• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ድርብ አኃዝ ዕድገት ወይስ ድርብ ድህነት?

June 21, 2014 06:49 am by Editor 10 Comments

በኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ የዓለምአቀፍ ልማት ትምህርት ክፍል ሥር የኢኮኖሚ ጥናት የሚያካሂደው የኦክስፎርድ የድህነትና የሰብዕ ልማት ማዕከል (The Oxford Poverty and Human Development Initiative (OPHI)) ሰሞኑን ባወጣው የ2014 የጥናት መረጃ ደሃ ከሚባሉት አገራት ዝርዝር ኢትዮጵያ ከመጨረሻው ሁለተኛ መሆኗን ገለጸ፡፡ የጥናቱ ዘገባ ኢህአዴግ በየጊዜው ከሚያቀርበው የዕድገት ስሌት ጋር በግልጽ የሚጋጭ መሆኑ ተነገረ፡፡

በዓለማችን በሚገኙ 108 በማደግ ላይ ባሉ አገራት በየጊዜው ጥናት የሚያካሂደው ማዕከል ጥናቱን በሚያካሂድበት ጊዜ 10 መለኪያዎችን እንደ ግብዓት እንደሚጠቀም ይናገራል፡፡ እነዚህም በሦስት ዘርፎች የተጠቃለሉ ናቸው – ትምህርት፣ ጤና እና የኑሮ ሁኔታ፡፡ በተለይ በኑሮ ሁኔታ ሥር ኤሌክትሪክ፣ ጽዳት፣ የሚጠጣ ውሃ፣ የንብረት ባለቤትነት፣ ወዘተ በግብዓትነት ተወስደዋል፡፡

በዚህ ዓይነት እኤአ ከ2002 እስከ 2011 ድረስ ያለውን መረጃ በማጠናቀር በወጣው ዘገባ መሠረት በኢትዮጵያ ውስጥ ከ100 ሰዎች መካከል 87ቱ ድሃ ተብለው የሚጠሩ ሲሆን 58ቱ ሰዎች ግን መናጢ ደሃ ተብለው የሚጠሩ መሆናቸውን ይናገራል፡፡ ድህነቱ በገጠር እጅግ የከፋ እንደሆነ በመጠቆም ከ100 ሰዎች ውስጥ 96ቱ ደሃዎች እንደሆኑ፤ በከተሞች አካባቢ ግን ከ100 ሰዎች መካከል 46ቱ ደሃ ተብለው የሚጠሩ መሆናቸውን ያስረዳል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በአጠቃላይ የአገሪቷ ክፍሎች ከ100 ሰዎች መካከል 31ዱ በቀን ከ20ብር በታች በሚገኝ ገቢ እንደሚኖሩ ጠቁሟል፡፡

ድህነቱ የከፋባቸው “ክልሎች” ብዙም ልዩነት እንደሌላቸው የሚያሳየው የጥናቱ ዘገባ ከሁሉም ግን ሶማሊ በደሃነት ቀዳሚ ነው፡፡ በጥቂት ነጥብ ልዩነት ኦሮሚያ፣ አፋር፣ አማራ፣ ቤንሻንጉል ጉሙዝ በቅደም ተከተል ተቀምጠዋል፡፡ በእነዚህ አምስት ክልሎች ከ100 ሰዎች ውስጥ 90 እና ከዚያ በላይ የሚሆኑት ደሆች መሆናቸው በጥናቱ ተዘርዝሯል፡፡

የ108 በማደግ ላይ ያሉ አገራት የድህነት መለኪያ ዝርዝር የያዘው ዘገባ በግልጽ እንደሚያሳየው የመጨረሻዋ ደሃ አገር ኒጀር ስትሆን ከዚያ ቀጥላ ኢትዮጵያ ነች፡፡ እስከ 10 ባሉት የመጨረሻ አገራት ውስጥ ማሊ፣ ቡርኪናፋሶ፣ ላይቤሪያ፣ ጊኒ፣ ሶማሊያ፣ ቡሩንዲ፣ መካከለኛው አፍሪካ እና ጊኒ ቢሳው ከ3 – 10 ደረጃ ላይ ይገኛሉ፡፡

በየጊዜው የኢትዮጵያ ዕድገት “ድርብ አኻዝ” እንደሆነ ለሚናገረው ኢህአዴግ ይህ ዓይነቱ ዓለምአቀፋዊ ዘገባ የከፋ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር በአስተያየት ሰጪዎች ዘንድ ይነገራል፡፡ በተለይ “ምርጫ” እየቀረበ ባለበት ወቅት ይህ ዓይነቱ በታዋቂ ዩኒቨርሲቲ የሚመራ ማዕከል የወጣ የጥናት ዘገባ የሚያመጣው ተጽዕኖ ከፍባለ ሁኔታ ለመጠቀም ተቃዋሚ ፓርቲዎች በቂውን ዝግጅት ማድረግ እንደሚገባቸው እነዚሁ ወገኖች ይናገራሉ፡፡ ኢህአዴግ የማይስማማውን ማንኛውንም ዓይነት ዘገባ “የልማት ጸሮች” ያወጡት፣ “የአሸባሪዎች እጅ ያለበት”፣ “የኒዎ ሊበራል አቀንቃኞች ዘገባ”፣ “የኪራይ ሰብሳቢዎች ምኞት”፣ ወዘተ እያለ እንደሚያጥላላውና እንደሁኔታው የተለመደውን “ማጣፊያ” በኢቲቪ ወይም ሌሎች ድቃይ “የሚዲያ” ክፍሎች ላይ እንደሚያቀርብ ጎልጉል አስተያየት የጠየቃቸው በኢትዮጵያ የከፍተኛ ተቋም ምሁር ገልጸዋል፡፡

ይህ የኦክስፎርድ ማዕከል ይህንን ጨምሮ በየጊዜው የሚያቀርባቸው የጥናትና ምርምር ውጤቶች በበርካታ ዓለምአቀፋዊ ድርጅቶች፣ በፖሊሲ አውጪዎች እንዲሁም የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም (UNDP) እና ሌሎች ተመሳሳይ ተቋማት ጥቅም ላይ እንደሚያውሉት በድረገጹ ላይ አስታውቋል፡፡

የጥናቱን ዘገባ በPDF ለማግኘት እዚህ ላይ ይጫኑ፡፡ በቀጥታ ከማዕከሉ ድረገጽ ላይ ለማግኘት እዚህ ላይ ይጫኑ፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Fikreselassie says

    June 22, 2014 04:53 pm at 4:53 pm

    Please! If it is possible send the full text of research through this email address.

    Reply
    • Editor says

      June 26, 2014 07:07 am at 7:07 am

      We did but your email is not working. The email we sent you bounced back.

      Reply
  2. Belayneh Girmie says

    June 23, 2014 09:22 pm at 9:22 pm

    golguloch be FDRE mengist yewushet mora yetedekewn ewunet sitawetut libie yirsal. bertu!!!

    Reply
  3. Asnake Balcha Dedebe says

    June 24, 2014 01:00 am at 1:00 am

    የናንተ ዘገባ የኣገራችንን እውነተኛ ገፅታ ስለሚያሳይ ቀጥሉበት በርቱ።

    Reply
  4. Esubalew says

    June 25, 2014 10:52 am at 10:52 am

    I’m not goining to listen to such kind of foolishness, as i&my beloved country are on the right track!!

    Reply
  5. Zola zone says

    June 30, 2014 01:15 pm at 1:15 pm

    World Bank report is the standard to determine the economic level of countries. Do not forget that it was Oxford who give synonyms term to this country as poverty. No-one, even EPRDF, deny our impoverish status. But this is a very biased report because there is visible change in the country in terms of education, road construction, rail …….

    Ethiopia is on the right track despite challenges. What matters is not numbers but tangible facts on the ground .

    Reply
    • afufutu says

      June 30, 2014 11:02 pm at 11:02 pm

      good if you insult floosh one time he insult him self all his life

      Reply
  6. yonas says

    July 1, 2014 11:13 am at 11:13 am

    I’m here in Ethiopia and I can see the reality and other Ethiopians the same they can’t confused by this article It’s shame and immoral things to write this false and Idiot Article I don’t think It is political game it’s about a country I read many similar articles write by Eritreans .

    Reply
  7. hussein amanu says

    July 2, 2014 05:20 pm at 5:20 pm

    በርግጥም በኢትጵያ እድገት አለ ፡፡ ነገር ግን አድገቱን በተለያየ መንገድ መፈተሺ ያስፈልጋል፡፡ ለምሳሌ
     እድገቱ በሁሉም በኢትዮጵያ ዜጎች ተሰርቶ የመጣ ነው ወይ?
     ሁሉም የኢትዮጵያ ዜጎች ከእድገቱ ተጠቃሚ ሆነዋል ወይ?
     እድገቱ የመጣው በሁሉም የአኮኖሚ ዘርፍ ነው ወይ?
     እድገቱ በአገሪቱ ላይ ከዋጋ ንረት የፀዳ ነው ወይ?
     እድገቱስ ቀጣይነቱ ለምን ያህል ዓመት ተጠንቶ ተረጋግጧል ወይ? /ምክንያቱም 11.6 የነበረው ወደ 8 ዘቅ ብሏልና/
     ሁሉም የኢትዮጵያ ዜጎች በት/ት፣በጤና፣በውሃ፣በመልካም አሰተዳደር፣በእኩላዊነት ፍትህ፣ በቤት ባለቤትነት፣በጥሩ የስራ በህል፣አኩል የፖለቲካ ተሳትፎ እኩል ተደራሽ ሆነዋል ወይ?
    ስለዚህ እድገት ማለት የአስፋልት መንገድ መዘርጋት አሊያም የሰማይ ጠቀስ ህንፃ መገንባት በብቻውን የእድገት ምልክት እንጅ ያለቀለት 24 ሰዓት የሚደሰኩርለት እድገት አይመስለኝም፡፡ ለመሆኑ ኢትዮጵያንን የሚያደነጋግሩት በፓርላማ ላይ ″Growth″ እና ″Development″ የሚሉ ቃላቶችን እያቀያየሩ ስለሚጠቀሟቸው ይመስለኛል፡፡ የቃላቶቹን ልዩነትና አንድነት ሁሉም የአገሪቱ ዜጋ ቢገነዘባቸው ሰምና ወርቁን ይረዳ ነበር፡፡

    Reply
  8. weywne says

    August 21, 2014 03:40 pm at 3:40 pm

    bertu menager coment madrig alchalinim ayizon,

    Reply

Leave a Reply to Belayneh Girmie Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am
  • ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ September 7, 2023 01:40 pm
  • “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል” September 7, 2023 01:31 am
  • ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል August 24, 2023 11:50 pm
  • ጀብደኛው August 24, 2023 10:06 am
  • ጎንደርና ባሕር ዳር ከተሞች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው ተመልሰዋል August 13, 2023 10:55 pm
  • ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች August 13, 2023 10:26 pm
  • ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ August 13, 2023 09:11 pm
  • ወደ ኤርትራ በኮንትሮባንድ የሚሻገሩ ቆሳቁሶች እየተያዙ ነው August 11, 2023 12:52 pm
  • የአማራ ክልል ትልልቅ ከተሞች ተኩስ ዓልባ ሆነው ውለዋል August 10, 2023 04:31 pm
  • “አንድ ሰው ለመግደል ኅንፃውን ማቃጠል” የኢ-ዲሞክራሲና ጽንፈኛ ኃይሎች ቅዠት፤ (ክፍል ሁለት) August 10, 2023 09:44 am
  • “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ August 10, 2023 09:08 am
  • በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ August 9, 2023 11:47 am
  • ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ  August 8, 2023 05:47 pm
  • “ሃሳብ ሲነጥፍ ነፍጥ አንግቤ እዋጋለሁ” የሚሉ አካላት ላይ እርምጃ ይወሰዳል – የመከላከያ ሠራዊት August 1, 2023 09:25 am
  • ደቡብ አፍሪካ የመሸጉ ወንጀለኞች ለሕግ ተላልፈው ሊሰጡ ነው July 31, 2023 09:27 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule