• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በጥቁር ገበያ የዶላር ዋጋ በሰላሳ ሳንቲም መቀነሱ አነጋጋሪ እየሆነ ነው

May 23, 2013 03:29 am by Editor Leave a Comment

በአዲስ አበባ የሚገኙ የጥቁር ገበያ ባለድርሻዎች በከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት እና ታዋቂ ነጋዴዎች ከሙስና ጋር በተያያዘ ተጠርጥረው በመታሰራቸው በተፈጠረ መደናገጥ መነሻ ከፍተኛ የሆነ ኪሳራ እያጋጠማቸው መሆኑን ገልፀው፣ የዶላር ምንዛሪ በታሪኩ የሰላሳ ሳንቲም ቅናሽ አሳይቷል።

የከፍተኛ ባለስልጣናቱ በወንጀል የመጠርጠር ዜና ከመሰማቱ በፊት ሃያ ብር ከአርባ ሳንቲም የነበረው የዶላር ምንዛሪ ወደ ሃያ ብር ከአስር ሳንቲም በሳምንት ውስጥ ቀንሷል። በዚህ ቅናሽ ውስጥ አስደንጋጭ የሆነው ክስተት በማንኛውም አይነት ምንዛሪ መጠን ዶላር ወደላይ ሲጨምር ሆነ ሲቀንስ በሰላሳ ሳንቲም የልዩነት ምንዛሪ ውስጥ ወድቆ አለማወቁ መሆኑን ከስፍራው ያገኘነው መረጃዎች ያሳያሉ። በሙስና ከተጠረጠሩ ባለስልጣናት እና ነጋዴዎች ጋር በተያያዘ ይህ ልዩነት መፈጠሩ አብዛኛው የጥቁር ገበያ የዶላር ምንዛሪ ባለድርሻ አካላትን ማስደንገጡን ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ወገኖች ጠቁመዋል።

ባለፉት አራት ወራት ውስጥ ከፍተኛ የዶላር እጥረት በሀገሪቷ ሲከሰት የጥቁር ገበያ ባለድርሻ አካላት ከፍተኛ ተጠቃሚ መሆናቸውን ቢገለጽም፣ ከመንግስት እና ከግል ባንኮች ሰራተኞች የገጠማቸው ችግር ግን እጅግ ፈታኝ እንደነበር አስረድተዋል። ይህም ሲባል፣ ለአንድ የአሜሪካን ዶላር ከአንድ ብር እስከ አንድ ብር ከሃምሳ ሳንቲም የባንኩ ደንበኞች ክፍያ እየፈጸሙ ከፍተኛ መጠን ያለው የዶላር ምንዛሪ ከባንኮቹ ማግኘትን በአማራጭነት በመውሰዳቸው ወደ እኛ ከመምጣት ባንኮንችን ተመራጭ ያደርጉ ነበር። ሆኖም ከፍተኛ መጠን ዶላር የማይፈልጉ ደንበኞች በወቅቱ ስለነበሯቸው ከፍተኛ ተጠቃሚ መሆናቸውንም አልሸሸጉም።

በአሁን ሰዓት ከመንግስት ኪራይ ሰብሳቢ የተለያዩ ባለስልጣናት እና ነጋዴዎች ወደ እነሱ ይፈስ የነበረው የኢትዮጵያ ብር ለዶላር ምንዛሪ ከፍተኛ ጠቀሜታ የነበረው ከመሆኑ አንፃር አሁን የተፈጠረው ድንጋጤ በከፍተኛ ሁኔታ የጥቁር ገበያውን የዶላር ምንዛሪ ይጐዳዋል። የተፈጠረው ድንጋጤ ግለሰቦችን ሳይቀሩ ማሸማቀቁን ያነጋገርናቸው ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ወገኖች አረጋግጠዋል። በስፍራው የተገኙት መረጃዎችም የሚያሳዩት ከመንግስት ከፍተኛ ኪራይ ሰብሳቢ ባለስልጣናት ሰንሰለት ይፈስ የነበረው የኢትዮጵያ ብር ለጊዜ ተቀዛቅዟል። ሁኔታዎች በዚህ ከቀጠሉ የጥቁር ገበያው አደጋ ውስጥ መውደቁ አይቀርም የሚል ስጋት እንዳላቸው ገልፀዋል።

ለምን የኢትዮጵያ ብር ወደ ጥቁር ገበያ ይላካል?

በሙስና ውስጥ የተዘፈቁ የመንግስት ባለስልጣናት እና ተባባሪ የንግዱ ማሕበረሰብ አባላት ከሕግ አግባብ ውጪ የሚያገኙትን የኢትዮጵያ ብር በአዲስ አበባ ጥቁር ገበያ ውስጥ በዘረጉት ሰንሰለት ወደ አሜሪካ ዶላር ለውጠው ወደ ውጭ ሀገር እንዲወጣ በማድረግ ተጠቃሚ በመሆናቸው መሆኑን ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

በተለይ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት በዚህ መልኩ የሰበሰቡትን የአሜሪካ ዶላር በተሰጣቸው ያለመፈተሸ መብት በመጠቀም እና በገቢዎችና ጉምሩክ በዘረጉት የኪራይ ሰብሳቢ ሰንሰለቶች አማካይ ወደ ውጭ ይዘውት የሚወጡበት አሰራር ሊኖር እንደሚችል ግምታቸውን አስቀምጠዋል። የሰበሰቡትን የአሜሪካ ዶላር በሳምሶናዊት ቦርሳቸው ውስጥ በመጨመር እና ቦርሳውን ላይ ያለመፈተሽ መብት የሚያጎናጽፋቸውን ልጣፍ በመለጠፍ በቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ በቀጥታ ዶላሩን ይዘው የሚወጡበት ዕድል ከፍተኛ በመሆኑ ሊጠቀሙበት ይችላሉ ሲሉ ግምታቸውን ተናግረዋል።

በአስረጅነት ግምታቸውን ሲያስቀምጡ የገቢዎችና ጉምሩክ ምክትል ዋና ዳሬክተር የነበሩት አቶ ገብረዋህድ ወ/ጊዮርጊስ መኖሪያ ቤት የተገኘው 26ሺ የአሜሪካ ዶላር እና 19ሺ ዩሮ የአውሮፓ ሕብረት የመገበያያ ገንዘብ በዚህ መልኩ የተሰበሰቡ ሊሆን እንደሚችል ያላቸውን ግምት ገልፀዋል። አያይዘውም አንድ ግለሰብ ከ200 የአሜሪካ ዶለር ምንዛሪ ውጪ ይዞ መገኘት እንደማይችል በኢትዮጵያ ሕግ መስፈሩንም አስታውሰዋል። እንዲሁም በአቶ አስመላሽ ወ/ማሪያም መኖሪያ ቤት የተገኘውም አንድ ሚሊዮን የኢትዮጵያ ብር ወደ ዶላር ለመቀየር የተቀመጠ ገንዘብ ሊሆን እንደሚችል ከጥቁር ገበያ ያገኘነው ግምታዊ መረጃ ያሳያል።

ይህን መሰል ተግባር መፈጸም ትርጉሙ ብዙ ሊሆን ይችላል። በተለይ አንድ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣን በሀገር ውስጥ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ እጥረት መኖሩ እያወቀ የኢትዮጵያን ብር በዶላር እየመነዘረ ወደ ውጭ ሀገር በማስወጣት ተግባር ላይ ከተሰማራ እንደሀገር ትልቅ በደል መሆኑን መገንዘብ ሮኬት ሳይንስ አይሆንም። በዚህ መልኩ የተሰማሩ የመንግስት ባለስልጣናት በወፍ በረር ሲታይ፣ ዶላር ማሸሽ ቢመስልም በተግባር ግን ሲመነዘር የኢትዮጵያ መንግስትን እና ሥርዓቱን ቀስ በቀስ እየሸራረፉ ሊጨርሱት መዘጋጀታቸውን የሚያሳይ ነው። የፓርቲ ሹመኞቹን የመንግስትን ስርዓት ለዘረጋው ገዥ ፓርቲ ቢተውም፣ ተግባራቸው ግን ሕገ መንግስቱን በጠራራ ፀሐይ እየበጣጠሱት ስለመሆኑ አስረጂ አያስፈልገውም።

የገንዘብ ምንጩ ስትራቴጂ

እ.ኤ.አ. የሴፕቴምበር 11 ቀን 2001 የአሜሪካኑን የሽብር ጥቃት ተከትሎ ትንሹ ቡሽ ሴፕቴምበር 20 ቀን 2001 “WAR ON TERROR” በሚል መጠሪያ ዓለም ውስጥ የሚገኙ አሸባሪዎችን ለመደምሰስ ያስችላል በሚል አዲስ ስትራቴጂ ይዘው ብቅ አሉ። ቡሽ ቀጠል አድርገው በአሸባሪዎች ላይ የምንከፍተው ዘመቻ ‘የመስቀል ጦርነት’ ነው በማለት ለዓለም ሕዝብ በይፋ ተናገሩ።

ቡሽ ብዙም ሩቅ ሳይጓዙ በአደባባይ “የመስቀል ጦርነት” የሚለውን ቃል ተገቢ አይደለም፤ ከእስልምና እምነት ተከታዮች ጋር አወዛጋቢ ፍቺ ያመጣል በማለት በይፋ ይቅርታ ጠይቀዋል። ጦርነቱን የምንጀምረው በአልቃይዳ እና በእሱ የሽብር መረብ ከተያያዙ አሸባሪዎች ጋር ነው ሲሉ አቋማቸውን በግልፅ አስቀመጡ። ዓለም ከአሜሪካ ጎን ቆመ። ቡሽም፣ ‘ወይ ከእኛ ወይም ከእነሱ’ ጋር መሆንን ምረጡ ብለው ለዓለም ዓቀፉ ሕብረተሰብ ጥሪ አቀረቡ። ዓለምም በወቅቱ በጐ ምላሽ ሰጣቸው። ጦርነቱ እንደቀጠለ ነው። ኦሳማ ቢላደን ግን ከአስር ዓመት በኋላ ተገድሏል።

እዚህ ላይ ልብ ማለት ያለብን ቁምነገር፤ እንደቡሽ የመጀመሪያ አቀራረብ ቢሆን የተቀደሰውን የእስልምና እምነት ከሽብር ተግባር ጋር ጨፍልቆ ለማየት ያለመ ነበር። ሆኖም ቡሽ ፈጥነው አባባላቸው ስህተት መሆኑን አርመው በይፋ ይቅርታ ጠየቁ። ስለዚህም ነገሮች ለያይቶ ማየት እንጂ በአንድ ቅርጫት ውስጥ ወርውሮ አንድ መለያ መስጠት ተገቢ አለመሆኑ ከዚህ መረዳት ይቻላል።

በተነፃፃሪነት ሲታይ ደግሞ ገቢዎችና ጉምሩክ በቀድሞ ከፍተኛ አመራሮቹ በኩል የኢትዮጵያ ነጋዴዎችን በተለይ እዚህ አዲስ አበባ ውስጥ የሚገኙትን ነጋዴዎች በግብር ስም ሁሉም ነጋዴ ግብር አጭበርባሪ ኪራይ ሰብሳቢ በማድረግ ሽብር “TERROR ON TAX” በነጋዴው ላይ ረጩ። ነጋዴውም ግብር መክፈሉን ሳይሆን ለኪራይ ሰብሳቢ ወይም ለግብር አጭበርባሪ ታፔላን ላለመጋለጥ በሚል ብቻ የገቢዎችና ጉምሩክ ከፍተኛ ሃላፊዎች ተገዢ መሆኑ አረጋገጠ። በመጨረሻም በተፈበረከው የሽበር ማዕቀፍ ውስጥ ነጋዴው ወደቀ። ፍርሃት፣ ስጋት መለያው ሆነ።

ከዚህ በኋላ ከገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን የቀድሞ ከፍተኛ አመራሮቹ ጋር ተባብሮ መስራት የኪራይ ሰብሳቢዎች የህግ የበላይነትን ማረጋገጫ አድርጎ ተቀበለው። ለዚህ ማሳያ የሚሆነው መንግስት ከፍተኛውን የሙስና ወንጀል በራሱ መንገድ ደረሰበት እንጂ በአደባባይ በመውጣጥ ለማጋለጥ የደፈረ ታዋቂ ባለሃብት አንድም አልነበረም። በሕግ የማይነኩ በሚመስሉ የገቢዎችና የጉምሩክ ባለስልጣናት ጋር ሲራኮቱ የነበሩ ታዋቂ የከተማችን ባለሃብቶች ሕግ በራቸው ደጃፍ ሲመጣ ሌላ የፖለቲካ ዓላማ ያለው ተግባር እንጂ ሙስና አይመስለንም ሲሉ በአደባባይ በዘረጉት የኪራይ ሰብሳቢዎች የሙስና ሰንሰለት በመጠቀም ከተማውን እያሟሟቁ ይገኛሉ። እውነቱ ግን ሌላ ሆኖ ነው እየታየ ያለው።

ከዚህ ጋር በተያያዘ በባሕርዳር በተደረገ የኢሕአዴግ 9ኛው ጉባኤ ላይ ከተጋበዙ ባለሃብቶች መካከል አንዱ የከተማችን ባለሃብት ለጉባኤው ያቀረበው ጥያቄ አጠቃላይ መንፈሱ ሲታይ “የኪራይ ሰብሳቢ” መሰረታዊ ይዘት በመቀየር ወደ ‘ሽብር’ መለወጡን አመላካች ነው። ባለሃብቱ ጉባኤውን የጠየቀው እንዲህ ሲል ነበር፣ “የኪራይ ሰብሳቢ ፍቺው በጣም የተለጠጠ ነው። በትክክልም ምን እንደሆነ እንኳን ለመረዳት አዳጋች ነው። በጅምላ ሁሉም ነጋዴ በገባበት ቢሮ ውስጥ ኪራይ ሰብሳቢ እየተባለ ይሸማቀቃል። እኔ እራሴ አሁን ኪራይ ሰብሳቢ በሚባለው ፍቺ ኪራይ ሰብሳቢ ልሁን፣ አልሁን ማረጋገጥ እንኳን አልችልም” ሲል በነጋዴው ላይ የተለቀቀውን ሽብር ለጉባኤው አስረድቷል።

ቡሽም በጅምላ የሚካሄደው ጦርነት የመስቀል ጦርነት ነበር ያሉት። እሳቸው ግን በይፋ ይቅርታ ጠይቀዋል። የኢትዮጵያ መንግስትም ከንግዱ ማሕበረሰብ ጋር የበለጠ በመቀራረብ ለኪራይ ሰብሳቢዎች የተጋለጠውን የንግዱን ሕብረተሰብ ከሌላው ጤነኛ የንግዱ ሕብረተሰብ መለየት አለበት። ሁሉም ነጋዴ የኪራይ ሰብሳቢዎች መጠቀሚያም ተባባሪም ሊሆን ስለማይችል ነው። ንግድም ዓለምን የለወጠ የተከበረ ተግባር ከመሆኑ አንፃር መንግስት ከዚህ በፊትም ሲያደርገው እንደነበረው አሁንም አጋርነቱን ማሳየት ይጠበቅበታል። ስለዚህም መሰረታዊ የመንግስትን የገቢዎችና ጉምሩክ ፖሊሲን “በሽብር”፣ “በፍርሃት” ቆፈን ቀይረው ለራሳቸው ጥቅም ያደሩ የመንግስት ባለስልጣናት በፈጠሩት የተሳሳተ የኪራይ ሰብሳቢ ፍቺም በተቻለ ፍጥነት ለንግዱ ማሕበረሰብ መሰረታዊ ዕሳቤውን ማቅረብ ያስፈልጋል። በአንድ ቅርጫት ውስጥ የተቀመጠው የንግዱ ማሕበረሰብ ስምም ተገቢውን ስፍራ ሊያገኝ ይገባል። በመንግስትም በበኩሉ ኪራይ ሰብሳቢዎችን መያዙ ምርጫው ሳይሆን ግዴታው መሆኑን ግንዛቤ መውሰዱም ይጠቅማል። በተረፈ መንግስትና ጤናማው የንግዱ ማሕበረሰብ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጸች መሆናቸው የአደባባይ ሚስጥር በመሆኑ ብዙ ማለት አይቻልም። (ፎቶ: Euroradio)

(ሰንደቅ ጋዜጣ 8ኛ ዓመት ቁጥር 402 ረቡዕ ግንቦት 14/2005)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule