፣ ‹‹በምንም ምክንያት የደን መሬት ለእርሻ መሰጠት ስለሌለበት ደኑን ማልማት ለሚፈልጉ ሰዎች፣ ወይም በሕዝብ ተሳትፎ እንዲለማ ተገቢው እንዲፈጸም እጠይቃለሁ፤›› ሲሉ ማሳሰባቸው ይታወሳል፡፡

ነገር ግን በወቅቱ የግብርና ሚኒስቴርም ሆነ የክልሉ መንግሥት ቦታው ቁጥቋጦ እንጂ የደን መሬት አለመሆኑ እየተጠቀሰ የቅሬታ አቅራቢዎች ጥያቄ ውድቅ መደረጉ ይታወሳል፡፡ ከአራት ሳምንት በፊት የዚህ ኩባንያ ንብረት በእሳት የወደመ ሲሆን፣ በውድመቱ የተጠረጠሩ ስምንት ሰዎች በቁጥጥር ሥር ውለዋል፡፡

የክልሉ መንግሥት ይህንን እውነት ባመነበት ደብዳቤ ላይ ለኩባንያው የተሰጠው መሬት በደንና በወንዞች የተሞላ መሆኑን ከመግለጹም በላይ፣ ኅብረተሰቡ በቦታው ላይ የይገባኛል ጥያቄ እየቀረበና እሮሮም እያሰማ መሆኑን አምኖአል፡፡

በሦስተኛ ደረጃ የተቀመጠው ሳዑዲ ስታር ግብርና ልማት ኩባንያ ነው፡፡ ይህ ኩባንያ በ2001 ዓ.ም. በአኙዋ ዞን አቦቦ ወረዳ አሥር ሺሕ ሔክታር መሬት ተረክቧል፡፡ ኩባንያው ሰባት ሺሕ ሔክታር መሬት ቢመነጥርም፣ አርሶ በዘር የሸፈነው 135 ሔክታር መሬት ብቻ ነው፡፡

ኩባንያው ወደ ሥራ ከገባ አምስት ዓመታት ቢያስቆጥርም በርካታ ሥራዎቹ በጅምር ቀርተዋል፡፡ ወደ እርሻ የሚወስደው ዋናው መንገድ በድርጅቱ ከባድ ተሽከርካሪዎች በየጊዜው እየተባላሸ ኅብረተሰቡ እጅግ የሚመረርበት እንደሆነና ይህንን መንገድ ሳዑዲ ስታር በአስፋልት ደረጃ ለመገንባት የገባውን ቃል እንዳላከበረ ክልሉ ለፌዴራል መንግሥት በጻፈው ደብዳቤ አስታውቋል፡፡ ሳዑዲ ስታር በከፍተኛ የማኔጅመንትና የፋይናንስ ቀውስ ውስጥ እንደሚገኝ መረጃዎች እየጠቆሙ ከመሆኑም በላይ የኩባንያው ንብረት ለጉዳት እንደተዳረገ ይነገራል፡፡

የፌዴራል መንግሥት እነዚህ ኩባንያዎች ያሉበት ወቅታዊ ሁኔታ ገምግሞ ዕርምጃ እንዲወሰድ ክልሉ ጥያቄ አቅርቧል፡፡ (ሪፖርተር) (ፎቶ፡ ለማሳያነት ብቻ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Politics Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule