• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ልጄን ገድለው በማዳበሪያ አመጡልኝ” እናት

November 5, 2016 02:47 am by Editor Leave a Comment

የለቅሶ ሳግ በያዘው አንደበት የመረረ ሃዘን ይሰማል። ተናጋሪዋ የሚሰሩት ድራማ ወይንም ዘጋቢ ፊልም ሳይሆን በትክክል የደረሰባቸውን ነው። የልጃቸው አስከሬን እንደ ምናምንቴ በማዳበሪያ ተደርጎ ነው የተሰጣቸው። ልብ ይነካል። ያማል። ጉዳዩ ከሃዘንም በላይ ይሆናል። አንድ ልጃቸው “መመኪያዬ” የሚሉት ተገደለባቸው፤ ሌላኛው ክፉኛ ተደብድቦ ታሟል፤ ሁለቱ ታስረዋል። እኚህ የ65 ዓመት አዛውንት ሲያልቅ አያምር ሆነና ባዶ ሆኑ።

“ልጄን ገድለው በማዳበሪያ አመጡልኝ” አሉ። አስከትለው አስከሬኑ መበላሸቱንና ደም ይፈሰው እንደነበር ገለጹ። ወግ አይቀር ተቀበረ። አሁን አሁን “ወዴት እየሄድን ነው” ከማለትም ያለፈ ይመስላል። ስለ ጉዳዩ የተጠየቁት የወረዳው አስተዳዳሪ “በአሁኑ ሰዓት እንዲህ ያለ ችግር የለም” ማለታቸው፣ ዋና አስተዳዳሪውና የወረዳው ፖሊስ አዛዥ ምላሽ ለመስጠት አለመፈለጋቸው ሌላው አስዛኝ ጉዳይ ነው።

በምስራቅ ሸዋ ዞን፣ ቦሰት ወረዳ ቆምቤ ጉግሳ መንደር ነዋሪ የሆኑት ወ/ሮ ሎሚ ዋቀዮ የ65 ዓመት፣ ባለቤታቸው የ74 ዓመት አዛውንት ናቸው። እኒህ ሁለት አዛውንቶች የደረሰባቸው ሃዘንና ግፍ ኢህአዴግን ለሚደግፉም ሆነ ለሚቃወሙ ለሁሉም ልብ የሚሰብር ነው። የወ/ሮ ሎሚ ዋቀዮን ቤት መበተን ጀግንነትም አይሆንም። እሳቸው ላይ የደረሰው ሃዘን በፖለቲካ ሚዛንና ትርፍ ማየትም አግባብ አይሆንም።

“የሞተ አይመለስም” የሚሉት እናት “የተበታተኑትን ልጆቼን መልሱልኝ” በሚል ጠይቀዋል። እናም የገዢዎች ምላሽ ምን ይሆን? የሃላፊዎችስ ምላሽ ምን ይሆን?

ቀደም ሲል በወለጋ አንድ እናት የልጇ አስከሬን ላይ እንድትቀመጥ ተደርጎ የተፈጸመውን ያስታወሰው ይህ ዜና፣ አፋጣኝ ምላሽ የሚያሻው ሆኖ ተገኝቷል። የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ከታወጀና ከመታወጁ በፊት በአገሪቱ ታሪክ ክፉ የተባሉ ተግባራት ተፈጽመዋል። ይህ የሚቆምበትና ሁሉም ነገር በህግ የሚታይበት አግባብ እያለ እንዲህ አይነት የከፋ ድርጊት መፈጸም በየትኛም ጊዜ ዋጋ የሚያስከፍል፣ ለማንኛውም ወገን ገድል ሆኖ የማይቀመጥ፣ ነውና ሁሉንም ባግባቡ ማስተናገድ፣ አግባብ እንደሆነ አዛውንቶችና ነገሮችን በሰከነ መንፈስ የሚመለከቱ ይመክራሉ። (ምንጭ: ዛጎል ዜና)

የቪኦኤ ያጠናቀረው ዘገባ ከዚህ የሚከተለው ነው።

“የሞተው ልጄ ሞቷል፤ ያሉትን መልሱልኝ” ወ/ሮ ሎሚ ዋቀዮ

የአሜሪካ ድምጽ ያነጋገራቸው በምስራቅ ሸዋ ዘን ቦሰት ወረዳ የሚገኙ ወ/ሮ ሎሚ ዋቀዮ የተባሉ እናት አንድ ልጃቸው እንደተገደለ ሁለቱ እንደታሰሩና አንዱ በእጅጉ መደብደቡን ለአሜሪካ ድምጽ ተናግረዋል። በኢትዮጵያ ለስድስት ወር አስቸኳይ ጊዜ ከታወጀ አንድ ወር ሊሞላው ጥቂት ቀናት ይቀሩታል። ይህ ዐዋጅ ይፋ ከተደረገ በኋላ ሰዎች ከየቦታው እየተለቀሙ እንደሚታሰሩ በተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎችና በሰባዊ መብት ተሟጋቾች ጭምር ሲነገር ቆይቷል።

ወ/ሮ ሎሚ ዋቀዮ በምስራቅ ሸዋ ዞን ቦሰት ወረዳ ቆምቤ ጉግሳ በተባለ መንደር ነዋሪ እንደሆኑ ይናገራሉ። የ65 ዓመት አዛውንት ናቸው። ባለቤታቸው ደግሞ የ74 ዓመት አዛውንት መሆናቸውን ገልጸውልናል። እንደ ወ/ሮ ሎሚ ገለጻ አራት ልጆች ነበራቸው። አቢቲ ደጃሳ የተባለ የ30 ዓመት አርሶ አደር ልጅ ነበራቸው። ደምሴ ደቻሳ ወይም ደሜ እያሉ በቁልምጫ የሚጠሩት የ22 ዓመት ልጃቸው ደግሞ “አዳማ ሄዶ ሥራ ፍለጋ ሲንከራተት ተይዞ ታስሯል” ይላሉ። የት እንደታሰረ ግን አያውቁም።

ንጉሴ ደቻሳ የተባለው ልጃቸው ደግሞ ከቤት ውስጥ ተደብድቦ ተወስዶ ወለንጪቲ ተወስዶ መታሰሩን ይናገራሉ። ወ/ሮ ሎሚ በለቅሶ በታጀበ ድምጽ ረዳታቸው የ30 ዓመቱ ወጣት አቢቲ ደቻሳ ለስብሰባ ይፈለጋል ተብሎ ከቤታቸው ከተወሰደ በኋላ ጥቅምት 12 ቀን 2009 ዓ.ም አስክሬን እንደመጣላቸው ይናገራሉ።

የልጃቸው ለቅሶ ባይመጣና ቤታቸው ሐዘን ባይገባ ኖሮ ወለንጪቲ ታስሯል የተባለውን ልጃቸውን ንጉሴን ሄደው ይጠይቁት እንደነበር ገልጸዋል። “አንዱን በሞት አጣሁ። አሁን አንድ ሰው አብሮኝ የለም። ቤቴ ባዶውን ቀርቷል። ደካማ ነኝ” የሚሉት ወ/ሮ ሎሚ ዋቀዮ “የሞተው ልጄ ሞቷል፤ ያሉትን መልሱልኝ” ሲሉ ይጠይቃሉ። የወረዳው ምክትል አስተዳዳሪ አቶ መሐመድ ይህን በተመለከተ የደረሰን ሪፖርት የለም ብለዋል። (ፎቶ: New York Daily News A woman mourns during the funeral of Tesfu Tadese Biru, 32, a construction engineer who died during a stampede after police fired warning shots at an anti-government protest in Bishoftu the day before.)

የአሜሪካ ድምጽ የኦሮመኛ ቋንቋ ዝግጅት ባልደረባ ጃለኔ ገመዳ ያጠናቀረችውን ዘገባ በጽዮን ግርማ እዚህ ላይ በድምጽ አቅርባዋለች።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Social Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule