• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኢህአዴግ ኢህአዴግን ማፈን ጀመረ!

November 22, 2012 12:01 pm by Editor 1 Comment

የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ስም ሲነሳ አቶ በረከት ስምዖን በግንባር ቀደም ይጠቀሳሉ። የአቶ በረከት ንብረት ሆኖ የመለስን አመራር በታማኝነት ሲያገለግል የኖረው ይህ ተቋም ቆርጦ በመቀጠል፣ የዜጎችን ሃሳብ በማዛባት፣ ወሬን ባለማመጣጠንና የሃሰት ፕሮፓጋንዳ በማስተላለፍ የሚታወቅ ነው። ስለሚጠየፉት የማይመለከቱት እንዳሉ አፍ አውጥተው የሚናገሩም አሉ።

ለሙያው ቅርብ የሆኑ አስተያየት ሰጪዎች “ወገንተኛ እንኳን ቢኾን መሰረታዊ የሙያው ግዴታ ሳይጣስ ሊሆን ይገባል። አንድ መገናኛ ማመጣጠን ካልቻለ በራሱ ሙት ነው። እያደር ብቻውን ይቀራል” ሲሉ ኢቲቪን ይገልጹታል። እንደነሱ አባባል ኢቲቪ ከህዝብ ሳይሆን ከራሱ ጌቶችም ጋር ተነጥሎ የአንድ ወገን (ግለሰብ) ሎሌ የሆነ በድርጅት ቅርጽ የሚከላወስ ሱቅ በደረቴ አይነት ነው።

ኢቲቪ ሃሳባቸውን፣ ንግግራቸውን፣ አቋማቸውን፣ ጥቆማቸውንና ተቃውሟቸውን እየቀረጸ በማዛባት ከህዝብና ከሚወዱዋቸው ወገኖቻቸው ጋር እሳትና ጭድ ያደረጋቸው፣ ለተራ የፖለቲካ መጠቀሚያ ሰለባ የሆኑ ወገኖች ኢቲቪን “በደለን” በማለት መውቀስ የሚችሉበት አግባብ የላቸውም። ኢቲቪ “በአልቤርጎ ውለታ” የግል ሳሎናቸው ያደረጉትን ጨምሮ “ልማታዊ” የሚባሉት በግብር ጸረ ልማት የሆኑ ውስን ጋዜጠኞች ሎሌ ሆነው እንዳሻቸው የሚንፈላሰሱበት ቤት ስለሆነ ጠያቂም ከልካይም እንደሌለባቸው ስለ ተቋሙ የሚያውቁ ይመሰክራሉ።

ተቋሙ ከድርጅት ደረጃም ወርዶ የግለሰብና የተወሰኑ ቡድኖች መፈንጫ እንደሆነ በየጊዜው አስተያየት ቢሰጥም ማንም ደፍሮ ሊያስተካክለው አልቻለም። ኢህአዴግ መንግስት ከሆነበት ጊዜ ጀምሮ አቶ በረከት ብቻቸውን የሚጋልቡት የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ጡንቻው የራሱን የኢህአዴግ ከፍተኛ የሚባሉትን ባለሥልጣናት ድምጽ የማፈን አቅም ያለው መሆኑ በእጅጉ አነጋጋሪ ሆኗል።

ከፍተኛ ባለሥልጣናት በጠ/ሚኒስትር ጽ/ቤት ያካሄዱት ስብሰባ ለህዝብ ይቀርባል ከተባለ በኋላ መታፈኑ ባለሥልጣናቱን ሳይቀር አስቆጥቷል። ካለፉት ሁለት ወራት ጀምሮ አወዛጋቢና አነጋጋሪ ዜናዎችን የሚዘግበው ሰንደቅ ጋዜጣ “ለህዝብ ይፋ ይሆናል” ተብሎ ማስታወቂያ የተነገረለት ስርጭት በማን ትዕዛዝ ታፈነ የሚለው ጉዳይ ባለስልጣናቱን እንዳበሳጫቸው ጠቅሶ ሰፊ ሪፖርት ይፋ ሲያደርግ አንድ የሥራ ኃላፊ ከማናገሩ ውጪ ወደ ላይ ከፍ ብሎ አላነጣጠረም።

ሰንደቅ ጋዜጣ 8ኛ ዓመት ቁጥር 376 ረቡዕ ህዳር 12 ቀን 2005 በፌስ ቡክ ባሰራጨው ዜና ስብሰባውን በመከታተል ሪፖርት ያዘጋጀው ጋዜጠኛ አዲሱ መሸሻን በማነጋገር “የባለሥልጣናቱ ውይይት የታፈነው ሆን ተብሎ ነው” በማለት ምላሽ መስጠቱን እንደሚከተለው አስነብቧል።

የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ባልደረባ የሆነው ጋዜጠኛ አዲሱ መሸሻ በዕለቱ ዝግጅቱን እንዲከታተል ተመድቦ ዜናው ከስድስት ደቂቃ ተኩል በላይ ሠርቶ በዕለቱ መተላለፉን፣ የዜናው ይዘትም አዎንታዊ ግብረ-መልስ ከውይይት ተሳታፊዎች እንደነበረው አስታውሷል። ይኸው የባለሥልጣናት ውይይት ሰፋ ባለ ፕሮግራም እንዲዘጋጅም ከድርጅቱ የሥራ ኃላፊዎች መታዘዙንና ይህንንም ተከትሎ በማግስቱ ቅዳሜ ዕለት ሰፊ ፕሮግራም አዘጋጅቶ እሁድ እንደሚተላለፍ የሚገልፀውን ማስታወቂያ (ስፖት) ሠርቶ አስረክቦ በግል ጉዳይ እረፍት መውሰዱን አስታውሷል።

ሆኖም እሁድ ጥቅምት 25 ቀን 2005 ዓ.ም ይተላለፋል የተባለው ፕሮግራም እሱ ለጊዜው ባላወቀው ምክንያት ሳይተላለፍ መቅረቱን፣ ነገር ግን ስብሰባውን በአካል ተገኝቶ ያልተከታተለው አቶ ሳሙኤል ከበደ በተባለ ባልደረባው አማካይነት ቀደም ሲል አዘጋጅቶት የሄደው የተሟላ ፕሮግራም ተጥሎ፣ ሆን ተብሎ የባለሥልጣናቱ ሃሳቦች ተቆራርጦ ማክሰኞ ጥቅምት 27 ቀን 2005 ዓ.ም እንዲተላለፍ መደረጉን ገልጿል።

ጋዜጠኛ አዲሱ “የባለሥልጣናቱ ውይይት የመንግሥት አቋም እንጂ የግለሰብ አይደለም። እኔ ጉዳዩን የተከታተልኩት ባለሙያ እያለሁ፣ ሳይነገረኝና ሳላውቅ ያዘጋጀሁት ፕሮግራም ተጥሎ፣ ተዛብቶና ተቆራርጦ እንዲቀርብ በመደረጉ ኃላፊነቱን መውሰድ ያለበት ጋዜጠኛ ሳሙኤል ከበደ እንጂ ተቋሙ አይደለም” ማለቱን የሰንደቅ ዘገባ ያስረዳል።

የጎልጉል የአዲስ አበባ ሪፖርተር ያነጋገራቸው የኢቲቪ ምንጮች እንዳሉት ጋዜጠኛ አዲሱ መግለጫውን እንዲሰጥ ከበላይ ትዕዛዝ ወርዶለታል። የባለሥልጣናቱ ውይይት ሙሉ በሙሉ ለህዝብ ይተላለፋል ከተባለ በኋላ አለመተላለፉ፣ በማስቀጠልም ፕሮግራሙ ተቆራርጦ መቅረቡ ካበሳጫቸው ባለሥልጣናት መካከል አቶ አባይ ጸሃዬ ኢቲቪ ማብራሪያ እንዲሰጥ መጠየቃቸውን እንደሚያውቁ የጠቆሙት ምንጮች “ፕሮግራሙ ተዛብቶ እንዲተላለፍ ትዕዛዝ የተቀበሉት ሃላፊዎች መመሪያውን ከማን እንደሚቀበሉ ይታወቃል” ብለዋል።

አቶ በረከትን በቀጥታ ያልገለጹት የኢቲቪ ሰዎች፤ “ኢቲቪ ውስጥ ከፍተኛ ጉዳዮች እርሳቸው ሳያውቁት አይተላለፉም። ጨዋታው ኢህአዴግ ኢህአዴግን ማፈን ጀመረ የሚያስብል ነው” በማለት ባለሥልጣናቱ ላይ ሲደርስ አዲስ ሆነ እንጂ በርካታ ዜጎች በተመሳሳይ ሃሳባቸው እየተዛባ ለፖለቲካ ቅስቀሳ እንዲውል ሲደረግ ማየት የተለመደ መሆኑን አስታውቀዋል። ኢቲቪ ከድርጅትም ወርዶ የግለሰብ “ሎሌ” እንደሆነ ሲነገር ለሚሰሙ ባለሥልጣናት ከዚህ በላይ ማስረጃ ሊቀርብ እንደማይችልም አመልክተዋል።

አሊ ሱሌማን

ጥቅምት 23 ቀን 2005 ዓ ም በተካሄደው የከፍተኛ ባለሥልጣናት ውይይት ላይ ባለሥልጣናቱ ምን ቢናገሩ ነው ድምጻቸው እንዲታፈን የተደረገው የሚለው ጉዳይ አነጋጋሪ ሆኗል። በውይይቱ ወቅት ባለሥልጣናቱ ጠንካራና ባለሥልጣናትን እየለየ የሚያሳጣ አስተያየት መስጠታቸው፣ የጸረ ሙስና ኮሚሽነር አቶ አሊ ሱሌማን ኮሚሽኑ መረጃ ቢኖረውም ከሶ እንዳያስፈርድ ጫና እንዳለበት ለተሰነዘረባቸው ወቀሳ ምላሽ ሰጥተዋል። ህዝብ መማረሩና ሰሚ ማጣቱ፣ አደገኛ የማህበራዊና ኑሮ ውድነት ቀውስ መከሰቱ፣ የመንግስትን “ሌቦች” ለመቆጣጠር የተቋቋሙ መዋቅሮች ቅርንጫፎቹን እንጂ ግንዱን ገንድሰው ሊጥሉ አለመቻላቸው፣ የግንዱን ግድግዳ መገርሰስ ካልተቻለ ግንዶቹ እንደሚጠነክሩ፣ ኢህአዴግ ለራሱ ሲል ግንዱን መገርሰስ እንደሚገባው … ይህን ማድረግ ካልተቻለ አደጋ እንደሚሆን ከተለያዩ ባለስልጣናት ሃሳብ ተሰጥቷል።

“የግንዶቹን በር በርግዶ መግባት አልተቻለም” በማለት አቶ አባይ ጸሃዬን በመደገፍ የወደፊት የአቶ መለስ ምትክ እንደሚሆኑ የሚነገርላቸው የመገናኛና የኢንፎርሜሽን ሚኒስትሩ አቶ ደብረ ጽዮን ገ/ሚካኤል “ጊዜ መስጠት የለብንም።በዚህ ከቀጠለ አደገኛ ነው” ሲሉ ስርዓቱን እየበላው ያለውን የሙስናና መበስበስ አደጋ አመላክተዋል። የአዲስ አበባ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ “የችግሩ ምንጭ መዋቅራችን ነው” ሲሉ፣ ምክትል ጠ/ሚኒስትር ደመቀ መኮንን በበኩላቸው “ሰፊ ተጠያቂነት ይካሄዳል” ማለታቸው ተደምጧል።

ደብረ ጽዮን ገ/ሚካኤል

ዘጠነኛው መደበኛ ጉባኤውን ለማካሄድ በዝግጅት ላይ ያለው ኢህአዴግ፣ እናት  ፓርቲዎቹና አጋር ፓርቲዎቹ በተናጠል ባካሄዱት ተከታታይ ግምገማ በተመሳሳይ ሰዉ ድርጅቱን አልቀበልም ስለማለቱ፣ በልማት ሰራዊት ግንባታ ስም ለቀረበው የመደራጀት ጥያቄ አዎንታዊ መልስ መከልከሉ፣ በአባላትና በካድሬዎች መካከል የመጠራጠርና የመከዳዳት ስሜት መጎልበቱ፣ ከሁሉም በላይ ሙስና ከቁጥጥር በላይ መሆኑ ስርዓቱን አደጋ ላይ እንደጣለው ከተሰብሳቢዎቹ መሰንዘሩ ተደምጧል። የየፓርቲው መሪዎችም በተመሳሳይ ችግር እንዳለ መልሰው ለካድሬውና ለበታች አመራሩ ማስተጋባታቸው ችግሩን ማን ይፍታው በሚል ጥያቄ እንዲያነሱ እንዳስገደዳቸው አስተያየት እየተሰጠ ነው።

ኢህአዴግ ባለስልጣናትን ሆን ብሎ በሙስና በማበስበስ “አቋም የሌላቸው ታዛዥ” እንደሚያደርጋቸው፣ እንዲህ ያለው ተግባር አገርንና ራሱን ኢህአዴግን ወደ “ታላቁ” ጉድጓድ እንደሚነዳቸው ከወራት በፊት “መለስ የቆፈሩት ጉድጓድ” በሚል ርዕስ ከጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ጋር ቃለ ምልልስ ያካሄዱ አንድ የኢህአዴግ አመራር ማስታወቃቸው አይዘነጋም። በቃለ ምልልሱ ኢህአዴግ ስለመበስበሱ በስፋት የተወሳ ሲሆን በተለይም አቶ መለስ ካለፉ በኋላ ስርዓቱ እንዴት ሊፈረካከስ እንደሚችል ተመልክቷል። በተመሳሳይ ከወር በፊት ሪፖርተር ጋዜጣ በርዕሰ አንቀጹ ኢህአዴግ ከፍተኛ በሚባል የንቅዘትና የመውደቅ አደጋ እንደተጋረጠበት በመጠቆም ከወዲሁ መስተካከል ስላለባቸው ጉዳዮች ማሳሰቢያ መስጠቱም ይታወቃል።

(ሐብታሙ ሂካ ያምቦ፤ Habtamu Hiikaa Yaamboo; habtamu@goolgule.com)

ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

ከእሁድ እስከ እሁድ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: abay, bereket simon, etv, Full Width Top, meles, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. anoole says

    November 22, 2012 03:27 pm at 3:27 pm

    be nathanat ye masebebat gezena wakat nafakagn

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule