• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኢህአዴግ እያስታመመ ነው

December 15, 2012 01:51 am by Editor Leave a Comment

የአቡነ መርቆርዮስ ወደ አገር ቤት መመለስ ከስምምነት ላይ ተደረሰ፡፡ ልዩነት የተፈጠረው መንበራቸውን በመረከባቸው አብይ የቤ/ክርስቲያን ቀኖና ላይ ነው፡፡

ይህ የተገለጸው ከህዳር 26 እስከ ህዳር 30፤ 2005ዓም (December 5 – 9, 2012) በዳላስ ከተማ በቴክሳስ ጠቅላይ ግዛት በአገርቤቱ ሲኖዶስና በአሜሪካ ከሚገኘው ስደተኛ ሲኖዶስ ተወካዮች ድርድራቸው ካጠናቀቁ በኋላ ባወጡት የጋራ መግለጫ ነው፡፡

የጋራ መግለጫው ከመውጣቱ በፊት ፕሬዚዳንት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ አቡነ መርቆሪዮስ ከነሙሉ መንበራቸው አገር ቤት እንዲመለሱ የሚጠይቅና ማረጋገጫ የሚሰጥ ደብዳቤ ልከው ነበር፡፡

“የኔው የራሴ ደብዳቤ ነው” በማለት ለቪኦኤ የአማርኛ ክፍል በቃላቸው ጭምር ያረጋገጡት ፕሬዚዳንቱ ከአፍታ በኋላ “ያለሥልጣኔ ገብቼ የፈጸምኩት ነው” በማለት ደብዳቤውን መሰረዛቸውን አስታውቀው ነበር፡፡ ከጀርባው “እንዲህ ያለ ጣጣ አልመሰለኝም” በሚል ድፍን ምላሽ በመስጠት “የቀድሞ አቋሜን ትቸዋለው” ሲሉ ለቪኦኤ መልስ የሰጡት የመጀመሪያ ሃሳባቸውን በመቃወም ከአቡነ ህዝቅኤል ወቀሳ እንደተሰነዘረባቸው አልሸሸጉም፡፡

በቀጣይ አሜሪካ ሬዲዩ ለድጋሚ ጥያቄ ለፕሬዚዳንቱ ያደረገው የስልክ ጥሪ “እኔ የፖለቲካ ጉዳያቸው ልዩ አማካሪያቸው ነኝ” በማለት አቶ አሰፋ ከሲቶ ጉዳዩን አስመልክቶ የሰጡት መልስ ዳላስ በተደረገው ድርድር የአገርቤት ተወካዮች የሚይዙትን አቋም አስቀድሞ ያንጸባረቀ ነው፡፡

የመንግሥት አቋም ምን እንደሆነ የተናገሩት አቶ አሰፋ፤ አቡነ መርቆሪዮስ ወደአገራቸው መግባት እንደሚችሉ፤ ፍላጎት ካላቸው ለርዕሳነ ፓትሪያርክነት መወዳደር መብታቸው እንደሆነ፤ ቀደም ሲል የተወሰነላቸውን ውሳኔ ተግባራዊ ከማድረግ አኳያ መንግሥት ተቃውሞ እንደሌለው ጨምረው አብራርተዋል፡፡

በዚሁ ሬዲዮ አስተያየታቸውን እንዲሰጡ የተጠየቁት አቡነ ህዝቅያስ ፕሬዚዳንቱ ስለተናገሩት ሲጠየቁ ያስቀደሙት “ኢህአዴግ ስለሾማቸው ፕሬዚዳንቱ መዘላበድ አይችሉም” በማለት የፕሬዚዳንቱን ንግግርና አካሄድ በማውገዝ ነበር፡፡

ፕሬዚዳንቱ በጻፉት ደብዳቤ መንግሥትም መቆጣቱን ያስታወቁት አቡነ ህዝቅኤል፤ አቡነ መርቆሪዮስ ሟቹ አቡነ ጳውሎስ ፓትሪያርክ ከመሆናቸው በፊት የተወሰነላቸውን ተግባራዊ ከማድረግ ውጪ አዲስ ነገር እንደሌለ ተናግረዋል፡፡ አቡነ ህዝቅኤል እንዳሉት አቡነ መርቆሪዮስ በመረጡት ቦታ አስፈላጊውን ሁሉ ተሟልቶላቸው ለአገራቸው አፈር እንዲበቁ ከተወሰነው ውጪ የሚደረግ ነገር እንደሌለ ጨምረው አስታውቀዋል፡፡

ከመንግሥትና ከአገርቤት ሲኖዶስ በኩል ያለው ተመሳሳይ አቋም እየተገለጸ ባለበት ወቅት በውጪ ባለው ስደተኛው ሲኖድና በአገርቤቱ ሲኖድ መካከል አራት አራት ተወካዮች ያካተቱበት ድርድር እየተካሄደ ነበር፡፡ በድርድሩ መጨረሻ ሁለቱ አካላት በጋራ ባወጡት መግለጫ አንኳር ጉዳይ ከላይ የተቀመጠው የውሳኔ ሃሳብ ላይ የሚያጠነጥን ነው፡፡ በውጪ አገር የሚኖረው ሲኖዶስ አቡነ መርቆሪዮስ አገር ቤት ከነሙሉመንበራቸው ይመለሱ ሲል የአገርቤቱ ደግሞ ደግሞ ከላይ የተጠቀሰውን የመንግሥትንና የወከላቸውን ሲኖዶስ መሰረታዊ አቋም ከማስጠበቅ የዘለለ ነገር አላቀረበም፡፡ አብዛኛዎች የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቀኖና ሊከበር ነው፤ መንግሥትና አገር ቤት ያለው ሲኖዶስ የህዝብን ፍላጎት ሊያስተናግዱ የተዘጋጁ ይመስላሉ በሚል አስቀድመው ሙገሳና ምስጋና ያቀረቡለት ድርድር ዋናውን ጉዳይ አስቀምጦ ቀጣዩንና አራተኛውን ድርድር ከጥር 16 እስከ ጥር 18፤ 2005ዓም (January 24 – 26, 2013) በሎስ አንጀለስ ከተማ፤ ካሊፎርኒያ ጠቅላይ ግዛት ለማድረግ ቀጠሮ ይዞ ተለያይቷል፡፡

አስተያየት ሰጪዎች ከሙስሊሙ ማኅበረሰብ ጋር አጣብቂኝ ውስጥ የገባው ኢህአዴግ ከወትሮው በተለየ የአቡነ መርቆሪዮስን ጉዳይ የሚያስታምመው እንደሌሎች የፖለቲካ ድርድሮች ሰጥቶ መቀበል ወይም ውጤትን በእኩል መጋራት (win-win) የሚባል አማራጭ ስለሌለው ነው ይላሉ፡፡ በዚህም ምክንያት አገር ቤት ቤተክህነት አካባቢ ያሉትን የመንግሥት ወዳጆች እና ህዝበክርስቲያኑን ላለማስከፋት መለሳለስ የመረጠው ለዚህ ነው የሚል አስተያየት ሰጥተዋል፡፡

የመግለጫው ሙሉ ቃል ይህ እዚህ ላይ ይገኛል፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule