• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኢህአዴግ እያስታመመ ነው

December 15, 2012 01:51 am by Editor Leave a Comment

የአቡነ መርቆርዮስ ወደ አገር ቤት መመለስ ከስምምነት ላይ ተደረሰ፡፡ ልዩነት የተፈጠረው መንበራቸውን በመረከባቸው አብይ የቤ/ክርስቲያን ቀኖና ላይ ነው፡፡

ይህ የተገለጸው ከህዳር 26 እስከ ህዳር 30፤ 2005ዓም (December 5 – 9, 2012) በዳላስ ከተማ በቴክሳስ ጠቅላይ ግዛት በአገርቤቱ ሲኖዶስና በአሜሪካ ከሚገኘው ስደተኛ ሲኖዶስ ተወካዮች ድርድራቸው ካጠናቀቁ በኋላ ባወጡት የጋራ መግለጫ ነው፡፡

የጋራ መግለጫው ከመውጣቱ በፊት ፕሬዚዳንት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ አቡነ መርቆሪዮስ ከነሙሉ መንበራቸው አገር ቤት እንዲመለሱ የሚጠይቅና ማረጋገጫ የሚሰጥ ደብዳቤ ልከው ነበር፡፡

“የኔው የራሴ ደብዳቤ ነው” በማለት ለቪኦኤ የአማርኛ ክፍል በቃላቸው ጭምር ያረጋገጡት ፕሬዚዳንቱ ከአፍታ በኋላ “ያለሥልጣኔ ገብቼ የፈጸምኩት ነው” በማለት ደብዳቤውን መሰረዛቸውን አስታውቀው ነበር፡፡ ከጀርባው “እንዲህ ያለ ጣጣ አልመሰለኝም” በሚል ድፍን ምላሽ በመስጠት “የቀድሞ አቋሜን ትቸዋለው” ሲሉ ለቪኦኤ መልስ የሰጡት የመጀመሪያ ሃሳባቸውን በመቃወም ከአቡነ ህዝቅኤል ወቀሳ እንደተሰነዘረባቸው አልሸሸጉም፡፡

በቀጣይ አሜሪካ ሬዲዩ ለድጋሚ ጥያቄ ለፕሬዚዳንቱ ያደረገው የስልክ ጥሪ “እኔ የፖለቲካ ጉዳያቸው ልዩ አማካሪያቸው ነኝ” በማለት አቶ አሰፋ ከሲቶ ጉዳዩን አስመልክቶ የሰጡት መልስ ዳላስ በተደረገው ድርድር የአገርቤት ተወካዮች የሚይዙትን አቋም አስቀድሞ ያንጸባረቀ ነው፡፡

የመንግሥት አቋም ምን እንደሆነ የተናገሩት አቶ አሰፋ፤ አቡነ መርቆሪዮስ ወደአገራቸው መግባት እንደሚችሉ፤ ፍላጎት ካላቸው ለርዕሳነ ፓትሪያርክነት መወዳደር መብታቸው እንደሆነ፤ ቀደም ሲል የተወሰነላቸውን ውሳኔ ተግባራዊ ከማድረግ አኳያ መንግሥት ተቃውሞ እንደሌለው ጨምረው አብራርተዋል፡፡

በዚሁ ሬዲዮ አስተያየታቸውን እንዲሰጡ የተጠየቁት አቡነ ህዝቅያስ ፕሬዚዳንቱ ስለተናገሩት ሲጠየቁ ያስቀደሙት “ኢህአዴግ ስለሾማቸው ፕሬዚዳንቱ መዘላበድ አይችሉም” በማለት የፕሬዚዳንቱን ንግግርና አካሄድ በማውገዝ ነበር፡፡

ፕሬዚዳንቱ በጻፉት ደብዳቤ መንግሥትም መቆጣቱን ያስታወቁት አቡነ ህዝቅኤል፤ አቡነ መርቆሪዮስ ሟቹ አቡነ ጳውሎስ ፓትሪያርክ ከመሆናቸው በፊት የተወሰነላቸውን ተግባራዊ ከማድረግ ውጪ አዲስ ነገር እንደሌለ ተናግረዋል፡፡ አቡነ ህዝቅኤል እንዳሉት አቡነ መርቆሪዮስ በመረጡት ቦታ አስፈላጊውን ሁሉ ተሟልቶላቸው ለአገራቸው አፈር እንዲበቁ ከተወሰነው ውጪ የሚደረግ ነገር እንደሌለ ጨምረው አስታውቀዋል፡፡

ከመንግሥትና ከአገርቤት ሲኖዶስ በኩል ያለው ተመሳሳይ አቋም እየተገለጸ ባለበት ወቅት በውጪ ባለው ስደተኛው ሲኖድና በአገርቤቱ ሲኖድ መካከል አራት አራት ተወካዮች ያካተቱበት ድርድር እየተካሄደ ነበር፡፡ በድርድሩ መጨረሻ ሁለቱ አካላት በጋራ ባወጡት መግለጫ አንኳር ጉዳይ ከላይ የተቀመጠው የውሳኔ ሃሳብ ላይ የሚያጠነጥን ነው፡፡ በውጪ አገር የሚኖረው ሲኖዶስ አቡነ መርቆሪዮስ አገር ቤት ከነሙሉመንበራቸው ይመለሱ ሲል የአገርቤቱ ደግሞ ደግሞ ከላይ የተጠቀሰውን የመንግሥትንና የወከላቸውን ሲኖዶስ መሰረታዊ አቋም ከማስጠበቅ የዘለለ ነገር አላቀረበም፡፡ አብዛኛዎች የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቀኖና ሊከበር ነው፤ መንግሥትና አገር ቤት ያለው ሲኖዶስ የህዝብን ፍላጎት ሊያስተናግዱ የተዘጋጁ ይመስላሉ በሚል አስቀድመው ሙገሳና ምስጋና ያቀረቡለት ድርድር ዋናውን ጉዳይ አስቀምጦ ቀጣዩንና አራተኛውን ድርድር ከጥር 16 እስከ ጥር 18፤ 2005ዓም (January 24 – 26, 2013) በሎስ አንጀለስ ከተማ፤ ካሊፎርኒያ ጠቅላይ ግዛት ለማድረግ ቀጠሮ ይዞ ተለያይቷል፡፡

አስተያየት ሰጪዎች ከሙስሊሙ ማኅበረሰብ ጋር አጣብቂኝ ውስጥ የገባው ኢህአዴግ ከወትሮው በተለየ የአቡነ መርቆሪዮስን ጉዳይ የሚያስታምመው እንደሌሎች የፖለቲካ ድርድሮች ሰጥቶ መቀበል ወይም ውጤትን በእኩል መጋራት (win-win) የሚባል አማራጭ ስለሌለው ነው ይላሉ፡፡ በዚህም ምክንያት አገር ቤት ቤተክህነት አካባቢ ያሉትን የመንግሥት ወዳጆች እና ህዝበክርስቲያኑን ላለማስከፋት መለሳለስ የመረጠው ለዚህ ነው የሚል አስተያየት ሰጥተዋል፡፡

የመግለጫው ሙሉ ቃል ይህ እዚህ ላይ ይገኛል፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule