• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኢህአዴግ እያስታመመ ነው

December 15, 2012 01:51 am by Editor Leave a Comment

የአቡነ መርቆርዮስ ወደ አገር ቤት መመለስ ከስምምነት ላይ ተደረሰ፡፡ ልዩነት የተፈጠረው መንበራቸውን በመረከባቸው አብይ የቤ/ክርስቲያን ቀኖና ላይ ነው፡፡

ይህ የተገለጸው ከህዳር 26 እስከ ህዳር 30፤ 2005ዓም (December 5 – 9, 2012) በዳላስ ከተማ በቴክሳስ ጠቅላይ ግዛት በአገርቤቱ ሲኖዶስና በአሜሪካ ከሚገኘው ስደተኛ ሲኖዶስ ተወካዮች ድርድራቸው ካጠናቀቁ በኋላ ባወጡት የጋራ መግለጫ ነው፡፡

የጋራ መግለጫው ከመውጣቱ በፊት ፕሬዚዳንት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ አቡነ መርቆሪዮስ ከነሙሉ መንበራቸው አገር ቤት እንዲመለሱ የሚጠይቅና ማረጋገጫ የሚሰጥ ደብዳቤ ልከው ነበር፡፡

“የኔው የራሴ ደብዳቤ ነው” በማለት ለቪኦኤ የአማርኛ ክፍል በቃላቸው ጭምር ያረጋገጡት ፕሬዚዳንቱ ከአፍታ በኋላ “ያለሥልጣኔ ገብቼ የፈጸምኩት ነው” በማለት ደብዳቤውን መሰረዛቸውን አስታውቀው ነበር፡፡ ከጀርባው “እንዲህ ያለ ጣጣ አልመሰለኝም” በሚል ድፍን ምላሽ በመስጠት “የቀድሞ አቋሜን ትቸዋለው” ሲሉ ለቪኦኤ መልስ የሰጡት የመጀመሪያ ሃሳባቸውን በመቃወም ከአቡነ ህዝቅኤል ወቀሳ እንደተሰነዘረባቸው አልሸሸጉም፡፡

በቀጣይ አሜሪካ ሬዲዩ ለድጋሚ ጥያቄ ለፕሬዚዳንቱ ያደረገው የስልክ ጥሪ “እኔ የፖለቲካ ጉዳያቸው ልዩ አማካሪያቸው ነኝ” በማለት አቶ አሰፋ ከሲቶ ጉዳዩን አስመልክቶ የሰጡት መልስ ዳላስ በተደረገው ድርድር የአገርቤት ተወካዮች የሚይዙትን አቋም አስቀድሞ ያንጸባረቀ ነው፡፡

የመንግሥት አቋም ምን እንደሆነ የተናገሩት አቶ አሰፋ፤ አቡነ መርቆሪዮስ ወደአገራቸው መግባት እንደሚችሉ፤ ፍላጎት ካላቸው ለርዕሳነ ፓትሪያርክነት መወዳደር መብታቸው እንደሆነ፤ ቀደም ሲል የተወሰነላቸውን ውሳኔ ተግባራዊ ከማድረግ አኳያ መንግሥት ተቃውሞ እንደሌለው ጨምረው አብራርተዋል፡፡

በዚሁ ሬዲዮ አስተያየታቸውን እንዲሰጡ የተጠየቁት አቡነ ህዝቅያስ ፕሬዚዳንቱ ስለተናገሩት ሲጠየቁ ያስቀደሙት “ኢህአዴግ ስለሾማቸው ፕሬዚዳንቱ መዘላበድ አይችሉም” በማለት የፕሬዚዳንቱን ንግግርና አካሄድ በማውገዝ ነበር፡፡

ፕሬዚዳንቱ በጻፉት ደብዳቤ መንግሥትም መቆጣቱን ያስታወቁት አቡነ ህዝቅኤል፤ አቡነ መርቆሪዮስ ሟቹ አቡነ ጳውሎስ ፓትሪያርክ ከመሆናቸው በፊት የተወሰነላቸውን ተግባራዊ ከማድረግ ውጪ አዲስ ነገር እንደሌለ ተናግረዋል፡፡ አቡነ ህዝቅኤል እንዳሉት አቡነ መርቆሪዮስ በመረጡት ቦታ አስፈላጊውን ሁሉ ተሟልቶላቸው ለአገራቸው አፈር እንዲበቁ ከተወሰነው ውጪ የሚደረግ ነገር እንደሌለ ጨምረው አስታውቀዋል፡፡

ከመንግሥትና ከአገርቤት ሲኖዶስ በኩል ያለው ተመሳሳይ አቋም እየተገለጸ ባለበት ወቅት በውጪ ባለው ስደተኛው ሲኖድና በአገርቤቱ ሲኖድ መካከል አራት አራት ተወካዮች ያካተቱበት ድርድር እየተካሄደ ነበር፡፡ በድርድሩ መጨረሻ ሁለቱ አካላት በጋራ ባወጡት መግለጫ አንኳር ጉዳይ ከላይ የተቀመጠው የውሳኔ ሃሳብ ላይ የሚያጠነጥን ነው፡፡ በውጪ አገር የሚኖረው ሲኖዶስ አቡነ መርቆሪዮስ አገር ቤት ከነሙሉመንበራቸው ይመለሱ ሲል የአገርቤቱ ደግሞ ደግሞ ከላይ የተጠቀሰውን የመንግሥትንና የወከላቸውን ሲኖዶስ መሰረታዊ አቋም ከማስጠበቅ የዘለለ ነገር አላቀረበም፡፡ አብዛኛዎች የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቀኖና ሊከበር ነው፤ መንግሥትና አገር ቤት ያለው ሲኖዶስ የህዝብን ፍላጎት ሊያስተናግዱ የተዘጋጁ ይመስላሉ በሚል አስቀድመው ሙገሳና ምስጋና ያቀረቡለት ድርድር ዋናውን ጉዳይ አስቀምጦ ቀጣዩንና አራተኛውን ድርድር ከጥር 16 እስከ ጥር 18፤ 2005ዓም (January 24 – 26, 2013) በሎስ አንጀለስ ከተማ፤ ካሊፎርኒያ ጠቅላይ ግዛት ለማድረግ ቀጠሮ ይዞ ተለያይቷል፡፡

አስተያየት ሰጪዎች ከሙስሊሙ ማኅበረሰብ ጋር አጣብቂኝ ውስጥ የገባው ኢህአዴግ ከወትሮው በተለየ የአቡነ መርቆሪዮስን ጉዳይ የሚያስታምመው እንደሌሎች የፖለቲካ ድርድሮች ሰጥቶ መቀበል ወይም ውጤትን በእኩል መጋራት (win-win) የሚባል አማራጭ ስለሌለው ነው ይላሉ፡፡ በዚህም ምክንያት አገር ቤት ቤተክህነት አካባቢ ያሉትን የመንግሥት ወዳጆች እና ህዝበክርስቲያኑን ላለማስከፋት መለሳለስ የመረጠው ለዚህ ነው የሚል አስተያየት ሰጥተዋል፡፡

የመግለጫው ሙሉ ቃል ይህ እዚህ ላይ ይገኛል፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዛሬ ‘ኃያል ነን’ የሚሉ ሀገራት ኢትዮጵያ ላይ በሚዲያ /በመረጃ/፣ በዲፕሎማሲ፣ በሳይበር እና በተልእኮ የተቀነባበረ ‘ግራጫ ጦርነት’ እያካሄዱባት ነው” ጠ/ሚ ዐቢይ July 7, 2022 10:03 am
  • የኦሮሞ ልሂቃንና ፖለቲከኞች በአማራ ተወላጆች ላይ እየደረሰ ያለውን “የዘር ማጥፋት” ወንጀል እንዲያወግዙት አብን ጠየቀ July 6, 2022 01:38 pm
  • “አማራን ኦሮሚያ ውስጥ የመግደል እና የመጨፍጨፍ እቅድ የኦነግ ሳይሆን የኦሮሚያ ብልጽግና ነው” አቶ ሃንጋሳ July 6, 2022 01:53 am
  • “በኢትዮጵያዊያን የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ በመግባት ሀገሪቱን ማተራመስ አለብን” አይማን አብድልአዚዝ ግብጻዊው ፖለቲከኛ July 5, 2022 12:57 pm
  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule