• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በስደትም መሰለል – በኖርዌይ ኢትዮጵያውያን ተቃውሞ አሰሙ

April 14, 2014 08:37 pm by Editor 1 Comment

የኢህአዴግን የስለላ መዋቅርና አካሄድ አስመልክቶ እየወጡ ያሉ መረጃዎች ተበራክተዋል። ኢህአዴግ ራሱን እንደሚስለው ዓይነት ድርጅት ሳይሆን በሰብዓዊ መብት አያያዝ ጉድለት ያለበት፣ በሚዲያ ነጻነት ኋላ ቀር፣ የተቃዋሚ ፖለቲከኞችን በማሳደድ ግንባር ቀደም፣ አፋኝ ህግ በማውጣትና በማሸማቀቅ ወደር የማይገኝለት፣ ለሚያወጣው ህግና ደንብ የማይገዛ፣ የውስጥ ችግሩ ታይቶ በማይታወቅ መጠን ዜጎችን ለስደት እየዳረገ እንደሆነ እየተመሰከረበት ነው።

ኦባንግ ሜቶ
ኦባንግ ሜቶ

ኢህአዴግን ሸሽተው አገር ለቀው የተሰደዱ በስደት ምድርም ኢህአዴግ እየተፈታተናቸው እንደሆነ መግለጽ ከሰነበቱ ቆይቷል። በአሜሪካ፣ በካናዳ፣ በጀርመን፣ በስዊድንና በእንግሊዝ አገር ስደተኞችን በመሰለል ተግባር ላይ የተሰማሩ “የስደተኛ ሰላዮች” በስፋት ስለመኖራቸው መረጃ ማቅረብ እንደሚችሉ የሚገልጹ ጥቂት አይደሉም። የተለያዩ ድርጅቶች በዚህ ጉዳይ ምን ያህል እንደገፉበት መረጃ ባይወጣም አቶ ኦባንግ ሜቶ የሚመሩት የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ስራውን ያገባቸዋል ከሚላቸው ክፍሎች ጋር እየሰራ እንደሆነ በዚሁ መድረክ መገለጹ ይታወሳል። በወቅቱ አቶ ኦባንግ “ስደተኛ ሆኖ ስደተኛን መሰለል በህግ የተከለከለ ወንጀል ነውና በዚህ ጉዳይ ርህራሄ ሊኖር አይችልም” ነበር ያሉት።

ማርች 11 ቀን በኖርዌይ የኢትዮጵያ ስደተኞች ማህበር አስተባባሪነት ሰላማዊ ሰልፍ ተካሂዶ ነበር። በሰላማዊ ሰልፉ ላይ የፓርላማ ተወካይ፣ የኖአስና/NOASና ዘረኝነትን የሚቃወመው ድርጅት መሪ ተገኝተው ነበር። በሰላማዊ ሰልፉ ተገኝተው ንግግር ካደረጉት መካከል ወ/ት የሺሃረግ በቀለ ይጠቀሳሉ። በኖርዌይ የኢትዮጵያ ስደተኞች ማህበር ጸሐፊ ወ/ት የሺሃረግ በቀለ “እነሱ አገር ቤትም አገር አላቸው፤ በስደትም አገር አላቸው” በማለት ነበር ለጎልጉል አስተያየታቸውን መስጠት የጀመሩት።

yeshihareg
የሺሃረግ በቀለ

በሰልፉ ላይ ካቀረቡት ንግግር በተጨማሪ ለጎልጉል አስተያየታቸውን የሰጡት ጸሐፊዋ፣ ስደተኞች ሁሉ አንድ አይደሉም። “ሆን ተብሎ የስደት መረጃና ማስረጃ ማመልከቻው ተመቻችቶላቸው የሚላኩ የወያኔ ቅጥረኛ ሰላዮች አሉ። እነሱ ባለሁለት አገር ናቸው። እኛ አንድም አገር የለንም” ብለዋል። ይህንን ጉዳይ አቅም በፈቀደ ሁሉ ማህበሩ ከአባላቱና ድጋፍ ከሚሰጡት ሁሉ ጋር በመሆን ከዳር እንደሚያደርሰው ገልጸዋል።

“ልብ እንበል” በማለት አስረግጠው የገለጹት ስለ ሁለተኞቹ ስደተኞች ነው። ስርዓቱ ባለው የግፈኛነት፣ የዘረኛነት፣ የከፋፋይነት፣ የዴሞክራሲና የነጻነት እጦት የገፋቸው እውነተኛ ስደተኞች ባግባቡ መልስ ያለማግኘታቸው ጉዳይ ነው። “እነዚህ እውነተኛ ስደተኞች እኔን ጨምሮ አገር የለንም” ሲሉ አገር አልባ የመሆንን ስሜት ይገልጻሉ። ወ/ት የሺሃረግ የኖርዌይ ሚዲያዎችና በስለላ ተግባር የተሰማሩ “ስደተኞች” እንዳሉ በይፋ ቢናገሩም መንግሥት መልስ አለመስጠቱ ቢያሳዝናቸውም ማህበራቸው ትግሉን ይበልጥ እንዲገፋበት እንዳደረገው ነው የሚናገሩት።

የዲሞክራሲ ለውጥ ድጋፍ ሰጪ በኖርዌይ ተወካይ በሰላማዊ ሰልፉ ላይ ያረጋገጡትን በመጥቀስ ወ/ት የሺሃረግ የትግሉን መደጋገፍ አመላክተዋል። ድጋፍ ሰጪው መረጃ የማሰባሰብ ስራውን ማጠናቀቁን ማረጋገጡ፣ የስደት ከለላ ካገኙ በኋላ በስለላ የተሰማሩትን ክፍሎች አደባባይ ለማውጣት የሚደረገውን ትግል እንደሚያፋጥነው ከምስጋና ጋር እምነታቸውን ገልጸዋል።

3ማህበራቸው ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ባሉበት ሁሉ ወኪሎችን በመሰየም የግንኙነት መረብ መፍጠሩን ያመለከቱት ጸሐፊዋ፣ የግንኙነት ሰንሰለቱ መረጃዎችን በቅርብ ለመሰብሰብ እንደሚረዳ አስታውቀዋል። ላለፉት ሰባት ዓመታት የስደት ማመልከቻቸው አዎንታዊ መልስ እንዳላስገኘላቸው የጠቆሙት ወ/ት የሺሃረግ፣ “እንደ እኔ አይነቶች ብዙ ነን። ከኔም የሚብሱ አሉ። ከሚደርስብን የማህበራዊ ችግር በተደራቢ ካገራችን እንድንባረር ያደረጉን ሰዎች እዚህም እረፍት ሊነሱን አይገባም። አገር አልባ መሆን ያሳዝናል። እዚህ ኖርዌይ የተወለዳችሁ ወገኖችም ብትሆኑ ስደተኞች ናችሁና በመረጃ ማሰባሰቡ ስራ ተባበሩን” ሲሉ ጥሪ አስተላልፈዋል። ቀደም ሲል ለተባበሩትም ምስጋና አቅርበዋል። ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ ሙያዊ ምክርም ሆነ አግባብነት ያለው አስተዋጽዖ ለማበርከት ለሚፈልጉ ሁሉ ማህበራቸው በሩ ክፍት እንደሆነም ተናግረዋል።

በኖርዌይ የኢትዮጵያዊ ኮሚኒቲ ሊቀመንበር አቶ ፋሲል አለባቸው በበኩላቸው በተጠቀሰው ቀን ለተደረገው ሰላማዊ ሰልፍ ሙሉ ድጋፍ እንደሚሰጡ ገልጸዋል። “ሆን ተብሎ የስደት መረጃና ማስረጃ ተመቻችቶላቸው የሚመጡት ሰላዮች የስደት ሂደቱን በማበላሸት እውነተኛ ስደተኞች የከለላ ምላሽ እንዳይሰጣቸው ያደርጋሉ። በዚህ ዜጎች ተጎድተዋል” ሲሉ ለጎልጉል ገልጸዋል።

“እነዚሁ የተመቻቸላቸው ስደተኞች መልስ ካገኙ በኋላ ሆን ብለው ወደ አገራችን መመለስ እንፈልጋለን በማለት የስደተኛ ጉዳይ ለሚያስተናግዱት ክፍሎች የተሳሳተ መረጃ በመስጠት የሌሎች ስደተኞችን ጉዳይ በማበላሸት ስራ ይሳተፋሉ” የሚሉት አቶ ፋሲል አንዳንዴም የተሳሳተ መረጃና የተሳሳተ ምክንያት እንዳቀረቡ በመግለጽ እውነተኛ ስደተኞች ላይ ተጽዕኖ ሊያሳርፍ የሚችል ተግባር እንደሚፈጽሙ አመልክተዋል።2

ከዚህ በተለየ መልኩ ገንዘብ በመላክ /በሃዋላ/ ስራ የተሰማሩ ሰዎች እንዳሏቸው የሚገልጹት አቶ ፋሲል፣ “ወያኔዎቹ ገንዘብ በመላክ ስራ ባሰማሯቸው ሰዎች አማካይነት አገር ቤት ያሉትን ቤተሰቦች በመለየት እንደሚያስፈራሩ ይታወቃል” ሲሉ የትግሉን አስፈላጊነትና ከስደተኞች ማህበር ጥሪ ጎን ስለመቆም ይናገራሉ።

ኮሚኒቲው ለወገኖቹ ጉዳይ ዘወትር እንደሚያደርገው ሁሉ አሁን ለሚደረገው ትግል ከድጋፍ መስጠት ባለፈ አብሮ ለመስራት ዝግጁ እንደሆነ ያሳሰቡት አቶ ፋሲል፣ ማንም ቢሆን ለህግ ሊገዛ እንደሚገባ በሚያስገድድ ስራ ላይ መሰማራት እንደሚኖርበት አመላክተዋል። በማያያዝም አሁን ወደ ዩኒቨርሲቲዎች፣ ወደ ማህበረሰቡ፣ ወደ አክቲቪስቶችና አቅም ያላቸውን ክፍሎች ግንዛቤ የማስጨበትና ጉዳዩን አጀንዳ አድርጎ የመትከል ስራ ላይ ትኩረት ተደርጎ ስራው እንደሚሰራ አስረድተዋል።

ወ/ት የሺሃረግ የመረጃ ማሰባሰቡ ስራ ሲጠናቀቅ ጉዳዩን ከኖርዌይ የፍትህ ተሟጋች አካላት ጋር በመሆን አስቀድሞ ለፍትህ ሚኒስትር፣ በመቀጠልም በየደረጃው ለሚመለከታቸው ክፍሎችና ለዓለም አቀፍ ተቋማት የማሳወቁ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ለጎልጉል ተናግረዋል።

4በሰላማዊ ሰልፉ የተለያዩ ከተሞች የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና ሃሳቡን የደገፉ ተገኝተዋል። አቶ መለስ ለመጨረሻ ጊዜ ኖርዌይ በመጡ ጊዜ የተፈጠረውን ጉዳይ በማስታወስ የስደተኞች ማህበር ቢዘገይም አሁን የደረሰበት ደረጃ ሊበረታታ እንደሚገባ የጠቆሙ አሉ። ስቴንሻዬር የስደተኞች ካምፕ “ስደተኛ” ተብሎ ተመዝግቦ የነበረ እብድ ወጣት አብረውት ካምፕ የሚኖሩ አገር ቤት ያለውን ስርዓት በመቃወም ለህዝብ ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራ ሲሰሩ አብሯቸው ይሳተፍ ነበር። ሲሰለፉና ህወሃትን ሲያወግዙ፣ ኢህአዴግን ሲቃወሙ፣ አብሮ በመሆን እየተቃወመ ቪዲዮ ይቀርጽ ነበር። በመጨረሻ በድንገት ተነስቶ አገር ቤት ተመለሰ።

የልጁ በድንገት መሰወር ያሳባቸው የካምፑ ነዋሪዎች ሲያጣሩ በስም የጠቀሱት ሰው አዲስ አበባ መመለሱ ተረጋገጠ። ከወራት በኋላ አቶ መለስ ኦስሎ ሲመጡ ይኸው ሰው ኦስሎ ተገኘ። በማለት የጠቆሙት ክፍሎች ይህንን ጉዳይ ፖሊስ እንደሚያወቀው፣ ማመልከቻ እንደገባለት አብረውት የነበሩት አሁን ድረስ በስጋት ላይ እንዳሉ ይገልጻሉ።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. zeraer says

    April 16, 2014 03:16 pm at 3:16 pm

    ***ኩክ ማውጫ***
    …የእኛ ሀገረ ገዢ!…
    የየዋህ ህዝብ እንባ ሀዘን እንጉርጉሮ
    የዘወትር ዋይታ ብሶትና እሮሮ
    እራፊ ,ማይሰማ ባላንቴና ጀሮ
    ባይሆንማ ኖሮ ሳትጠልቅ ጀምበር
    ረሃብ እና ችጋር አፈር በልተው ነበር
    …የእኛ ሀገር ገዢዎች…
    የስልጣንን እርካብ ወጥተው የማይወርዱ
    የህዝብ አቤቱታ መስማት የማይወዱ
    …ለምድን ነው ቢባል?
    እኔን እንደገባኝ ሁሉ አፈቀላጤ
    ጀሮ ታምቡራቸው!
    ሳይቋጥር አይቀርም ትንሽ ኩክ ቢጤ
    ወሬ አፈናፋኙ ጀሮ ጠቢው ሁላ
    በጀሮ ታምቡሩ ኩክ ነው የሞላ
    …ይህም ስለሆነ!…
    የፍትህ ያለህ፣የነፃነት ያለህ
    የምግብ ያለህ፣ የውሃ ያለህ
    የመብራት ያለህ፣የመሪ ያለህ
    ያገር ያለህ ብለን ሰልፍ ከምንወጣ
    እኛው ተመካክረን ሌላ መፍትሄ እናምጣ

    …እንደኔ እንደኔ ግን!…
    ኑ! ስሙኝ አንሰማም መጋፈጡን ትተን
    በአንድነት ተባብረን አውጫጭኝ አውጥተን
    በካዝናቸው ላይ የጎደለ ሞልተን
    ለመሪዎቻችን እናድርግ እገዛ
    ጀሮ መቧጠጫ ኩክ ማውጫ እንግዛ፡፡

    ዘቢ
    እስኪ ለግጥሙ እናንተ ከዚህ የተሻለ ርእስ ስጡት?

    Reply

Leave a Reply to zeraer Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “የገቡበት ገብተን አንድ ሰው አናስቀርም – በተለይ አመራሩን” ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ February 15, 2021 11:46 pm
  • የትግራይ ገበሬና የከተማ ነዋሪ በሠራዊታችን ላይ አንድ ጥይት አልተኮሰም – ሪር አድሚራል ክንዱ February 4, 2021 01:51 pm
  • ኢንተርፖል፤ የህወሃት ሳምሪዎች የማይካድራ ጭፍጭፋ ከቦኮሃራም የከፋ ነው February 4, 2021 11:10 am
  • ጄኔራሎች “ተገድለዋል” በሚል የሀሰት መረጃ ሲያሰራጭ የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ February 4, 2021 08:48 am
  • በትግራይ ክልል በሴቶች ላይ ተፈጸመ የተባለውን ጥቃት የሚያጣራ ግብረ ኃይል መቀሌ ገባ February 3, 2021 12:06 pm
  • ፓርቲዎች የምርጫ መወዳደሪያ ምልክቶቻቸውን ወሰዱ February 3, 2021 10:29 am
  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule