• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የጋምቤላ ክልል በህንድና በሳዑዲ ኩባንያዎች ላይ ዕርምጃ እንዲወሰድ ጠየቀ

December 11, 2013 05:10 am by Editor Leave a Comment

የጋምቤላ ክልላዊ መንግሥት ሦስት የውጭ አገር ኩባንያዎች ከፍተኛ ችግር ታይቶባቸዋል፣ የፕሮጀክት አፈጻጸማቸውም ደካማ ነው በሚል የፌዴራል መንግሥት ዕርምጃ እንዲወስድ ጠየቀ፡፡

የክልሉ መንግሥት በቅርቡ ለግብርና ሚኒስቴር፣ በግልባጭ ደግሞ ለጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት በጻፈው ደብዳቤ የህንድ ኩባንያዎች የሆኑትን ካሩቱሪንና ቬርደንታ ሃርቨስት፣ እንዲሁም የሼክ መሐመድ አል አሙዲ ኩባንያ የሆነው ሳዑዲ ስታር የእርምትና የማስተካከያ ዕርምጃ እንዲወሰድባቸው ጠይቋል፡፡

በጋምቤላ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ጋትሉዋክ ቱት ኮት ተፈርሞ የወጣው ደብዳቤ እንደሚያመለክተው፣ የክልሉ መንግሥት በነዋሪዎች አስተያየት ላይ ተመርኩዞ የራሱን ግምገማ አካሂዷል፡፡ ክልሉ ባካሄደው ግምገማ በተለይ እነዚህ ሦስት የውጭ አገር ኩባንያዎች ከፍተኛ ችግር እንደታየባቸውና የፕሮጀክት አፈጻጸማቸውም ደካማ መሆኑን አረጋግጧል፡፡

ከእነዚህ ኩባንያዎች መካከል ካሩቱሪ አግሮ ኢንዱስትሪ ተጠቃሽ ነው፡፡ ካሩቱሪ በ2000 ዓ.ም. በኑዌር ዞንና በኢታንግ ልዩ ወረዳ አንድ መቶ ሺሕ ሔክታር መሬት ወስዷል፡፡ ኩባንያው ከወሰደው መሬት ውስጥ 25 ሺሕ ሔክታር መሬት ላይ ምንጣሮ አካሂዷል፡፡ ነገር ግን ከመነጠረው መሬት ታርሶ በዘር የተሸፈነው ስምንት ሺሕ ሔክታር መሬት ነው፡፡ ከዚህ ውስጥ በ7,750 ሔክታር በቆሎ፣ በ250 ሔክታር ሸንኮራ አገዳ አልምቷል፡፡ ነገር ግን ኩባንያው ሥራ ከጀመረ አምስት ዓመት ቢሆነውም እስካሁን ከሙከራ የዘለለ ለገበያ የቀረበ ምርት አለመኖሩ በክልሉ ተጠቅሷል፡፡

የክልሉ ፕሬዚዳንት ደብዳቤ እንደሚያስረዳው፣ ኩባንያው በቢዝነስ ፕላኑ ለአካባቢው ኅብረተሰብ ማኅበራዊ አገልግሎት የሚውሉ ግንባታዎችን እንደሚገነባ ቢገልጽም፣ ግንባታው ካለመካሄዱም በላይ የመሬት ግብርም በወቅቱ አልተከፈለም፡፡

ኩባንያው የባሮ ወንዝ ወደ ማሳው እንዳይገባ በወንዙ ዳር የሠራቸው ግድቦች በአካባቢው ኅብረተሰብ ላይ ከፍተኛ ጎርፍ አደጋና ከፍተኛ የንብረትና እርሻ ውድመት አስከትለዋል ብሏል፡፡

በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠው የህንዱ ኩባንያ ቬርዳንታ ሃርቨስት አግሮ ኢንዱስትሪ ነው፡፡ ይህ ኩባንያ በ2000 ዓ.ም. በክልሉ ማጃንግ ዞን ጎደሬ ወረዳ 3,012 ሔክታር መሬት ተረክቧል፡፡ ‹‹ድርጅቱ ከመነሻው መሬቱን ሲረከብ ሻይ ቅጠል ለማልማት ቢሆንም፣ የእርሻ ሥራውን እያከናወነ የሚገኘው በአካባቢው ከፍተኛ የሆነ ጥቅጥቅ ደንና ወንዞችና ጅረቶች በሚገኙበት ሥፍራ በመሆኑ፣ ብዙ ደን እየወደመና ወንዞችና ጅረቶችም እየደረቁ መሆናቸው እየተስተዋለ ነው፤›› ሲል ክልሉ ለፌዴራል መንግሥት የጻፈው ደብዳቤ ያመለክታል፡፡

‹‹ድርጅቱ ከቆመለት ዓላማ በተቃራኒ ከአካባቢው ደን ጣውላ በማምረት ሲያጓጉዝ በተጨባጭ ተይዟል፤›› ሲል ደብዳቤው ጨምሮ ያስረዳል፡፡

ክልሉ ለፌዴራል መንግሥት የጻፈው ይህ ደብዳቤ ያንፀባረቃቸው ሐሳቦች ከዚህ በፊት በነበሩት ጊዜያት የካዳቸው እንደነበሩ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ወገኖች ያስታውሳሉ፡፡ ይህ ኩባንያ የአካባቢው ነዋሪዎችና የአካባቢ ተቆርቋሪዎች እየሄደበት ያለው መንገድ አግባብ አለመሆኑን በተደጋጋሚ ሲገልጹ፣ የቀድሞው ፕሬዚዳንት አቶ ግርማ ወልደ ጊዮርጊስ ታህሳስ 2003 ዓ.ም. ለግብርና ሚኒስትሩ አቶ ተፈራ ደርበው በጻፉት ደብዳቤ፣ ‹‹በምንም ምክንያት የደን መሬት ለእርሻ መሰጠት ስለሌለበት ደኑን ማልማት ለሚፈልጉ ሰዎች፣ ወይም በሕዝብ ተሳትፎ እንዲለማ ተገቢው እንዲፈጸም እጠይቃለሁ፤›› ሲሉ ማሳሰባቸው ይታወሳል፡፡

ነገር ግን በወቅቱ የግብርና ሚኒስቴርም ሆነ የክልሉ መንግሥት ቦታው ቁጥቋጦ እንጂ የደን መሬት አለመሆኑ እየተጠቀሰ የቅሬታ አቅራቢዎች ጥያቄ ውድቅ መደረጉ ይታወሳል፡፡ ከአራት ሳምንት በፊት የዚህ ኩባንያ ንብረት በእሳት የወደመ ሲሆን፣ በውድመቱ የተጠረጠሩ ስምንት ሰዎች በቁጥጥር ሥር ውለዋል፡፡

የክልሉ መንግሥት ይህንን እውነት ባመነበት ደብዳቤ ላይ ለኩባንያው የተሰጠው መሬት በደንና በወንዞች የተሞላ መሆኑን ከመግለጹም በላይ፣ ኅብረተሰቡ በቦታው ላይ የይገባኛል ጥያቄ እየቀረበና እሮሮም እያሰማ መሆኑን አምኖአል፡፡

በሦስተኛ ደረጃ የተቀመጠው ሳዑዲ ስታር ግብርና ልማት ኩባንያ ነው፡፡ ይህ ኩባንያ በ2001 ዓ.ም. በአኙዋ ዞን አቦቦ ወረዳ አሥር ሺሕ ሔክታር መሬት ተረክቧል፡፡ ኩባንያው ሰባት ሺሕ ሔክታር መሬት ቢመነጥርም፣ አርሶ በዘር የሸፈነው 135 ሔክታር መሬት ብቻ ነው፡፡

ኩባንያው ወደ ሥራ ከገባ አምስት ዓመታት ቢያስቆጥርም በርካታ ሥራዎቹ በጅምር ቀርተዋል፡፡ ወደ እርሻ የሚወስደው ዋናው መንገድ በድርጅቱ ከባድ ተሽከርካሪዎች በየጊዜው እየተባላሸ ኅብረተሰቡ እጅግ የሚመረርበት እንደሆነና ይህንን መንገድ ሳዑዲ ስታር በአስፋልት ደረጃ ለመገንባት የገባውን ቃል እንዳላከበረ ክልሉ ለፌዴራል መንግሥት በጻፈው ደብዳቤ አስታውቋል፡፡ ሳዑዲ ስታር በከፍተኛ የማኔጅመንትና የፋይናንስ ቀውስ ውስጥ እንደሚገኝ መረጃዎች እየጠቆሙ ከመሆኑም በላይ የኩባንያው ንብረት ለጉዳት እንደተዳረገ ይነገራል፡፡

የፌዴራል መንግሥት እነዚህ ኩባንያዎች ያሉበት ወቅታዊ ሁኔታ ገምግሞ ዕርምጃ እንዲወሰድ ክልሉ ጥያቄ አቅርቧል፡፡ (ሪፖርተር) (ፎቶ፡ ለማሳያነት ብቻ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Politics Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሤራ አክሻፊው ጎንደር ለሦስተኛ ጊዜ ታሪክ ሠራ May 10, 2023 09:25 am
  • ማር በከፍተኛ ደረጃ የኮንትሮባንድ ሰለባ ሆኗል May 9, 2023 09:24 am
  • ኦነግ በኦሮሚያ ሪፈረንደም እንዲካሄድ መጠየቁ ለሰላም ንግግሩ ዕንቅፋት ሆነ May 4, 2023 01:12 am
  • መረጃ ቲቪ ያጋራው አሳሳች መረጃ May 2, 2023 12:37 pm
  • “ከፈጣሪ በታች መከላከያ የሁላችን ዋስ ጠበቃ ነው፤ ትልቅ ይቅርታ እንጠይቃለን” April 13, 2023 10:19 am
  • በትግራይ የ”ልጆቻችን የት ናቸው?” ጥያቄ እየተሰማ ነው April 13, 2023 08:56 am
  • በትህነግ የፈረሰው የአክሱም ኤርፖርት ያስከተለው ዘርፈብዙ ኪሣራ April 13, 2023 03:21 am
  • “የከተማው ነዋሪ በመሰላቸቱ ተፈናቃዮች ከፍተኛ የምግብ ችግር” ገጥሟቸዋል April 12, 2023 09:23 am
  • ከዕድሜ ልክ እስከ 20 ዓመት ቅጣት ተበይኖባቸዋል April 11, 2023 02:58 pm
  • የኡጋንዳ የክልሎች ሚኒስትር በቆርቆሮ ሌብነት ተጠርጥረው ታሰሩ April 10, 2023 03:59 pm
  • ታከለ ከተነሳ በኋላ የመዐድን ሌቦች እየተያዙ ነው April 6, 2023 02:53 pm
  • አገር ለማተራመስ ያለመ የምሁራን፣ የሚዲያ ባለቤቶችና አክቲቪስቶች ህቡዕ ቡድን ተያዘ April 4, 2023 10:07 am
  • በ10 ዓመት ውስጥ ከ44 ቢሊየን ዶላር በላይ ሸሽቷል April 4, 2023 09:26 am
  • አየር ጨብጦ አሁን ያለውን መንግሥት ከሥልጣን ልቀቁ አይሆንም March 29, 2023 09:47 am
  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule