• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኢህአዴግ ከብሔር “ተኮር” ተቃዋሚዎች ጋር ሊሸማገል ነው

December 14, 2013 03:41 am by Editor Leave a Comment

ኢህአዴግ በብሔርና በክልል ደረጃ ከተደራጁ የተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች መካከል ግጭት ባለባቸው አካባቢዎች ለሚንቀሳቀሱት ቅድሚያ በመስጠት ለመደራደር የሚያስችለውን ቅድመ ሁኔታ በማመቻቸት ላይ መሆኑን የጎልጉል ምንጮች ገለጹ። ምንጮቹ እንደጠቆሙት ኢህአዴግ ለዚህ ተግባሩ ወዳጅ ጎረቤት አገሮችን፣ አንጋፋ የጎሳ መሪዎችንና ያፈገፈጉ የቀድሞ ተቃዋሚ መሪዎችን እየተጠቀመ ነው።

ህወሃት አሁን በአገሪቱ ከቀን ወደ ቀን እየተስፋፋ የሄደው አለመረጋጋት እንዳሳሰበው የጠቆሙት የኢህአዴግ ሰው ድርጅቱ እርቅ ላይ ከመቼውም በላይ ትኩረት ሰጥቶ ለመስራት ስትራቴጂ መንደፉን አመልክተዋል።

“ከውጥረት ለመውጣት ወይም ውጥረትን ለመቀነስ” በሚል ኢህአዴግ ትኩረት ሰጥቶ የጀመረው አዲሱ የ”ሰላም” መንገድ ህብረ ብሔር ድርጅቶችን ያላከተተበትን ምክንያት አልተብራራም። ይሁን እንጂ ከኢህአዴግ ባህሪ አንጻር አቋሙ ሊቀየር የሚችል መሆኑን አልሸሸጉም።

ለድርድር የተመረጡትን ብሔርና ክልል “ተኮር” ድርጅቶች ይፋ ማድረግ ለጊዜው እንደሚቸግራቸው ምንጮቹ ተናግረዋል። በድፍኑ ግን በተለይ ምዕራብ ኢትዮጵያ፣ ደቡብ ክልልና ምስራቅ ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚንቀሳቀሱ የነጻ አውጪና ብሔርን መሰረት ያደረጉ ድርጅቶች በማዕቀፉ ውስጥ እንዳሉ አመላክተዋል።

ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ የውጪ ኢንቨስተሮች ፍሰት መቀነሱ፣ ገብተው በመንቀሳቀስ ላይ የሚገኙት ድርጅቶችም ከጸጥታና መሰል ችግሮች አገር ለቀው ወደመውጣቱ ላይ በመሆናቸው፣ አገሪቱ ውስጥ ያለው የስራ አጥነት ችግር እየተወሳሰበ መሄዱና ድህነት በቃላት ሊገለጽ ከሚችለው በላይ መስፋቱ ህወሃቶችን እንዳሳሰባቸው ያስታወቁት የጎልጉል መረጃ ሰጪዎች “የኢህአዴግ አቻ ፓርቲዎችም ለህወሃት ያላቸው የአገልጋይነት መንፈስ እየተመናመነ መሄዱ ዋንኛው የህወሃት ጭንቀት ነው” ብለዋል። በዚህም የተነሳ እርቅ ከምንጊዜውም በላይ አስፈላጊ የሆነበት ወቅት ነው።

ህወሃት ባደራጃቸው የብሔርና የጎሳ ድርጅቶች ጥላ ስር ለይስሙላ ራሳቸውን በራሳቸው ያስተዳድራሉ ከሚባሉ ክልሎችና ዞኖች “እውነተኛ ውክልና አለን” የሚሉ ብሄርን፣ ክልልንና ዞንን መሰረት አድርገው ከሚንቀሳቀሱ ድርጅቶች ጋር ለማካሄድ የታሰበው ድርድር ተግባራዊ ከሆነ አተገባበሩ እንዴት ሊሆን እንደሚችልም ምንጮቹ አላብራሩም። ይሁን እንጂ ቀደም ሲል ኦህዴድንና ኦነግን ለማስማማት ተካሂዶ በነበረው ንግግር ኦነግን ወደ ኦህዴድ ለማጠቃለልና ለኦነግ ስልጣን ለማጋራት የታቀደው እቅድ መክሸፉን አስታውሰዋል።

መረጃ ሰጪዎቹ አያይዘው እንደተናገሩት በቀዳሚነት በተለይ ከሶስት ክልልና ብሔር “ተኮር” ድርጅቶች ጋር ኢህአዴግ ለማከናወን የሚፈልገው እርቅ በክልሉ ወይም በዞኑ በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት ያላቸውን መሪዎች እጁን ዘርግቶ እስከመቀበል የሚያደርሰው ነው። ቀጥለው ሲያስረዱም ሙሉ አስተዳደራዊ ስልጣን እስከመስጠት ሊደርስ እንደሚችል ተናግረዋል።

ህወሃት ከአፈጣጠሩ ጀምሮ አገሪቱን አሳንሶ አዳክሞና ቆራርጦ የማቀራመት ዓላማ ስላለው ምን አልባትም በደቡብ ክልል አዲስ ክልል ሊወለድ ይችላል የሚል ስጋት እንዳለ ከምንጮቹ መረጃ ለመረዳት ተችሏል።

Isaias-Afwerki-in-Kenya2
ኢሣያስ ከደቡብ ሱዳን መሪ ሳልቫ ኪር ጋር

በማስታረቁ ስራ ላይ የተሰማሩትን ማንነት መግለጽ ለጊዜው አግባብ አይደለም በማለት ዝምታን የመረጡት የኢህአዴግ ሰዎች እርቅ በመላው አገሪቱ እንደሚያስፈልግ አብዛኛው ካድሬና የበላይ አመራሮች ምኞት መሆኑን ጠቁመዋል። ዋናው ቁልፍ ያለው በህወሃት እጅ በመሆኑ ክልሎችን ቀደም ሲል ያስቀየመ አካሄድ በመሆኑ በአሁኑ እርቅ አካሄድ ላይ የክልል ከፍተኛ ባለስልጣኖችም እንደተሰማሩበት ተመልክቷል። ሰሞኑን ግንቦት 7 የፍትህና የዴሞክራሲ ንቅናቄ ኢህአዴግ ለሶስት ጊዜ ያህል የእርቅ ጥያቄ እንዳቀረበለት መግለጹና ኢህአዴግም በኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት በኩል ግንቦት 7ን የመታረቅ እቅድ እንደሌለው በመግለጽ ጉዳዩን ማጣጣሉ ይታወሳል።

ደቡብ ሱዳን ኢትዮጵያና ኤርትራን ለመሸምገል በይፋ ማስታወቋ፣ ኳታርም ቀደም ሲል በተመሳሳይ ለእርቅ ላይ ታች ስትል መቆየቷ የሚታወስ ነው። የሁለቱም አገራት የሽምግልና ሩጫ ምን ውጤት እንዳስመዘገበ የሚታወቅ ኦፊሳላዊ መረጃ ከየትኛውም ወገን አልተደመጠም። ይልቁኑም ህወሃትና ሻዕቢያ አንዱ የሌላውን ባላንጣ በማደራጀት ስራ ላይ መጠመዳቸው ነው በይፋ እየተነገረ ያለው።

Isaias-Afwerki-in-Kenya1
የኬኒያው መሪ ዑሁሩ ኬኒያታና ኢሣያስ

በሌላ በከል ደግሞ ኢጋድንና የኢጋድ አገራት መሪዎችን በይፋ ሲዘልፉ የነበሩት የኤርትራ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ሰሞኑን በሱዳን ያደረጉት ጉብኝት ተከትሎ አዳዲስ መረጃዎች እየተሰሙ ነው። ከኢጋድ ጋር ያላቸውን ግንኙነት በይፋ ለማደስ እየሰሩ መሆናቸውም ተነግሯል። ኤርትራ በተባበሩት መንግስታት የተጣለባት እቀባ እንዲነሳላት አጠንክራ እየተከራከረች ባለችበት ወቅት ላይ ሆና ኢጋድን በወጉ ለመወዳጀት ወስናለች መባሉ ወሬውን ሚዛን የሚደፋ እንደሚያደርገው በርካቶች ይስማሙበታል።

ኢህአዴግ በቀጠናው ብሎም በኢጋድ ውስጥ ባለው ተሰሚነት የተነሳ መድረኩ ሻዕቢያንና ወያኔን በማገናኘት ለማሸማገል ለሚደረገው ጉዞ የመጀመሪያው ርምጃ እንደሆነ ከግምት በላይ የሚናገሩም አሉ። ከካርቱሙ ጉብኝት በኋላ በኬኒያ 50ኛ ዓመት የነጻነት በዓል ላይ የተገኙት ፕሬዚዳንት ኢሳያስ በጉዳዩ ላይ ከቀጣናው አገራት ጋር እንደሚመክሩበት በመግለጽ ጉብኝታቸውን ከዚሁ ጋር የሚያይዙ አሉ። ይህን አስመልክቶ ግን ከየትኛውም ወገን በገሃድ የተሰጠ መግለጫ ግን የለም።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule