• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኢህአዴግ ኅብረ ብሔር ፓርቲ ሲሆን ኤፈርትና ሚድሮክ ይዋሃዳሉ?

April 1, 2016 06:51 am by Editor 4 Comments

ኢህአዴግን ወደ ኅብረ ብሔር ፓርቲ የማሸጋገር ሥራ እየተሰራ መሆኑንን ሃይለማርያም ደሳለኝ የአገሪቱን “ምሁራን” ባናገሩበት ወቅት ፍንጭ ሠጥተዋል። የዛሬ ሰባት ዓመት ከመስከረም 5 እስከ 7 ቀን 2001 ዓ.ም ሃዋሳ ተካሂዶ በነበረ የኢህአዴግ ድርጅታዊ ጉባኤ አቶ መለስ ድርጅታቸው ወደ ብሄራዊ ፓርቲ ወይም አሃዳዊ ፓርቲ ስለመሸጋገሩ እየተጠና መሆኑንን ተናገረው በቀጣዩ ጉባኤ ሪፖርቱ እንደሚቀርብ ቃል ገብተው ነበር። ጥያቄው ዝም ብሎ የቀረበ ሳይሆን ታስቦበትና ከዚህ ቀደም የተሰጠውን መልስ በማስታወስ ነበር። ይህ የሚያሳየው አሃዳዊ ፓርቲ የመሆን ጉዳይ የዛሬ አለመሆኑን ነው።

ከብአዴን እንደሆነ የጠቀሰ አንድ ጉባኤተኛ ጥያቄውን ሲያነሳ ቀደም ሲል ይህ ጉዳይ ተነሥቶ እንደነበር ጠቆመ። በማስከተልም በወቅቱ ጥያቄው ሲነሳ አጥኚ ግብረ ሃይል መሰየሙን አወሳ። አያይዞም “ጉዳዩ የት ደረሰ?” በሚል ማሳሰቢያ መሰል ንግግር ምላሽ ጠየቀ። እንደውም አጥኚው ክፍል ምላሽ ቢሰጥበት ሲል መንገድ አመላከተ። በወቅቱ አቶ ተፈራ ዋልዋም ወ/ሮ አዜብ መስፍን ጎን ተቀምጠው ለጥያቄው ድጋፍ ሰጥተው እንደነበርም በጉባኤው የተሳተፉ ያስታውሳሉ። ሌሎች ድጋፍ የሰጡም ነበሩ።

አቶ መለስ ድርጅታቸው ኅብረ ብሔር እንዲሆን ለቀረበው ጥያቄ “ይህንኑ ጉዳይ እንዲያጠና የተቋቋመው ሃይል እያጠናው ነው” ሲሉ ነበር የመለሱት። በመልሳቸው ትግበራው የጥያቄውን ያህል ቀላል ጉዳይ እንደማይሆን አልሸሸጉም ነበር። ይህንኑ የአቶ መለስ መልስ ተከትሎ ወዲያውኑ የተለያዩ አስተያየቶች ተሰነዘሩ። የአሁኑ ብአዴን “ኢህዴን” ተብለህ መጠራት አትችልም ተብሎ ወደ ብአዴን የተከለሰው የእነ አዲሱና በረከት ድርጅት በነሱም ባይሆን በሌሎች አባላቱ በኩል ቅሬታውን አሰምቷል። ከሁሉም በላይ ግን ሚዛን የደፋው የኢህአዴግ አባልና አጋር ድርጅቶች ኤፈርት ላይ የሚያሰሙት ሹክሹክታ ነበር። ኤፈርትን “ቦዬ” በማለት አጥብቀው የሚጠሉት የኦህዴድ ሰዎች ናቸው። “ቦዬ” ማለት ያገኘውን ሁሉ የሚያግበሰብስ አሳማ እንደ ማለት ነው።

በሌላ በኩል ኢህአዴግን ኅብረ ብሔር ፓርቲ እንዳይሆን በግንባር ቀደምትነት ቅሬታ የሚያሰማው ህወሃት ነው። በጉዳዩ ዙሪያ በቂ መረጃ ያላቸው እንደሚሉት ህወሃት በሃሳቡ የማይስማማው ኤፈርት የተሰኘው የድርጅቱ የንግድ ኢምፓየር ባካበተው ሃብትና ነጻ አውጪው ግንባር ካለው የቆየ ህልሙ በመነሳት እንደሆነ ይነገራል። ኢህአዴግ ኅብረ ብሔር ፓርቲ ከሆነ በቅድሚያ በግንባሩ ውስጥ ያሉት ድርጅቶች ይከስማሉ። ድርጅቶቹ ከከሰሙ ያላቸው ሃብት ይቀላቀላል። የሁሉም ድርጅቶች የንግድ ተቋማት ተዋህደው ከሁሉም ወገኖች የተውጣጡ የቦርድ አባልት እንዲመሩት ይደረጋል። ራሱን የትግራይ ነጻ አውጪ ግምባር ብሎ ለሚጠራው ህወሃት ይህ አካሄድ ትክክለኛ የውኅደት አሠራር ቢሆንም እስካሁን ሊዋጥለት ያልቻለ እውነታ ነው፡፡

ከራሱ ከህወሃት አባላት በየጊዜው የሚያፈተልከው የኤፈርት ጉዳይ እስካሁን መልስ ቀርቦበት አያውቅም። ከህወሃት አባላትና ደጋፊዎች ዘንድም ልዩ ጥያቄ የሚነሳው በጀቱ የት ደርሷል? ካፒታሉ በጥሬ ገንዘብና በቁስ ሲተመን በጥቅሉ ምን ያህል ሃብት አለው? ለምን ኦዲት አይደረግም? የኦዲት ሪፖርትስ ለምን አይቀርብበትም? የሚሉና በርካታ የግልጽነት ችግሮች ናቸው። መልስ ግን የለም። የሚገርመው ግን ኤፈርትን በተለያየ የአመራር ደረጃ ይመሩ የነበሩ ከኃላፊነት ሲነሱ ወይም ሲባረሩ፣ ከአገር ሲለቁ ወይም ሥራ ሲለቁ ስለ ድርጅቱ የሚሉት ነገር አለመኖሩ ነው።

ህወሃት በዘመነ ህንፍሽፍሽ ለሁለት ተሰንጠቆ ስለ መበስበስ አደጋ በአደባባይ ሲነገር፣ ሙስና ስልታዊ መምቻ መሳሪያ ሆኖ ሲታወጅና የመለስን ህልውና የተፈታተኑ ናቸው የተባሉትን ሲከረቸሙ፣ አንዱ አባራሪ ሆኖ ሌላው ሲባረር የኤፈርት ጉዳይ ግን ለሁሉም ወገኖች በእኩል ደረጃ ሚስጥርነቱ የተጠበቀ መሆኑ ነው።አባራሪውም ሆነ ተባራሪው ኤፈርት ላይ ዝግ ናቸው። ኦዲት ተደርጎ እንደማያውቅ በገደምዳሜ ከመናገራቸው በቀር እነሱም ሲፈጩና ሲከኩ በነበረበት ወቅት ስለሚያውቁት ሃቅ አያወሩም፤ አያብራሩም፤ አይጽፉም። ከሁለት ዓመት በፊት በድንገት ከኤፈርት ዋና ኃላፊነታቸው ሳይሰናበቱ ካገር ወጥተው ስደትን የተቀላቀሉት የህወሃት ሰው ምንም አለመተንፈሳቸው አግራሞቱን እጅግ የሚያሰፋ እንደሆነ ብዙዎች ያምናሉ። እናም ይህ እውነት ባለበት ሁኔታ ኢህአዴግን ኅብረ ብሔር ፓርቲ ለማድረግ ታስቧል የሚባለው ቧልት ከመሆን አይዘልም የሚል ስምምነት አለ።

ቀደም ሲል ሲብላሉና በተባራሪ ሲነሱ የነበሩ ጉዳዮች አሁን አሁን አደባባይ መውጣት ጀምረዋል። “ታላቋ ትግራይ” ድንበሯ ኤርትራን ዘልቆ እንደሚገባ አፍቃሪ ህወሃት ድረገጾች ይፋ እያደረጉ ነው። ከኤርትራ በኩል ምላሽ ባይሰጥም “ትግራዋይ” ኤርትራን ጠቅልላ “የታፈረችና የተከበረች ታላቅ አገር” ለመሆን የሌሎችን የመብትና የማንነት ጥያቄ እየጨፈለቀች በመገስገስ ላይ መሆንዋ አሁንም የሃይለማርያምን ቃል ትርጉም አልባ የሚያደርግ ስለመሆኑ ተቺዎች ይናገራሉ።

አሁን ከፖለቲካው ጡዘት ጋር ተዳምሮ ቦዬ የደረሰበት ደረጃ የድርጅቶችን ውህደት የማይታሰብ ያደርገዋል የሚሉ ወገኖች ሃሳቡን “ጊዜ ወለድ ማደናገሪያ” ይሉታል። ላለፉት 25ዓመታት አገር እየመራ በሽፍትነት ዘመኑ “የትግራይ ነጻ አውጪ” የሚለውን ስሙን ለመቀየር የሚያንቀው ህወሃት፣ ስሙን ፍቆ፣ ሃብቱን አዋህዶ፣ ለአብላጫ ድምጽና ለአብዛኞች ውክልና ለመገዛት ምሎ አሃዳዊ ፓርቲ ሊሆን ይችላል ብሎ ማሰብ “አሳማን ከተፈጥሮው ህግ ውጪ ዶሮ የማድረግ ያህል ነው” በማለት በሃሳቡ የሚሳለቁ ጥቂት አይደሉም። ምናልባት በእኩይ ሳይንሳዊ “ጥበብ” ተግባራዊ ማድረግ የሚቻልበት ዘመን እስኪመጣ ላሁኑ የማይታሰብ ነው ይላሉ፡፡

ለአገራዊ ጉዳይና ለአገሪቱ ታሪካዊ ዳራዎች ደንታ የሌለው ህወሃት፣ አገሪቱን ባህር አልባ ያደረገው ህወሃት፣ ዜጎቹን የሚጨፈጭፈው ህወሃት፣ የኢትዮጵያን ትልቅነትን አጥብቆ የሚጠላው ህወሃት፣ የሚምልባቸውን አርሶ አደሮች የሚበላው ህወሃት፣ ክልሉን እያሰፋ ሌሎችን የሚያቀጭጨው ህወሃት፣ ባህሪውና ፍጥረቱ ሁሉ ብሔራዊ የሚባሉ የአንድነት ማሳያ ታሪኮችን የሚበላው ህወሃት፣ አገሪቱን በጎሳና በብሔር ቆራርጦ ወደ ረመጥነት የቀየረው ህወሃት፣ ህጻናት አረጋዊ ሳይል በአልሞ ተኳሾች የሚገድለው ህወሃት፣ እመራቸዋለሁ ከሚላቸው ዜጎች ይልቅ ለሌሎች ክብር የሚሰጠው ህወሃት፣ በሙስናና በዝርፊያ “እስከ እንጥሉ የገማው” ህወሃት፤ ዓላማው፣ ሃሳቡና ፍጥረቱ ውኅደት አድርጎ ብሔር ተኮር ውጥኑን ሊያስቀይረው አያስችለውም ሲሉ ዜናውን ከጅምሩ ያጣጥሉታል።

እነዚህ ወገኖችን ጨምሮ በርካታ የኦህዴድ አባላት ሚድሮክና ኤፈርት ግንኙነት እንዳላቸው ያምናሉ። የሼኽ መሐመድ ሁሴን አላሙዲ ድንገት ሃብታም መሆንና ግብር እንኳን ሳይከፍሉ ኦሮሚያ ላይ እንዲፈነጩ የተፈቀደላቸው ከህወሃት ጋር ባላቸው የንግድ ትሥሥር እንደሆነ የኦህዴድ ከፍተኛ አመራሮች ሳይቀሩ ያምናሉ። እነዚህ ወገኖች ህወሃት አሃዳዊ ፓርቲ የሚሆነው ኤፈርትን በኦፊሴል ከሚድሮክ ጋር ሲያዋህድ እንደሆነ ይጠቅሳሉ። አሁን አሁን ኤፈርት ወርቅ ባለበት ሚድሮክን እየተከተለ መሬት መመራቱ የዚሁ የግንኙነቱ ማደግ ውጤት እንደሆነ እነዚሁ ክፍሎች ይናገራሉ።

ከሁሉም በላይ በ2001 ሃዋሳ በተደረገው የኢህአዴግ ጉባኤ በተባለው መሰረት ጉዳዩን እንዲያጠና የተሰየመው ኮሚቴ ጥናቱ ስንት ዓመት የሚፈጅ ሆኖ ነው የጥናቱ ውጤት የማይገለጸው? ከ2001 በፊት የተቋቋመው ኮሚቴ ለመሆኑ አለ? እነማን ናቸው? ጥናቱስ ተካሂዷል? ወይስ ጨበጣ ነው? አቶ መለስ አጥኚው ኮሚቴ የጥናቱን ውጤት በ2003 ኦህዴድ በሚያዘጋጀው የአዳማው ጉባኤ ያቀርባል ብለው ነበር። ዛሬ ድረስ የተሰማ ነገር የለም። ስለ ጉዳዩ የምታውቁ አስተያየታችሁን ላኩልን።

ትግራይን መልሶ ለማቋቋም የተመሠረተው ኤፈርት በስድስት ዘርፎች ማለትም በፋብሪካ ምርት (ማኑፋክቸሪንግ)፣ በአገልግሎት ሰጪ፣ በሸቀጥ ንግድ፣ በግንባታ (ኮንስትራክሽን)፣ በማዕድን ፍለጋ እና በግብርና ሥራ የተሰማሩ የ14 ኩባንያዎች ባለቤት እንደሆነ በድረገጹ ላይ ተመልክቷል፡፡ ከእነዚህ መካከል መስፍን ኢንጂነሪንግ፣ መሰቦ የሲሚንቶ ፋብሪካ፣ አዲግራት የሚገኘው የመድኃኒት ፋብሪካ፣ አልመዳ ጨርቃጨርቅ፣ ጉና፣ ሱር ኮንስትራክሽን፣ ኢዛና የመዓድን ፍለጋ፣ በወልቃይት ጠገዴና በሁመራ ዘመናዊ የግብርና ተግባር የሚያከናውነው ሂወት ዘመናዊ እርሻ “ሜካናይዜሽን”፣ እና ሌሎች ኩባንያዎች በተለያዩ የኢትዮጵያ ክልሎች ሸቀጣቸውን “ለማከፋፈል” በአዲስ አበባ በጥቂት ሠራተኞች የሚንቀሳቀስ የማሰራጫ ቢሮ ሲኖራቸው ፋብሪካዎቹ በትግራይ ውስጥ በሺዎች ለሚቆጠሩ የክልሉ ነዋሪዎች የሥራ ዕድል እንደከፈቱ ድረገጹ ጨምሮ ይናገራል፡፡ የኤፈርትን ተልዕኮ ምን እንደሆነ ድረገጹ ሲያስረዳም በተለይ በትግራይ ድህነትን በመቀነስ ወይም በማስወገድና ልማትን በማስፋፋት ቀዳሚና ወሳኝ ሚና መጫወት እንደሆነ በግልጽ ይናገራል፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. geresu says

    April 2, 2016 03:49 pm at 3:49 pm

    ወያኔ ባታሽቃብጪ ይሻልሻል!! አቶ ሀይለማሪያም የአንቺ ሴራ ገና ያልገባቸው ይመስላሉ:: ህብረ ብሄር ወላ ገለመኔ የሚል ጊዚያዊ ማደናገሪያሽን ቂሎች ይዝፈኑልሽ:: ዛሬ ኢትዮጵያኖች የምንፈልገው ፍፁማዊ ለውጥ እንጂ ጥገናዊ ወይም የሽንገላ ለውጥ አንፈልግም:: ብዙ አባብለንሻል! ለምነንሻል! አልተጠቀምሽበትም! ጊዜው አልፈብሽ አሁን መነጋገር ያለብን አንቺ በመጣሽበት ብቸኛ አማራጭ ጠበንጃና ጠበንጃ ብቻ ነው:: ከጅምሩም ወያኔ ተብሎ ሀገር መሪ ሳይሆን ገንጣይና አስገንጣይ እንጂ ኢትዮጵያዊ መንፈስ የለሽም!! ጠባብ ድርጅት ነሽ!! ተኩላ! ቢበዛ ቢበዛ ያለሽ አላማ ብሄር ከብሄር: ጎሳ ከጎሳ በማናቆር የትግራይን ግዛት ማስፋፋት ብሎም መገንጠልና ምስኪኑን የትግራይ ህዝብ ከኢትዮጵያዊያን ወንድሞቹ ጋር አበደም በማድረግ ወደጦርነት በመማገድ የብልጣብልጦች የስልጣን ማራዘሚያና ሀብት ማጋበሻ ዘዴ አድርጎ መጠቀም ነው:: ከዚህ ያለፈ ምንም ራእይ የለሽም ! የደደቢት ደደብ!

    Reply
  2. gud says

    April 7, 2016 04:51 pm at 4:51 pm

    To all people of Ere

    We understand your pain . We will free u from the bondage soon . We know the movement of your people in Frankfurt , Roma , Paris , New York etc ….tesfa setchi new !!!

    Reply
  3. Yikir says

    April 9, 2016 12:30 am at 12:30 am

    Thank u ! Geresu & Gud. Weyanen mamen ketom ayichalim.Hibire biher parti kerto :hullunim neger leweyane binitew ;ethiopian ena hizibuwan yatefal.yatefal.yatefal:: iwiru meriyachin /kiray minister H/Aram Desalegni /yebanda,banda ,banda, gumare new..,.,.,….AWIRA YETEBALEWIN YAWERAL .SIRAW YE ETHIOPIAN GETSITA MATENAGER NEW. Hodam new .jeddddaaaal new. Uziraaa’eeel new. Yemot melak new. DIL LE ETHIOPIA HIZIB.

    Reply
  4. ሸመልስይማም says

    April 26, 2016 03:57 pm at 3:57 pm

    በጣምትክክል

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule