• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በደሴ የዳቦ ግራም የቀነሱ ሶስት ዓመት ተፈረደባቸው

January 14, 2013 07:41 am by Editor Leave a Comment

በደሴ ከተማ ግብር ከፋዩ ነጋዴና ግብር ሰብሳቢው ክፍል አልተስማሙም። የከተማዋ ሹመኞች፣ ነጋዴዎች፣ በአነስተኛና ጥቃቅን ንግድ የታቀፉና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ከንቲባውን ሲወቅሱ ተሰማ። በፓርላማ የንግድ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ርምጃ እንደሚወሰድ ጠቁሟል። በግምገማው ማብቂያ ከንቲባው ለፓርላማ አባላቱ ቢሯቸው ክፍት አድርገው እሳቸው ግን አልነበሩም። የጎልጉል ምንጮች እንደሚሉት ግምገማውን ተከትሎ የሚወሰድ ርምጃ ይኖራል። የዳቦ ግራም ቀንሰው የተገኙ ሶስት ዓመት ተፈርዶባቸዋል።

የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት አየር ላይ ያዋለው ዜና በደሴ ከተማ ግምገማና የመስክ ምልከታ የተደረገበትን ዋና ምክንያት አልጠቆመም። በዘገባው እንደተጠቆመው የንግድ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ባካሄደው የመስክ ምልከታ የከተማዋን ከንቲባ የሚያጋልጥ አቤቱታ ቀርቦላቸዋል።

ከደሴ ምክር ቤት አባል አንዱ የሆኑት ሲናገሩ “ከመቀሌ ስኳር በኮንትሮባንድ ጭነው የተያዙ አሉ፤ በነጻ ተለቀቁ” በማለት የፍርድ ሂደቱ ሚዛን የተለያየ መሆኑን አመልክተዋል። ሲያብራሩም “የዳቦ ግራም ቀንሰው በተያዙ ላይ ብቻ ሶስት ዓመት ተፈርዷል” ማለታቸውን ኢቲቪ ባልተለመደ ሁኔታ ይፋ አድርጓል።

ከኮንትሮባንድ ጋር በተያያዘ የህወሃት የቀድሞ ታጋዮችና ለመከላከያ ቅርበት ያላቸው የትግራይ ሰዎች በስፋት የሚሳተፉበት የህገወጥ የንግድ ስራ መሆኑ በስፋት አቤቱታ የሚቀርብበት ችግር ነው። ግብር እና ቀረጥ የሚከፍሉ ነጋዴዎች በኮንትሮባንድ ከሚያስገቡ ህገወጦች ጋር መወዳደር ያልቻሉበት ደረጃ ላይ መድረሳቸውን ጠቅሰው ለሟቹ ጠ/ሚኒስትር በገሃድ መናገራቸው አይዘነጋም።

እስከመተማ እህል በትራክተር በማጓጓዝ በሱዳን በኩል ወደ ኤርትራ ጤፍና የቅባት አህል በኮንትሮባንድ የሚያስተላልፉት “ሻዕቢያ ጠላታችን ነው፤ ሻዕቢያ ህገወጥ ንግድ እያካሄደብን ነው” በማለት ጥይት እስከመተኮስ የደረሱት የህወሃት ሰዎች እንደነበሩም በተደጋጋሚ የተገለጸ ጉዳይ ነው።

ኢቲቪ ቀንጭቦ ያሰማን የደሴ አስተዳደሮች  ያቀረቡት የፍርድ ሂደት  መዛባት ጥያቄ ተከትሎ አስተያየት የሰጡ እንዳሉት “ህግና የህግ የበላይነት ለአንድ አገር ህዝብ መሰረታዊ ዋስትና ነው። ሁሉም ብሔሮች እኩል ናቸው በማለት የሚወተውተው ኢህአዴግ በተቀመጠበት የፍትህ ወንበር ላይ በብሄር እየተለየ እንደሚፈረድ በተደጋጋሚ ይሰማል።እንዲህ ያለው አካሄድ በየትኛውም የህብረተሰብ ክፍል መፈጸሙ ከህጋዊው አሰራር ይልቅ ህገወጡ አካሄድ እየጠነከረ መሄዱን የሚያሳይ መስታዋት ነው”፡፡

ከንግድ ጋር በተያያዘ አለመተማመን መፈጠሩን አስመልክቶ በተደረገ ውይይት የደሴ ንግድ ዘርፍ ፕሬዚዳንት አቶ አረፋይኔ በላይ “በደሴ ከተማ  የነጋዴውን ህብረተሰብ የሚያስተዳደር ስራ አስፈጻሚ የለም። ስለ አዲስ ሪፎርም በተባራሪ ከምንሰማው በስተቀር የተማርነው ነገር የለም ” ሲሉ ተደምጠዋል።

በደሴ ለግብር ክፍያ ተመን መነሻ ከሚሆነው የነጋዴዎች የዕለት ገቢ መዝገብ ዘጠና አምስት ከመቶ ተቀባይነት ሳያገኝ ውድቅ ተደርጓል። ነጋዴዎች የተጭበረበረ የሂሳብ መዝገብ ስለማቅረባቸው ዜናው በዝርዝር ባያስረዳም የቋሚ ኮሚቴው መሪ “ዘጠና አምስት ከመቶ የዕለት ገቢ መዝገብ ውድቅ ሆነ ማለት ምን ማለት ነው? መተማመን አልተቻለም” በማለት የችግሩን ግዝፈት ሲናገሩ በምስል አስደግፎ ኢቲቪ አቅርቧል።

ሶስት ዓይነት የሂሳብ መዝገብ እንዳለ የጠቆሙት የኮሚቴው መሪ፣ ትክክለኛ መዝገብ፣ ኪሳራንና ትርፍን የሚያመዛዝኑበት መዝገብ፣ ግብር ለመክፈል ከጥገኛ የሂሳብ ባለሙያ ጋር በመመሳጠር ባላንሱን ዜሮ አድርጎ የሚያቀርቡት መኖራቸውን አመልክተዋል። በስተመጨረሻም የማስተካከያ ስራ እንደሚሰራ አመልክተዋል።

በደሴ ከተማ የተካሄደው የመስክ ምልከታ ላይ ተደራጅተው በንግድ ስራ የተሰማሩ “የመዋቅር” ሰዎች ከንቲባውን ኮንነዋል። በቀረቡት አቤቱታዎችና ችግሮች ዙሪያ ለመነጋገር የከንቲባው ቢሮ የሄዱት የፓርላማ የንግድ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት ያገኙት ባዶ ቢሮ ነበር። ከንቲባው ለምን ቢሯቸው መገኘትና መወያየት እንዳልፈለጉ የተገለጸ ነገር ባይኖርም፣ ከንቲባ ጀማል ካሳውና እሳቸው የሚመሩት ካቢኔ ከመኮርኮም እንደማያመልጡ ተገምቷል። የኢህአዴግ ባህልና አሰራር እንደሚያመለክተው መኮርኮም ሲፈልግ አስቀድሞ የሚዲያ ሥራ ይሰራል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሤራ አክሻፊው ጎንደር ለሦስተኛ ጊዜ ታሪክ ሠራ May 10, 2023 09:25 am
  • ማር በከፍተኛ ደረጃ የኮንትሮባንድ ሰለባ ሆኗል May 9, 2023 09:24 am
  • ኦነግ በኦሮሚያ ሪፈረንደም እንዲካሄድ መጠየቁ ለሰላም ንግግሩ ዕንቅፋት ሆነ May 4, 2023 01:12 am
  • መረጃ ቲቪ ያጋራው አሳሳች መረጃ May 2, 2023 12:37 pm
  • “ከፈጣሪ በታች መከላከያ የሁላችን ዋስ ጠበቃ ነው፤ ትልቅ ይቅርታ እንጠይቃለን” April 13, 2023 10:19 am
  • በትግራይ የ”ልጆቻችን የት ናቸው?” ጥያቄ እየተሰማ ነው April 13, 2023 08:56 am
  • በትህነግ የፈረሰው የአክሱም ኤርፖርት ያስከተለው ዘርፈብዙ ኪሣራ April 13, 2023 03:21 am
  • “የከተማው ነዋሪ በመሰላቸቱ ተፈናቃዮች ከፍተኛ የምግብ ችግር” ገጥሟቸዋል April 12, 2023 09:23 am
  • ከዕድሜ ልክ እስከ 20 ዓመት ቅጣት ተበይኖባቸዋል April 11, 2023 02:58 pm
  • የኡጋንዳ የክልሎች ሚኒስትር በቆርቆሮ ሌብነት ተጠርጥረው ታሰሩ April 10, 2023 03:59 pm
  • ታከለ ከተነሳ በኋላ የመዐድን ሌቦች እየተያዙ ነው April 6, 2023 02:53 pm
  • አገር ለማተራመስ ያለመ የምሁራን፣ የሚዲያ ባለቤቶችና አክቲቪስቶች ህቡዕ ቡድን ተያዘ April 4, 2023 10:07 am
  • በ10 ዓመት ውስጥ ከ44 ቢሊየን ዶላር በላይ ሸሽቷል April 4, 2023 09:26 am
  • አየር ጨብጦ አሁን ያለውን መንግሥት ከሥልጣን ልቀቁ አይሆንም March 29, 2023 09:47 am
  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule