• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በኬንያ ስደተኞች ከተማ ልቀቁ ተባሉ

January 5, 2013 09:18 am by Editor Leave a Comment

ወቅቱ 2003 አጋማሽ ላይ ነው። ሁለት የኢህአዴግ ሰዎች ድንበር አቋርጠው ናይሮቢ ይገባሉ። በናይሮቢ አድርገው ወደ ሌላ አገር ለመኮብለል ጊዜያዊ ማረፊያ መጠነኛ ሆቴል ይከራዩና ለሁለት አንድ ላይ ያርፋሉ። አንደኛው ከሰዎች ጋር ቀጠሮ እንዳለው አስታውቆ ወደ ጉዳዩ ይሄዳል። ቀጠሮው ቦታ ቆይቶ ለጓደኛው ስልክ ሲደውል “እንዳትመጣ፣ ጓደኛህን ከተኛበት ገብተው የማይታወቁ ሰዎች ወስደውታል” የሚል መልዕክት ይደርሰዋል። ከዚያን ቀን ጀምሮ ስለጓደኛው ሰምቶ አያውቅም። እሱም አገር ቀይሮ በስደት በመንከራተት ላይ ይገኛል።

ኬንያ ሶስት ዓይነት ስደተኞች አሉ። በኢኮኖሚ ድቀት የዕለት ጉርስ ፍለጋ የሚሰደዱ፣ በፖለቲካ ሳቢያ ኢህአዴግን ሽሽት አገር ለቀው የወጡ፣ በኢህአዴግ ልዩ ተልኮ ስደተኛ መስለው ኬንያ የሚኖሩ፤ ከናይሮቢ በስልክ ለጎልጉል መረጃ የሰጡት ወገኖች እንደደሚሉት በየጊዜው እየታፈኑ ወደ አገርቤት የሚላኩ ጥቂት አይደሉም። ይህ የሚሆነው ደግሞ በኬንያ ውስጥ ኢህአዴግ እጀ ረጅም በመሆኑ ነው። በዚህም ሳቢያ ለፖለቲካ ስደተኞች እያንዳንዷ ቀን የሰቀቀን ነች። ራስን የመጠበቅ!!

የኬንያ መንግስት “ለደህንነቴ ቅድሚያ” በሚል ሰሞኑንን ያስተላለፈው መመሪያ በስደት ናይሮቢ የሚኖሩትን ወገኖች ያስደነገጣቸውም ለዚሁ ነው። በኬንያ የሚኖሩ ስደተኞች ከተማ ለቅቀው ወደ ካምፕ እንዲገቡ በተላለፈው ትዕዛዝ መሰረት መመሪያው የሚመለከታቸው ኢትዮጵያዊያን የመፍትሄ ሃሳብ የላቸውም። ግን ጭንቀታቸውን ለማሰማት ያህል ይናገራሉ።

በናይሮቢ የዓለም የስደተኞች ኮሚሽንን ውሳኔ በመጠባበቅ ላይ ካሉት ስደተኞች መካከል አንዱ ብርሃኑ በየነ ይባላል። በዝዋይ ማረሚያ ቤት ታስሮ ተገርፏል። እሱ እንደሚለው የኬንያ መንግስት ሁሉንም ስደተኞች ባንድ መነጽር ሊመለከት አይገባም። በጅምላ ከዘጠኝ አገሮች ተሰድደው ኬንያ ለገቡት ጥገኝነት ጠያቂዎች በግል የፋይል ቁጥራቸው ወደ ካምፕ እንዲገቡ መመሪያ ተላልፏል።

በአዲሱ ዓመት ግርግር ጉዳዩ ተጓተተ እንጂ መመሪያው ተግባራዊ መሆኑ አይቀሬ ነው። የስደት ማመልከቻቸውን አስገብተው በተባበሩት የስደተኞች ኮሚሽን እውቅና ናይሮቢ እንደፍጥርጥራቸው ተቀምጠው ጉዳያቸውን የሚከታተሉም ሆኑ፣ በስደት ካምፕ ያሉ ኢትዮጵያዊያን ከቀላል የርስ በርስ ጸብ በስተቀር በወንጀል፣ በግድያና በጸያፍ ተግባር አይታወቁም። ከዚህም በላይ ለናይሮቢ ነዋሪዎች ስጋት የሚሆኑበት አንድም አግባብ እንደሌለ ብርሃኑ ያስረዳል።

በኬንያ ስደት ካምፖች ሙቀታቸው ከፍተኛ፣ ለመኖሪያ የማያመቹ፣ ለአካባቢ ወለድ በሽታዎች የተጋለጡ፣ በቂ የመኖሪያ ግብአት ያላሟሉ ከመሆናቸው በላይ ትልቁ ችግር የደህንነት እንደሆነ ያመለከተው ብርሃኑ አብዛኞችን ስጋት ላይ ስለጣለው ጉዳይ “ተመሳስለው በስደተኛ ስም ኬንያ የገቡት የኢህአዴግ የስለላ ሰዎች በየቀኑ ሰዎችን ያድናሉ። ወደ ኢትዮጵያ ይወስዳሉ። በዚህ መልኩ የታፈኑ በርካታ ናቸው። አንድ ላይ ተሰባስበን እንዴት እንቀመጣለን? ይህ እጅግ አሳሳቢና ከፍተኛ መዘዝ የሚያስከትል የሰብአዊ መብት ጥሰት ነው” ሲል የኬንያ መንግስት ውሳኔውን ሊያጤን እንደሚገባው ያሳስባል።

ይህ ብቻ አይደለም በኬኒያ ያለው ሙስናም ሌላው ስጋት ነው። “በኬንያ ገንዘብ ካለ ሁሉንም ማድረግ ይቻላል። ኢህአደግ ገንዘብ አለው። ገንዘብ ከተከፈለ ዋስትናችንን አሳልፎ የመስጠት ውሳኔም ሊወሰን ይችላል” የሚለው ግርማ ጉተማ “ኦነግን ፍርሃቻ በየስርቻው የሚንቀሳቀሰው ኢህአዴግ ይጥቀመው እንጂ ማንኛውንም ነገር የማድረግ ሞራል ስላለው ዋስትናችን የተመናመነ ያህል ይሰማኛል” ይላል።

ሁሉም እንደሚሉት የኬንያ መንግስት ውሳኔውን ተግባራዊ ከማድረጉ በፊት ኢትዮጵያዊያን ወገኖች ድምጻቸውን በያሉበት ሆነው ሊያሰሙ ይገባል። በየአቅጣጫው ጉዳዩን በማስመልከት ለኬንያ መንግስትና ለሚመለከታቸው ክፍሎች የስጋቱን ደረጃ ማሳወቅ ለነገ የማይባል አንገብጋቢ ጉዳይ እንደሆነ አበክረው ያስረዳሉ። በኬንያ ከደቡብ ኢትዮጵያ፣ ከአማራና ከኦሮሚያ የሚሰደዱ ኢትዮጵያውያን ቁጥር አብላጫውን ቁጥር ይይዛል።

Dadaab refugee camp, Kenya
ዳዳብ የስደተኞች ካምፕ ኬኒያ ሐምሌ 2003(ፎቶ:AlertNet)

በኬንያ በተደጋጋሚ በደረሰ የቦንብ ጥቃት ሳቢያ ዜጎች ከስደተኛ የሶማሌ ዜጎች ላይ ጥቃት መሰንዘራቸውና፣ የሶማሌ ዜጎችን በመቃወም የኬንያዊያን ጥያቄ ገፍቶ በመምጣቱ መንግስት ሁሉም ስደተኞች ወደ ካምፕ እንዲገቡ የሚያስገድድ መመሪያ አውጥቷል። የኬንያ የመከላከያ ሃይል በሶማሌ የአልቃይዳንና የአልሸባብን ሃይል ከዩጋንዳ፣ ከብሩንዲና ከኢትዮጵያ ሰራዊት ጋር በመሆን ማጥቃቱ ለቦንብ አደጋው እንደ ምክንያት ቢገለጽም፣ የኬንያ መንግስት ውሳኔውን ያሳለፈው አጠቃላይ አገሪቱ ውስጥ ለገቡት ስደተኞች ሁሉ ነው።

በዓለም ትልቁ የሚባለውና አብዛኛዎቹ ከሶማሊያ የሚመጡት ስደተኞች የሚገኙበት የዳዳብ ካምፕ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ስደተኞችን የሚገኙ በመሆናቸው ተጨማሪ ስደተኞችን ሊጨምር ባይችልም ሌሎች አዳዲስ ካምፖችን በማሰራት ስደተኞችን ወደዚያው ለማጎር እየታሰበ እንደሆነ ከኬኒያ የሚወጡ ዜናዎች ይጠቁማሉ፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule