• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በኬንያ ስደተኞች ከተማ ልቀቁ ተባሉ

January 5, 2013 09:18 am by Editor Leave a Comment

ወቅቱ 2003 አጋማሽ ላይ ነው። ሁለት የኢህአዴግ ሰዎች ድንበር አቋርጠው ናይሮቢ ይገባሉ። በናይሮቢ አድርገው ወደ ሌላ አገር ለመኮብለል ጊዜያዊ ማረፊያ መጠነኛ ሆቴል ይከራዩና ለሁለት አንድ ላይ ያርፋሉ። አንደኛው ከሰዎች ጋር ቀጠሮ እንዳለው አስታውቆ ወደ ጉዳዩ ይሄዳል። ቀጠሮው ቦታ ቆይቶ ለጓደኛው ስልክ ሲደውል “እንዳትመጣ፣ ጓደኛህን ከተኛበት ገብተው የማይታወቁ ሰዎች ወስደውታል” የሚል መልዕክት ይደርሰዋል። ከዚያን ቀን ጀምሮ ስለጓደኛው ሰምቶ አያውቅም። እሱም አገር ቀይሮ በስደት በመንከራተት ላይ ይገኛል።

ኬንያ ሶስት ዓይነት ስደተኞች አሉ። በኢኮኖሚ ድቀት የዕለት ጉርስ ፍለጋ የሚሰደዱ፣ በፖለቲካ ሳቢያ ኢህአዴግን ሽሽት አገር ለቀው የወጡ፣ በኢህአዴግ ልዩ ተልኮ ስደተኛ መስለው ኬንያ የሚኖሩ፤ ከናይሮቢ በስልክ ለጎልጉል መረጃ የሰጡት ወገኖች እንደደሚሉት በየጊዜው እየታፈኑ ወደ አገርቤት የሚላኩ ጥቂት አይደሉም። ይህ የሚሆነው ደግሞ በኬንያ ውስጥ ኢህአዴግ እጀ ረጅም በመሆኑ ነው። በዚህም ሳቢያ ለፖለቲካ ስደተኞች እያንዳንዷ ቀን የሰቀቀን ነች። ራስን የመጠበቅ!!

የኬንያ መንግስት “ለደህንነቴ ቅድሚያ” በሚል ሰሞኑንን ያስተላለፈው መመሪያ በስደት ናይሮቢ የሚኖሩትን ወገኖች ያስደነገጣቸውም ለዚሁ ነው። በኬንያ የሚኖሩ ስደተኞች ከተማ ለቅቀው ወደ ካምፕ እንዲገቡ በተላለፈው ትዕዛዝ መሰረት መመሪያው የሚመለከታቸው ኢትዮጵያዊያን የመፍትሄ ሃሳብ የላቸውም። ግን ጭንቀታቸውን ለማሰማት ያህል ይናገራሉ።

በናይሮቢ የዓለም የስደተኞች ኮሚሽንን ውሳኔ በመጠባበቅ ላይ ካሉት ስደተኞች መካከል አንዱ ብርሃኑ በየነ ይባላል። በዝዋይ ማረሚያ ቤት ታስሮ ተገርፏል። እሱ እንደሚለው የኬንያ መንግስት ሁሉንም ስደተኞች ባንድ መነጽር ሊመለከት አይገባም። በጅምላ ከዘጠኝ አገሮች ተሰድደው ኬንያ ለገቡት ጥገኝነት ጠያቂዎች በግል የፋይል ቁጥራቸው ወደ ካምፕ እንዲገቡ መመሪያ ተላልፏል።

በአዲሱ ዓመት ግርግር ጉዳዩ ተጓተተ እንጂ መመሪያው ተግባራዊ መሆኑ አይቀሬ ነው። የስደት ማመልከቻቸውን አስገብተው በተባበሩት የስደተኞች ኮሚሽን እውቅና ናይሮቢ እንደፍጥርጥራቸው ተቀምጠው ጉዳያቸውን የሚከታተሉም ሆኑ፣ በስደት ካምፕ ያሉ ኢትዮጵያዊያን ከቀላል የርስ በርስ ጸብ በስተቀር በወንጀል፣ በግድያና በጸያፍ ተግባር አይታወቁም። ከዚህም በላይ ለናይሮቢ ነዋሪዎች ስጋት የሚሆኑበት አንድም አግባብ እንደሌለ ብርሃኑ ያስረዳል።

በኬንያ ስደት ካምፖች ሙቀታቸው ከፍተኛ፣ ለመኖሪያ የማያመቹ፣ ለአካባቢ ወለድ በሽታዎች የተጋለጡ፣ በቂ የመኖሪያ ግብአት ያላሟሉ ከመሆናቸው በላይ ትልቁ ችግር የደህንነት እንደሆነ ያመለከተው ብርሃኑ አብዛኞችን ስጋት ላይ ስለጣለው ጉዳይ “ተመሳስለው በስደተኛ ስም ኬንያ የገቡት የኢህአዴግ የስለላ ሰዎች በየቀኑ ሰዎችን ያድናሉ። ወደ ኢትዮጵያ ይወስዳሉ። በዚህ መልኩ የታፈኑ በርካታ ናቸው። አንድ ላይ ተሰባስበን እንዴት እንቀመጣለን? ይህ እጅግ አሳሳቢና ከፍተኛ መዘዝ የሚያስከትል የሰብአዊ መብት ጥሰት ነው” ሲል የኬንያ መንግስት ውሳኔውን ሊያጤን እንደሚገባው ያሳስባል።

ይህ ብቻ አይደለም በኬኒያ ያለው ሙስናም ሌላው ስጋት ነው። “በኬንያ ገንዘብ ካለ ሁሉንም ማድረግ ይቻላል። ኢህአደግ ገንዘብ አለው። ገንዘብ ከተከፈለ ዋስትናችንን አሳልፎ የመስጠት ውሳኔም ሊወሰን ይችላል” የሚለው ግርማ ጉተማ “ኦነግን ፍርሃቻ በየስርቻው የሚንቀሳቀሰው ኢህአዴግ ይጥቀመው እንጂ ማንኛውንም ነገር የማድረግ ሞራል ስላለው ዋስትናችን የተመናመነ ያህል ይሰማኛል” ይላል።

ሁሉም እንደሚሉት የኬንያ መንግስት ውሳኔውን ተግባራዊ ከማድረጉ በፊት ኢትዮጵያዊያን ወገኖች ድምጻቸውን በያሉበት ሆነው ሊያሰሙ ይገባል። በየአቅጣጫው ጉዳዩን በማስመልከት ለኬንያ መንግስትና ለሚመለከታቸው ክፍሎች የስጋቱን ደረጃ ማሳወቅ ለነገ የማይባል አንገብጋቢ ጉዳይ እንደሆነ አበክረው ያስረዳሉ። በኬንያ ከደቡብ ኢትዮጵያ፣ ከአማራና ከኦሮሚያ የሚሰደዱ ኢትዮጵያውያን ቁጥር አብላጫውን ቁጥር ይይዛል።

Dadaab refugee camp, Kenya
ዳዳብ የስደተኞች ካምፕ ኬኒያ ሐምሌ 2003(ፎቶ:AlertNet)

በኬንያ በተደጋጋሚ በደረሰ የቦንብ ጥቃት ሳቢያ ዜጎች ከስደተኛ የሶማሌ ዜጎች ላይ ጥቃት መሰንዘራቸውና፣ የሶማሌ ዜጎችን በመቃወም የኬንያዊያን ጥያቄ ገፍቶ በመምጣቱ መንግስት ሁሉም ስደተኞች ወደ ካምፕ እንዲገቡ የሚያስገድድ መመሪያ አውጥቷል። የኬንያ የመከላከያ ሃይል በሶማሌ የአልቃይዳንና የአልሸባብን ሃይል ከዩጋንዳ፣ ከብሩንዲና ከኢትዮጵያ ሰራዊት ጋር በመሆን ማጥቃቱ ለቦንብ አደጋው እንደ ምክንያት ቢገለጽም፣ የኬንያ መንግስት ውሳኔውን ያሳለፈው አጠቃላይ አገሪቱ ውስጥ ለገቡት ስደተኞች ሁሉ ነው።

በዓለም ትልቁ የሚባለውና አብዛኛዎቹ ከሶማሊያ የሚመጡት ስደተኞች የሚገኙበት የዳዳብ ካምፕ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ስደተኞችን የሚገኙ በመሆናቸው ተጨማሪ ስደተኞችን ሊጨምር ባይችልም ሌሎች አዳዲስ ካምፖችን በማሰራት ስደተኞችን ወደዚያው ለማጎር እየታሰበ እንደሆነ ከኬኒያ የሚወጡ ዜናዎች ይጠቁማሉ፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule