• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የዕርቁ ካርድ እንዳይባክን!! የተደበቃችሁ ተገለጡ!!

August 24, 2013 02:52 am by Editor 3 Comments

“ከፍትህ ጋር ተቀነባብሮ ያልተፈጸመ ዕርቅ ዘላቂነት የለውም፤ ሁላችንም ሰላም እንዲሰፍን ተስፋ የምናደርግ ብንሆንም የምንመኘው ሰላም በፍትህና በሕግ ላይ የተመሠረተ መሆን ይገባዋል እንጂ በተገኘው ሁኔታ ይሁን የምንለው መሆን የለበትም” የቀድሞ የፊሊፕንስ ፕሬዚዳንት ኮራዞን አኪኖ፡፡

ወደ ሥልጣን የተጠጉና ለመጠጋት የሚያስቡ ፓርቲዎችና ግለሰቦች እንዲሁም ሥልጣንን የተቆጣጠሩ ወዘተ በአገራችን ዕርቅ እንዲመጣ ሲመኙ፣ ሲያቅዱ፣ ፕሮግራም ሲያወጡ፣ ዲስኩር ሲሰጡ፣ … ቢያንስ አራት አሥርተ ዓመታትን አስቆጥረናል፡፡ “ብሔራዊ ዕርቅ፣ አገር አቀፋዊ ዕርቅ፣ … ” እየተባለ ሲነገር የሰማነው አሁን አይደለም፡፡ እስኪሰለቸን ሰምተናል። እርቅን ያህል ታላቅ ጉዳይ “የፖለቲካ ሃይሎጋ ሆ” አስመስለው ሲጫወቱበት የቆዩ፣ አሁንም ድረስ “ባገር ሽማግሌነት” ስም የሚቆምሩ የትውልድና ያገር “ችግር ቁልፍ ተወናዮች” እንዳሉ ህዝብ ያውቃል። ለይቶ በስም ይጠራቸዋል።

በአገራችን ከትዳርና መሰል ማኅበራዊ ጉዳዮች ጋር በተያያዘ ግጭቶች ሲከሰቱ ተጣዪ ወገኖችን ለማስታረቅ ሽማግሌዎች ይመረጣሉ፡፡ እነዚህ ሽማግሌዎች ተናግረው የሚያሳምኑ፣ ነገራቸው ተቀባይነት ያለው፣ ኅብረተሰቡ የሚያከብራቸው፣ ቃላቸው መሬት ጠብ የማይል፣ ከፍ ያለ የመንፈስ ልዕልና የተጎናጸፉ፣ የተከበሩ፣ እውነተኛና ዋንኛ ዓላማቸው በኅብረተሰቡ ዘንድ ሰላምና ዕርቅ የማስፈን ብቻ የሆኑ ናቸው፡፡

ይህንን ዓይነቱን አገራዊ ቅርስ ወደ ፖለቲካው በማምጣት ሙሉውን ሃሳብ ሳይሆን ቁንጽል የሆነውን “ሽምግልና እና ዕርቅ” የሚለውን ሃሳብ ብቻ በመውሰድ በርካታ የፖለቲካ ሰዎች የዕርቅን ሃሳብ ሲያራምዱ ቆይተዋል፡፡ እኛም እንጠይቃለን – ለምን አልተሳካላቸውም? መልሱ ቀላል ነው – የዕርቅንና የሽምግልና መስፈርትን ስለማያሟሉ ወይም ማሟላት ስላልቻሉ ነው!!

ሥልጣንና ወንበር በቀን ቅዠትና በሌት ሕልማቸው ዕረፍት የነሳቸው፣ ኅብረተሰቡ ሙሉ እምነት ሊሰጣቸው የማይችሉ፣ የማይታመኑ፣ ከዚያም አልፎ በተደጋጋሚ ቀይ ካርድ የተሰጣቸው፣ እውነትና ሐቅን ይዘው ሳይሆን ቂምንና በቀልን ቋጥረው የተነሱ፣ ሲናገሩ ሕዝብን ሊያሳምንና ሊያቀራርብ የሚችል ሃሳብ ሳይሆን የበለጠ የሚያራርቅና የሚያጨካክን መርዝ የሚረጩ፣ ላመኑበት ዕውነት እስከመጨረሻ የመቆም ወኔ ያላቸው ሳይሆኑ ከየቦታው ለሚወረወርላቸው ቁራሽ የተገዙና ኅሊናቸውን የሸጡ፣ ዕድሜያቸው ዓመታትን ከመቁጠር በስተቀር “ሽማግሌ” ተብሎ ለመጠራት ማዕረግ ያልበቁ፣ ተምረናል፣ አውቀናል፣ ተፈላስፈንበታል ቢሉም ሲናገሩ ግን አፋቸው ደም የሚሞላ፣ … ዝንተዓለም ዕርቅ፣ ብሔራዊ ዕርቅ፣ … እያሉ ቢሰብኩ እንዴት ለሽምግልናና ዕርቅ ሹመት ይበቃሉ? እንዴትስ ሕዝብ አመኔታውን ይሰጣቸዋል?

ስለዚህ የዕርቅ ሃሳብ በኢትዮጵያ ውስጥ ተግባራዊ አልሆነም ብቻ ሳይሆን የምንለው መልዕክቱም በትክክለኛ ሰዎች አልተሰበከም፡፡ ወደ ሕዝብ ጆሮ አልደረሰም፡፡ ህዝብ እንዲሰማ አልተደረገም። ሕዝብ እንዲሰማ የተደረገውና የሚደነቁርበት “እንግዴ” የሆነ እርቅ በመሆኑ ችግርን ከማክረር የዘለለ መፍትሄ አላስገኘም። በጉቦ፣ አንጃ በመፍጠርና ድርጅትን በመሰንጠቅ የሚደረጉ መስማማቶች መካን ሆነው ቀርተዋል። ሽምግልናውን ጭምር ያቆሸሸው ኢህአዴግ ቀና ከሆነ አሁንም ተስፋ አለ። ሕዝብ አልተጣላምና!!

ከቀድሞው አለቃቸው በተለየ መልኩ መንፈሣዊ እንደሆኑ የተነገረላቸው ጠ/ሚ/ር ሃይለማርያምም ሃሳቡን የገለጸን ሁሉ “አሸባሪ፣ አክራሪ፣ …” በማለት ሳይሆን ያነበቡት ቅዱስ መጽሐፍ ባስተማራቸውና አምነዋለሁ በሚሉት መልኩ ታሪክ በመሥራት የኢትዮጵያ ታዳጊ ለመሆን ጊዜው አላለፈባቸውም፡፡ ከአለቃቸው ሞት ብዙ የሚማሩት እንደሚኖር እናምናለን፡፡ ሕዝብ ተመርሮና፣ ስቃይ የዕለት ተዕለት ኑሮው በሆነበት በአሁኑ ወቅት ለማርገብ ያልሞከሩት ውስብስብ ችግር ማሰሮው ተሰብሮ ጂኒው ከወጣ በኋላ የገነቡት “ታላቅ የመከላከያ ሠራዊትም ሆነ የፌዴራል ኃይል” መልሶ ወደ ማሰሮው መመለስ አይችልም፡፡ እናም አቶ ሃይለማርያም ራሳቸውን ለመስዋዕት እስከማቅረብ ድረስ በመሔድ ኢትዮጵያ ላይ የረመጠውን ረመጥ ለማስወገድ የእርቅ ዋጋ እንዲከፍሉ ለማሳሰብ እንወዳለን። እሳቸውና የሚመሩት ኢህአዴግን ጨምሮ ሰላም የሚሹ በርካቶች አሉና እርቅን እንደሚቀበሉ ለማወጅ ይዘጋጁ። አሁን የቀረው አንድ መፍትሔ እርቅ ብቻ ነውና!!

ከላይ ከጠቀስናቸው ሌላ የኅብረተሰብ ክፍሎች ደግሞ አሉ፡፡ የመንፈስ ልዕልናቸው እጅግ ከፍ ያለ፣ በኅብረተሰቡ ዘንድ መታመን የሚችሉ፣ የአገራቸውን ሰላምና ጸጥታ እንጂ ሌላ ዓይነት የሥልጣንም ሆነ የግልጥቅም የሌላቸው፣ የዕርቅን ሃሳብ ከልባቸው የሚያምኑና ተበድለውም እንኳን ለመጪው ትውልድና ለአገር ጥቅም ሲሉ በደላቸውን ውጠው ልባቸውን ለዕርቅ ክፍት ያደረጉ፣ በእርግጥ ሽማግሌ የሚለው ሥልጣንና ሹመት የሚገባቸው – በዕድሜ ስለበለጸጉ ሳይሆን ሃሳባቸው ጽዱ፣ አመለካከታቸው ቅን፣ ምኞታቸው ግልጽ የሆኑ የአገር ልጆች አሉ፡፡

እንዲህ ዓይነት ሰዎች በተቃዋሚው ጎራ ወይም በሃይማኖት ድርጅት ብቻ ሳይሆን በገዢው ኃይልም ውስጥ አሉ፡፡ “ከአነሳሳችን ኢትዮጵያን እንደዚህ ለማድረግ አይደለም” የሚሉና እስካሁን ከቁጭት ባላለፈ ምንም ሳያደርጉ የተቀመጡ ግን አጋጣሚ የሚጠብቁ አሉ፡፡ የሚደረገው ነገር ሁሉ ያቅለሸለሻቸውና መውጫውን የሚፈልጉ ወይም አስተማማኝ መውጫ ከሚያሳያቸው ጋር ለመሰለፍ ፍላጎት ያላቸው አሉ፡፡

በሁሉም ወገን ያለው ሚዲያ ሰክሮና ሕዝቡንም እያሰከረ ባለበት ባሁኑ ወቅት ዕድል ፈንታ ያልተሰጣቸው ቅን ሰዎች መኖራቸው ሊያስደንቀን አይገባም፡፡ የሃይማኖት መሪዎች ካድሬ በሆኑበትና ወንጌላውያን ለብጣሽ ዳቦ አዳሪ በሆኑበት ዘመን ኢትዮጵያ አሁንም ሃቀኛና ትሁት ሰዎች አሏት፡፡ ለእነዚህ ኢትዮጵያውያን የእኛም ጥሪ ከተደበቃችሁበት ውጡ! ለኅሊናችሁ ተገዙ! ለአገራችሁ የዕርቅን መፍትሔ በመተግበር ከዚህ በፊት ተሰርቶ ያልታወቀ ታሪክ ሥሩ! የሚል ነው፡፡ ለአገራችን የወደፊት ዕጣ የቀረን አንድ የመጫወቻ ካርድ ዕርቅ ነው፤ እንዳይባክን ማድረግ በዓላማው የሚያምኑና ሕዝብ የሚቀበላቸው ሽማግሌዎች ኃላፊነት ነው፡፡ ሕዝብ እንደማይቀበላችሁ እያወቃችሁ እንደማንኛውም የፖለቲካ ፕሮግራምም ሆነ ተሞክሮ ዕርቅን በመሞከር ይህንን የተቀደሰ ዓላማ ለመልከፍ የምትፈልጉ ሁሉ እስካሁን ያልተሳካላችሁ ለምን እንደሆነ በመመርመር ራሳችሁን ጠይቁ፡፡ከማትደበቁት ህሊናችሁ ጋር በመስማማት ቀናውን ውሳኔ እንድትወስኑ ለመመወከር እንወዳለን።

እናንተ በተለያየ ምክንያት ራሳችሁን ደብቃችሁ ያላችሁ ለዚህ ክቡር ዓላማ በመነሳት አገራችሁን አድኑ፤ ኢትዮጵያን የዕርቅ ተምሳሌት አድርጓትና ደም መፋሰስን በየቀኑ የሚመኙላትን የውስጥና የውጭ ኃይሎች አሳፍሩ! በሽፍንፍን፤ በአዝሃለሁ – ተቀበል አካሄድ፤ ለሥልጣን ባተኮረ ድብቅ ዓላማ፣ … ሳይሆን በእውነትና በፍትሕ ላይ የተመሠረተ ዕርቅ ለአገራችሁ አምጡ፡፡ እንደ አንድ የሚዲያ አካል ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣም ከጎናችሁ ይቆማል፡፡


ይህ ርዕሰ አንቀጽ የ“ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ®” አቋም ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Editorial Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. anoole wako says

    August 24, 2013 05:56 am at 5:56 am

    tekekelagna ena waktaw malekt naw ! Joro yalaw yesma ! Ayn yalaw yanbeb ! Lebona yalaw yasalasel !

    Reply
  2. koster says

    August 24, 2013 10:46 am at 10:46 am

    Do not expect peace from a puppet, the question is when will he be slaughtered by the home grown fascists.

    Reply
  3. gishay says

    August 27, 2013 07:09 am at 7:09 am

    Yes it is time for reconcilliation . hulum beashenafinet liweta yemichelew bezih menged bicha new . qenenet kale hagerachin be ereqe menged tedenalech . ethiopiawi meftehe bicha new yemiyadenen . golgul please be the mouth of this noble idea. thanks

    Reply

Leave a Reply to gishay Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule