• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ፕሮፍ ተሸኙ!

October 6, 2020 11:14 pm by Editor 3 Comments

የጂኦግራፊ ሊቅ የሰብዓዊ መብት ተሟጋችና ደራሲ መስፍን ወልደ ማርያም (ፕሮፌሰር) (1922-2013)

“አንድ ትውልድ ይወለዳል፣ በጊዜው እንደጊዜው ያድጋል፣ ያልፋል፣ በሌላ ትውልድ ይተካል። አዲሱም ትውልድ የተረከበውን ቅርስ ይዞ ይነሳና በራሱ ጥረት አዳዲስ ሥራዎችን ሠርቶ ይጨምርበትና ያድጋል፣ አዲስ ነገርን ትቶ ያልፋል። የቀደመው ትውልድ ተፈጥሮና ኑሮው ከሚያስገድደው በላይ ለሚቀጥለው ትውልድ መስዋዕት መሆን አይችልም፣ አይጠበቅበትምም። በምፅዋትና በሞግዚት አስተዳደር የሚኖር ትውልድ ለሚቀጥለው ትውልድ የሚያስተላልፈው ዕዳ ብቻ ነው፣ ዕዳን በውርስ ተሸክሞ የሚፈጠር ትውልድ ያለምርኩዝ መንቀሳቀስ አይችልም፣ ምርኩዝ ሊሆኑት የሚችሉት እነዚያው የዕዳው ባለቤቶች ናቸው። ስለዚህም ከዕዳና ከምፅዋት አዙሪት አይወጣም።”

ይህን ጠሊቅ ዕይታ የትውልድ ቅብብሎሽ አንፃራዊ ገጽታና ትችት በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ “ትውልዶች” በሚል ርዕስ መስከረም 7 ቀን 2013 ዓ.ም. ዜና  ዕረፍታቸው ከመሰማቱ ከአሥር አምስት ቀናት በፊት የከተቡት ሊቁ መስፍን ወልደ ማርያም (ፕሮፌሰር) ናቸው።

በኢትዮጵያ ዘርፈ ብዙ ጉዳዮች ላይ ሐሳባቸውን ለማንፀባረቅ ችላ የማይሉ፣ ዕውቀታቸውንና ምልከታቸውን በአደባባይ ለማስተጋባት የሚተጉ ነበሩ ፕሮፌሰር መስፍን ወልደ ማርያም።  “ነፃ ሐሳብ ለነፃ ሕዝብ” የሚል አስተምህሮ የነበራቸው ያንንም ለመተግበር ዕውንም ለማድረግ ወደ ኋላ ማለት ማፈግፈግን ዞር በል የሚሉ ናቸው ይሏቸዋል። ለሰብዓዊ መብቶች መከበር ከሦስት አሠርታት ወዲህ ኢሰመጉን በመመሥረት ያሳዩት ተላሚነት ይበልታን አስገኝቶላቸዋል።

ከዘውዳዊው ሥርዓት እስከ ወታደራዊው የደርግ መንግሥት፣ ከሕዝባዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊኩ እስከ አሁን ዘመኑ ፌዴራላዊ ሪፐብሊክ መንግሥታት  ድረስ የሽግግር ዘመኑንም ጨምሮ በገሀድ በመሔስ የሚሰማቸውን በመጣጥፍና በተለያዩ መገናኛ ብዙኃን በመግለጽ ከቀዳሚነት ይጠቀሳሉ። በተለይ ደርግ ወድቆ ኢሕአዴግ መንበረ ሥልጣኑን ሲጨብጥ በሽግግሩ ዘመን በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ከወቅቱ የሽግግር መንግሥቱ ፕሬዚዳንት አቶ መለስ ዜናዊ ጋር ክርክር የገጠሙበት መንገድም (ሌሎች ምሁራን ጨምሮ) በብዙዎች ዘንድ ይታወሳል።

በ1950ዎቹና በ1960ዎቹ በሰሜን ኢትዮጵያ የደረሰውን ድርቅና ረሃብ ተከትሎ የተፈጠረውን ቀውስ ይፋ በማድረግ የሚጠቀሱት በስሚ ስሚ ያገኙትን ሳይሆን በተለያዩ አካባቢዎች በመገኘት ያዩትን የተመለከቱትን በፎቶግራፍ ጭምር በማስደገፍ ከባልደረቦቻቸው ጋር መጣራቸው ይወሳላቸዋል። በርሳቸው አገላለጽ ‹‹ጠኔ›› የሚባለውን ረሃብ አስመልክቶ መፍትሔ ማሳያ መጽሐፍም እስከ ማዘጋጀት መድረሳቸው ገጸ ታሪካቸው ያሳያል።

 ከባህር ማዶ የቅድመና ድኅረ ምረቃ ትምህርታቸውን ካጠናቀቁ በኋላ የሥራውን ገበታ የተቀላቀሉት የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ  ዩኒቨርሲቲን ነው። በዘመኑ  ጥቂት ምሁራን ብቻ የሚያደርጉትን ለሚያስተምሩት ትምህርት የመማርያ መጽሐፍ በማዘጋጀት ረገድም ዓይነተኛ ተጠቃሽ ናቸው።

በአካዴሚያ ሕይወታቸው ለፕሮፌሰርነት የበቁበት የጂኦግራፊያ መምህርነታቸው የኢትዮጵያን መልክዓ ምድር በጥልቀት የሚያሳይ መጽሐፍን አበርክተዋል። የትምህርት  ክፍሉንም እስከ መምራት ደርሰዋል።

ፕሮፌሰር መስፍን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በነበሩበትና ጡረታ ከወጡም በኋላ ጥናታዊ ጽሑፎችንና መጻሕፍትን አሳትመዋል። የኢትዮጵያ ጥናት ዓለም አቀፍ ጉባዔን ጨምሮ በተለያዩ ዓለም አቀፍ መድረኮች ጥናቶቻቸውን አቅርበዋል። የአደባባይ ምሁር ካሰኛቸው አንዱ የተለያዩ ጽሑፎችን በማዘጋጀት በጋዜጦች፣ በመጽሔቶችና በማኅበራዊ ትስስር መድረኮች ያለመታከት ሲያካፍሉ መቆየታቸው ነበር።

በገጣሚነትም የሚታወቁት ፕሮፌሰር መስፍን በመስከረም 1967 ዓ.ም. ያሳተሟት “እንጉርጉሮ” የግጥም መድበል የኅብረተሰቡን እንጉርጉሮ  ያንፀባረቀች ናት።  ከ38 ዓመት በኋላም የአገሬው እንጉርጉሮ  ፈውስ  ባለማግኘቱም የ2005  ዓ.ም. “ዛሬም እንጉርጉሮ” በማለት አሳትመዋል።

ካዘጋጇቸውና የኅትመት ብርሃን ካገኙት መካከል “ኢትዮጵያ ከየት ወዴት፣ አደጋ ያንዣበበበት የአፍሪካ ቀንድ፣ ሥልጣን ባሕልና አገዛዝ፣ ፖሊቲካና ምርጫ፣ የክህደት ቁልቁለት፣ አገቱኒ፣ መክሸፍ እንደ ኢትዮጵያ ታሪክ፣ አድማጭ ያጣ ጩኸት፣ እንዘጭ! እምቦጭ! የኢትዮጵያ ጉዞ፣ አዳፍኔ፣ ፍርሃትና መክሸፍ፣ ዛሬም እንደ ትናንትና” ተጠቃሽ ናቸው።

በዘውዳዊ ሥርዓት የተጀመረው ፖለቲካዊ ትግላቸው ወደ ፓርቲ ሕይወት የተሸጋገረው በ1997 ዓ.ም. በተደረገው አገራዊ ምርጫ ዋዜማ ከትግል አጋሮቻቸው ጋር ባቋቋሙት ቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ፓርቲ አማካይነት ነው። ምርጫውን ተከትሎ በተፈጠረው ቀውስም ‹‹የሕገ መንግሥቱን ሥርዓት አደጋ ላይ በመጣል›› በሚል ከሌሎች ጓዶቻቸው ጋር እንዲታሰሩ ተፈርዶባቸው በይቅርታ መለቀቃቸው ይታወሳል።

ከአባታቸው አቶ ወልደ ማርያም እንዳለና ከእናታቸው ወ/ሮ ይመኙሻል ዘውዴ ሚያዝያ 15 ቀን 1922 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ የተወለዱት ፕሮፌሰር መስፍን፣ በልጅነታቸው ዘመን በ1937 ዓ.ም. ለድቁና ያበቃቸውን የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን መሠረታዊ ትምህርት ተከታትለዋል። በተፈሪ መኰንን ትምህርት ቤትም የአንደኛና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ካጠናቀቁ በኋላ ወደ ህንድ አገር በማቅናት የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ከፑንጃብ ዩኒቨርሲቲ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን በአሜሪካ ከሚገኘው ክላርክ ዩኒቨርሲቲ አግኝተዋል። ትምህርታቸውን አጠናቅቀው ከተመለሱ በኋላ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ማገልገላቸው ከመጀመራቸው በፊት በካርታና ጂኦግራፊ ኢንስቲትዩት ውስጥ ሠርተዋል።

ባደረባቸው ሕመም ሳቢያ ሕክምናቸውን ሲከታተሉ የቆዩት ፕሮፌሰር መስፍን ማክሰኞ መስከረም 19 ቀን 2013 ዓ.ም. ለረቡዕ አጥቢያ በ90 ዓመታቸው አርፈዋል። ሥርዓተ ቀብራቸውም ከሰኞ በኋላ እንደሚፈጸም የቀብሩ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል ለመገናኛ ብዙኃን መግለጻቸው ታውቋል።

ዜና ዕረፍታቸውን ተከትሎ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) በሐዘን መግለጫቸው፣ “የሐሳብ ልዕልና ምልክት፣ የሰላማዊ ትግል አርአያ፣ ላመኑበት ነገር እስከ መጨረሻቸው ሞጋች፣ ላመኑበት እውነት ብቻ የሚቆሙት ፕሮፌሰር መስፍን ወልደ ማርያም በማረፋቸው ጥልቅ ሐዘን ተሰምቶኛል፤” ብለዋል።

ከአርባ ስድስት ዓመታት በፊት በወርኃ መስከረም ካሳተሟት “እንጉርጉሮ” የግጥም መድበል ውስጥ የሞትን ምንነት ከገለጹበት ውስጥ የሚከተለው አንጓ ይገኝበታል።

ሞት ማለት:-
ሞት አለመስጋት ነው የግዴለሽ ዓለም፣
ድንጋይ ተሸክሞ በውኃ ላይ መቆም፣
ጤንነት የለበት፣ አያጠቃው ሕመም፣
ትዝታ የለበት፣ አይታይበት ሕልም፣
ቡቃያው አያሸት፣ ፍሬው አይለመልም።
ዝናብ አይዘንብበት ድርቀት ነው ዘላለም።
ማንም አይጎዳ ማንም አይጠቀም።

የሦስት ልጆች አባት የነበሩት ፕሮፌሰር መስፍን፣ በኅልፈታቸው ዋዜማ በ13ኛዋ ወር ጳጉሜን “መልካም ምኞት ለአዲስ ዓመት” በሚል ርዕስ በፌስቡክ ገጻቸው እንዲህ ተመኝተው ነበር።

“2012 ዓ.ም. ቆሻሻውን አራግፎብናል። ነገር ግን እግዚአብሔር ክረምቱን ከባድ አድርጎታል፣ እግዚአብሔር ክረምቱን ያከበደው በውስጣችንም ሆነ በላያችን የተሸከምነውን ቆሻሻ ለማጠብ እንድንችል ይሆናል። እግዚአብሔር ልባችንን በፍቅር፣ አዕምሮአችንን በዕውቀት ይሙላልን”። (ሪፖርተር)

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሽኝት ፕሮግራም ሲካሄድ

ጉዞ ወደ ቅድስት ሥላሴ
ቅድስት ሥላሴ
ሽኝት
የትውልድ ፈርጦች፤ የኢትዮጵያ አንጸባራቂ ዕንቁዎች – ፕሮፌሰር መስፍን እና ፕሮፌሰር አስራት (ማኅበራዊ ሚዲያ)

(በተለይ ካልተጠቀሰ ፎቶዎቹ በሙሉ የተወሰዱት ከኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ የማኅበራዊ ገጽ ነው)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Middle Column, News, Politics, Social Tagged With: mesfin, prof mesfin

Reader Interactions

Comments

  1. ታዛቢ says

    October 13, 2020 09:11 pm at 9:11 pm

    ለጎልጉል ምስጋናዬ ልክ የለውም!
    የኝህ ታላቅ ሰው ታሪክ እንዲህ ባጭሩ ቅልብጭ ብሎ: ግና ለትውልድ በሚተላለፍ መልክ በመዘከሩ ኮርቼባችኋለሁ!!

    Reply
  2. Mulugeta Andargie says

    October 18, 2020 07:32 am at 7:32 am

    Mulugeta Andargie

    በፕሮፍ ላይ የሰጠሃቸው ጸያፍ አስተያየትና በግጥም የላከው አስተያየት፤ ሁለቱም ተሰርዘዋል።

    አስተያየት ልኬ አላተማችሁልኝም ብለህ እንደ ሁልጊዜው እንዳታላዝን ነው ይህንን የነገርንህ።

    አርታኢ

    Reply
  3. Mulugeta Andargie says

    November 1, 2020 03:09 am at 3:09 am

    ጎልጉሌች ስለ ዘረኝነት ትዋጋላችሁ? እስቲ ፊታችሁን በመስታወት ተመልከቱት። ሞኝ የለም!! ስትፎክት ትኖራለህ እንጂ፤ ነጻ ህዝብ መሆናችንን ኣረጋግጠናል። እኔ እንደ እናንተ ኣላዝንንም።ህዝባችን ነጻ ነው። ሰርቶ፥ ለፍቶ፥ ጥሮ ግሮ ያድራል። የሃይለስላሴ መንግስት፥ የደርግ መንግስት ያሰቃየው ነበር። ያ ይመለሳል ብላችሁ የምታስቡ ከሆነ ህልም ነው። ቀሺሞች።

    Reply

Leave a Reply to ታዛቢ Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule