• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኢህአዴግ እያስታመመ ነው

December 15, 2012 01:51 am by Editor Leave a Comment

የአቡነ መርቆርዮስ ወደ አገር ቤት መመለስ ከስምምነት ላይ ተደረሰ፡፡ ልዩነት የተፈጠረው መንበራቸውን በመረከባቸው አብይ የቤ/ክርስቲያን ቀኖና ላይ ነው፡፡

ይህ የተገለጸው ከህዳር 26 እስከ ህዳር 30፤ 2005ዓም (December 5 – 9, 2012) በዳላስ ከተማ በቴክሳስ ጠቅላይ ግዛት በአገርቤቱ ሲኖዶስና በአሜሪካ ከሚገኘው ስደተኛ ሲኖዶስ ተወካዮች ድርድራቸው ካጠናቀቁ በኋላ ባወጡት የጋራ መግለጫ ነው፡፡

የጋራ መግለጫው ከመውጣቱ በፊት ፕሬዚዳንት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ አቡነ መርቆሪዮስ ከነሙሉ መንበራቸው አገር ቤት እንዲመለሱ የሚጠይቅና ማረጋገጫ የሚሰጥ ደብዳቤ ልከው ነበር፡፡

“የኔው የራሴ ደብዳቤ ነው” በማለት ለቪኦኤ የአማርኛ ክፍል በቃላቸው ጭምር ያረጋገጡት ፕሬዚዳንቱ ከአፍታ በኋላ “ያለሥልጣኔ ገብቼ የፈጸምኩት ነው” በማለት ደብዳቤውን መሰረዛቸውን አስታውቀው ነበር፡፡ ከጀርባው “እንዲህ ያለ ጣጣ አልመሰለኝም” በሚል ድፍን ምላሽ በመስጠት “የቀድሞ አቋሜን ትቸዋለው” ሲሉ ለቪኦኤ መልስ የሰጡት የመጀመሪያ ሃሳባቸውን በመቃወም ከአቡነ ህዝቅኤል ወቀሳ እንደተሰነዘረባቸው አልሸሸጉም፡፡

በቀጣይ አሜሪካ ሬዲዩ ለድጋሚ ጥያቄ ለፕሬዚዳንቱ ያደረገው የስልክ ጥሪ “እኔ የፖለቲካ ጉዳያቸው ልዩ አማካሪያቸው ነኝ” በማለት አቶ አሰፋ ከሲቶ ጉዳዩን አስመልክቶ የሰጡት መልስ ዳላስ በተደረገው ድርድር የአገርቤት ተወካዮች የሚይዙትን አቋም አስቀድሞ ያንጸባረቀ ነው፡፡

የመንግሥት አቋም ምን እንደሆነ የተናገሩት አቶ አሰፋ፤ አቡነ መርቆሪዮስ ወደአገራቸው መግባት እንደሚችሉ፤ ፍላጎት ካላቸው ለርዕሳነ ፓትሪያርክነት መወዳደር መብታቸው እንደሆነ፤ ቀደም ሲል የተወሰነላቸውን ውሳኔ ተግባራዊ ከማድረግ አኳያ መንግሥት ተቃውሞ እንደሌለው ጨምረው አብራርተዋል፡፡

በዚሁ ሬዲዮ አስተያየታቸውን እንዲሰጡ የተጠየቁት አቡነ ህዝቅያስ ፕሬዚዳንቱ ስለተናገሩት ሲጠየቁ ያስቀደሙት “ኢህአዴግ ስለሾማቸው ፕሬዚዳንቱ መዘላበድ አይችሉም” በማለት የፕሬዚዳንቱን ንግግርና አካሄድ በማውገዝ ነበር፡፡

ፕሬዚዳንቱ በጻፉት ደብዳቤ መንግሥትም መቆጣቱን ያስታወቁት አቡነ ህዝቅኤል፤ አቡነ መርቆሪዮስ ሟቹ አቡነ ጳውሎስ ፓትሪያርክ ከመሆናቸው በፊት የተወሰነላቸውን ተግባራዊ ከማድረግ ውጪ አዲስ ነገር እንደሌለ ተናግረዋል፡፡ አቡነ ህዝቅኤል እንዳሉት አቡነ መርቆሪዮስ በመረጡት ቦታ አስፈላጊውን ሁሉ ተሟልቶላቸው ለአገራቸው አፈር እንዲበቁ ከተወሰነው ውጪ የሚደረግ ነገር እንደሌለ ጨምረው አስታውቀዋል፡፡

ከመንግሥትና ከአገርቤት ሲኖዶስ በኩል ያለው ተመሳሳይ አቋም እየተገለጸ ባለበት ወቅት በውጪ ባለው ስደተኛው ሲኖድና በአገርቤቱ ሲኖድ መካከል አራት አራት ተወካዮች ያካተቱበት ድርድር እየተካሄደ ነበር፡፡ በድርድሩ መጨረሻ ሁለቱ አካላት በጋራ ባወጡት መግለጫ አንኳር ጉዳይ ከላይ የተቀመጠው የውሳኔ ሃሳብ ላይ የሚያጠነጥን ነው፡፡ በውጪ አገር የሚኖረው ሲኖዶስ አቡነ መርቆሪዮስ አገር ቤት ከነሙሉመንበራቸው ይመለሱ ሲል የአገርቤቱ ደግሞ ደግሞ ከላይ የተጠቀሰውን የመንግሥትንና የወከላቸውን ሲኖዶስ መሰረታዊ አቋም ከማስጠበቅ የዘለለ ነገር አላቀረበም፡፡ አብዛኛዎች የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቀኖና ሊከበር ነው፤ መንግሥትና አገር ቤት ያለው ሲኖዶስ የህዝብን ፍላጎት ሊያስተናግዱ የተዘጋጁ ይመስላሉ በሚል አስቀድመው ሙገሳና ምስጋና ያቀረቡለት ድርድር ዋናውን ጉዳይ አስቀምጦ ቀጣዩንና አራተኛውን ድርድር ከጥር 16 እስከ ጥር 18፤ 2005ዓም (January 24 – 26, 2013) በሎስ አንጀለስ ከተማ፤ ካሊፎርኒያ ጠቅላይ ግዛት ለማድረግ ቀጠሮ ይዞ ተለያይቷል፡፡

አስተያየት ሰጪዎች ከሙስሊሙ ማኅበረሰብ ጋር አጣብቂኝ ውስጥ የገባው ኢህአዴግ ከወትሮው በተለየ የአቡነ መርቆሪዮስን ጉዳይ የሚያስታምመው እንደሌሎች የፖለቲካ ድርድሮች ሰጥቶ መቀበል ወይም ውጤትን በእኩል መጋራት (win-win) የሚባል አማራጭ ስለሌለው ነው ይላሉ፡፡ በዚህም ምክንያት አገር ቤት ቤተክህነት አካባቢ ያሉትን የመንግሥት ወዳጆች እና ህዝበክርስቲያኑን ላለማስከፋት መለሳለስ የመረጠው ለዚህ ነው የሚል አስተያየት ሰጥተዋል፡፡

የመግለጫው ሙሉ ቃል ይህ እዚህ ላይ ይገኛል፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am
  • የኦነግ ሸኔ አባላትን ዕድሜ ለማሳጠር የጂፒኤስ ቴክኖሎጂ ጥቅም ላይ እየዋለ ነው December 7, 2020 12:38 am
  • የቆሰሉ ወታደሮች በጠቅላይ ሚኒስትሩ ተጎበኙ December 6, 2020 11:41 pm
  • “ከዚህ በኋላ ይዘን እንታገላለን እንጂ ሠጥተን አንጠይቅም” ኮሎኔል ደመቀ December 2, 2020 12:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule