• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ምርጫው አዲስ “ጠቅላይ ሚ/ር” አግኝቷል

May 8, 2015 08:42 am by Editor 2 Comments

በሊቢያ ታፍነው የነበሩ ወደ 30 የሚጠጉ ኢትዮጵያውያን በግብጽ ጦር ኃይል ነጻ አውጪነት መለቀቃቸውን የግብጽ መንግሥት አስታወቀ፡፡ የግብጹ ፕሬዚዳንት አልሲሲ የተለቀቁትን ኢትዮጵያውያን አውሮፕላን ማረፊያ ድረስ በመገኘት አቀባበል አደረጉላቸው፡፡ ኢህአዴግ እንደተለመደው “የተለቀቁት ኢትዮጵውያን መሆናቸውን አጣራለሁ” እንደማይል ተገምቷል፡፡ “ተይዘን የነበረው በሊቢያ የኢሚግሬሽን ባለሥልጣናት ነበር” ከተለቀቁት አንዱ ኢትዮጵያዊ፡፡

በተለያዩ የዓለም መገናኛ ብዙሃን ሐሙስ በተሰራጨው የዜና መረጃ መሠረት በሊቢያ ደርና እና ምስራታ በተባሉ ከተሞች ታፍነው የነበሩ 30 የሚደርሱ ኢትዮጵያውያን በግብጽ ጦር ኃይል እና በሊቢያ ድጋፍ ነጻ መለቀቃቸው ተሰምቷል፡፡

ዜናውን ከካይሮ አውሮፕላን ማረፊያ የግብጽ የዜና አውታሮች በቀጥታ ለአገራቸውና ለዓለም ሕዝብ እንዲሰራጭ አድርገውታል፡፡ ኢትዮጵያውያኑን የጫነው የምስር (አልምስሪያ) አውሮፕላን መሬት ሲነካ ከፓይለቱ ክፍል አካባቢ የግብጽ ሰንደቅ ሲውለበለብ ተመልክቷል፡፡ ቀጥሎም የተለቀቁት ከአውሮፕላኑ ከመውጣታቸው በፊት የግብጹ ፕሬዚዳንት አብደል ፈታህ አልሲሲ እስኪመጡ እንዲጠብቁ ተደረገ፡፡ እርሳቸውም እንደደረሱ ኢትዮጵያውያኑ የግብጽን ሰንደቅ እያውለበለቡ ሲወጡ ፕሬዚዳንቱ እያንዳንዳቸውን “እንኳን ለምስር አፈር አበቃችሁ” በሚል ፈገግታ እየጨበጡ ተቀብለዋቸዋል፡፡

“ከጥቂት ሳምንታት በፊት ኢትዮጵያውያን በግፍ ከታረዱ በኋላ በዚያ ስለሚገኙት ኢትዮጵያውያን ወንድሞቻችን ሁኔታ ግብጽ በጥልቀት ስታስብ ነበር፤ ለዚህም ነው እነዚህ ኢትዮጵያውያን ወንድሞቻችን ወደቤታቸው እንዲመለሱ በጣም ጥረት ስናደርግ የነበረው” በማለት የቀድሞው የጦር ጄኔራል አልሲሲ እዚያው አየር ማረፊያው የተለቀቁትን ኢትዮጵያውያን ከኋላቸው አድርገው በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስረድተዋል፡፡

ይኸው ከሳምንታት በፊት በኢትዮጵያውያን ላይ የደረሰው አሰቃቂ ግድያ እጅግ ያሳመማቸው መሆኑን የተናገሩት ፕሬዚዳንቱ እነዚህን ኢትዮጵያውያን በህይወት አስለቅቆ ወደ ግብጽ ለማምጣት የተፈለገው ጥረት ሁሉ መደረጉን በንግግራቸው ገልጸዋል፡፡ “የግብጽ (የጦር ሠራዊትና የደኅንነት) አገልግሎቶች በዚህ ኢትዮጵያውያን ወንድሞቻችን በመከላከል፣ በማዳንና በማስለቀቅ ተግባር ተሳትፈዋል” ያሉት ፕሬዚዳንቱ “በሊቢያ የሚከሰተው ነገር ሁላችንንም ይመለከተናል” ብለዋል፡፡

ዜናው እንደተሰማ ለጎልጉል አስተያየታቸውን የሰጡ እንዳሉት “ከመጪው ምርጫ አኳያ ይህ የግብጽ ተግባር እና የፕሬዚዳንቱ ቁርጠኝነት እንዲሁም ደመላሽነት አብዱል ፈታህ አልሲሲ በመጪው ምርጫ ጠቅላይ ሚኒስትራችን ቢሆኑ ሳይሻል የሚቀር አይመስለኝም” በማለት ከአዲስ አበባ አካባቢ በላኩት ዋዛ አዘል መልዕክት አስታውቀዋል፡፡

የወገኖቻችን አሰቃቂ ግድያ እንደተሰማ “ኢትዮጵያውያን መሆናቸውን እያጣራን ነው” በማለት ሲያላግጥ የነበረው ኢህአዴግ ሦስት ቀን “ብሔራዊ ሃዘን” በማለት ቢያውጅም ከአንድ ቀን በላይ መቀጠል አለመቻሉ ብዙዎችን ያጠያየቀ ጉዳይ ሆኗል፡፡ ከዚህም ሌላ ደርግን “በጦርነትና በጀግንነት” አሸንፈን “ነጻ አወጣን”፣ “ተራራ ያንቀጠቀጠ ትውልድ” ነን የሚለው ህወሃት “ካስፈለገም ጦርነትን እንሰራለን” ሲል እንዳልኖረ ሁሉ 30ኢትዮጵያውያን በግፍ ከታረዱ በኋላ ምንም ዓይነት የጀግንነት፣ የአርበኝነት ወይም የጦረኝነት ምላሽ ቢያንስ እንኳን ለማሳየት አለመቻሉ ከመጀመሪያውኑ ባዶ ጀግንነት የተሸከመ በምዕራባውያን ድጋፍ የራሱን ወገን በመሸጥ ሥልጣን ላይ የተቀመጠ፤ ኢትዮጵያዊነት ስሜት፣ ኩራትና ወኔ የሌለው በከንቱ ጀብዱ የተሞላ ባዶውን የቀረ ቀፎ ድርጅት መሆኑን አስመስክሯል፤ ለዚህም ነው ለሃዘን የወጣው ሰልፈኛ “ያገር አንበሳ የውጭ ሬሳ” ብሎ የፈከረው በማለት ብዙዎች ለጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ አስተያየታቸውን ሲሰጡ ከርመዋል፡፡

ከዚህ ዜና ጋር በተያያዘ የግብጽ ሚዲያ ኢትዮጵያውያኑ ከታፈኑበት ተለቀቁ ቢልም ከተፈቱት መካከል አስተያየቱን የሰጠ አንድ ኢትዮጵያዊ እንደተናገረው ተይዘው የነበረው በሊቢያ የጸረ ሕገወጥ ኢሚግሬሽን አካል እንደነበረና የግብጽ መንግሥት መጥቶ እንዳስለቀቃቸው ተናግሯል፡፡

ከፕሬዚዳንት አልሲሲ ጽ/ቤት የተለቀቀው መረጃ እንደጠቆመው ፕሬዚዳንት ሲሲ “የመጀመሪያውን ዙር ከሊቢያ ተመላሽ ኢትዮጵያውያን ወንድሞችን” መቀበላቸውንና ይህም በቀጣይነት የሚካሄድ ዘመቻ መሆኑን አመላክቷል፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Yite says

    May 10, 2015 11:35 pm at 11:35 pm

    Ewunetegna yehagerna yewegen fikr yalew zega yinur.
    ENE KEMOTKU SERDO AYBKEL SEWOCH BEIHADIG MERIWOCH lay silemitay

    Reply
  2. በለው ! says

    May 11, 2015 05:17 pm at 5:17 pm

    >>> የግብጹ ፕሬዚዳንት አልሲሲ በሊቢያ ታፍነው የነበሩ ወደ 30 የሚጠጉ ኢትዮጵያውያን በግብጽ ጦር ኃይል ነጻ አውጪነት በመለቀቃቸው የተለቀቁትን ኢትዮጵያውያን አውሮፕላን ማረፊያ ድረስ በመገኘት “እንኳን ለምስር አፈር አበቃችሁ” በማለት በፈገግታ እየጨበጡ አቀባበል አደረጉላቸው፡፡ያስለቀቁት የግብፅ ወታደሮችና የግብፁ ፕ/ት አብድል ፈታህ አልሲስ ግብፅም እራሷ ቀድሞውንም ኢትዮጵያ እንደነበሩ እናጣራለን!? እንግዲህ የሊቢያ ኢምግሬሽን ይሁን የኢህአዴግ ደላላ ወይንም እራሳቸው ግብፆች ያገቷቸውና ለፖለቲካ ድምቀት የሰሩትም ትዕይንት ከሆነም ይጣራል!።
    *****
    “ደርግን “በጦርነትና በጀግንነት” አሸንፈን “ነጻ አወጣን”፣ “ተራራ ያንቀጠቀጠ ትውልድ” ነን የሚለው ህወሃት “ካስፈለገም ጦርነትን እንሰራለን” ሲል እንዳልኖረ ሁሉ 30ኢትዮጵያውያን በግፍ ከታረዱ በኋላ ምንም ዓይነት የጀግንነት፣ የአርበኝነት ወይም የጦረኝነት ምላሽ ቢያንስ እንኳን ለማሳየት አለመቻሉ ከመጀመሪያውኑ ባዶ ጀግንነት የተሸከመ በምዕራባውያን ድጋፍ የራሱን ወገን በመሸጥ ሥልጣን ላይ የተቀመጠ፤ ኢትዮጵያዊነት ስሜት፣ ኩራትና ወኔ የሌለው በከንቱ ጀብዱ የተሞላ ባዶውን የቀረ ቀፎ ድርጅት መሆኑን አስመስክሯል፤” ይልቁንም የሕዝብን አመፅና ብሶት ‘እንደ ትኩስ ድንች’ ሲፈጀው ሕጋዊ ደላሎች አነማን? ምን እደሰሩ? ለፓርቲው የሰጡትን የገንአብ መጠን ሳይናገር “በሕገወጥ ደላላና ሰማያዊ ተፎካካሪ ፓርቲ ላይ ጣለው …
    *******
    ** በመሠረቱ ህወአት/ወያኔ.ኢህአዴግ ልመታዊ አትረፊ ደርጅት ነው…የድሃ ልጅ ይገላል እንጂ ያለትርፍ አይሞትም ከሱማልያና ደቡብ ሱዳን የባሪያ አሳዳሪዎቻቸውን የግል ጥቅም ለማስከበር ኢንቨስትመንታቸውን ለመንከባከብ ግን የወሰደና ያስበላው የድሃ ገበሬ ልጅ ቁጥር አይታወቅም! አይነገርም! አይጠቅም!..ሻእቢያ የቀጠናው አታራማሽ ሲሆን ህወአት የቀጠናው ሰላም አስከባሪ ሆኖ ኢህንን ነጭ.. በነጭ ወሬ..በቢጫ ጋዜጠኛና ልማታዊ አርቲስት ዳንኪራ ታጅቦ ሞኖፓሊያቸውን በማስፋፋት ይቦጠቡጣሉ። ለዚህም ሥልጣን አስከባሪዎች የጋራ ድርሻቸውን(ኮሚሽናቸውን) በታላቁ ባለሀብት(ሺክ አላሙዲን) ሥም በእጅአዙር ይቀበላሉ፡ ኢህአዴግና ቤተሰቦቻቸው ያለባቸውን ብድር ከፍለው እስኪያገባድዱ የሀገሪቱን ግማሽ የልማት ቦታ ለሃያ ዓመት አጥረው በመያዣ ያስቀምጣሉ..አብዮታዊ(ፖለቲካ) ልማታዊ(ገንዘብ) ዴሞክራሲያዊ (ወሬ) ታጅቦ አጀይብ ያሰኘ ወሮ በላ ቡድን!!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm
  • የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት? January 23, 2025 03:41 pm
  • ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ? January 23, 2025 03:04 pm
  • የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተወልደ አስተዳደር ዘመን ለተሠራ ስህተት 425ሺ ዶላር ተቀጣ December 14, 2024 01:44 am
  • በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል November 27, 2024 12:09 pm
  • የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን እንዲያርም ጥብቅ መመሪያ ተሰጠው November 27, 2024 11:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule