• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በደሴ የዳቦ ግራም የቀነሱ ሶስት ዓመት ተፈረደባቸው

January 14, 2013 07:41 am by Editor Leave a Comment

በደሴ ከተማ ግብር ከፋዩ ነጋዴና ግብር ሰብሳቢው ክፍል አልተስማሙም። የከተማዋ ሹመኞች፣ ነጋዴዎች፣ በአነስተኛና ጥቃቅን ንግድ የታቀፉና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ከንቲባውን ሲወቅሱ ተሰማ። በፓርላማ የንግድ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ርምጃ እንደሚወሰድ ጠቁሟል። በግምገማው ማብቂያ ከንቲባው ለፓርላማ አባላቱ ቢሯቸው ክፍት አድርገው እሳቸው ግን አልነበሩም። የጎልጉል ምንጮች እንደሚሉት ግምገማውን ተከትሎ የሚወሰድ ርምጃ ይኖራል። የዳቦ ግራም ቀንሰው የተገኙ ሶስት ዓመት ተፈርዶባቸዋል።

የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት አየር ላይ ያዋለው ዜና በደሴ ከተማ ግምገማና የመስክ ምልከታ የተደረገበትን ዋና ምክንያት አልጠቆመም። በዘገባው እንደተጠቆመው የንግድ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ባካሄደው የመስክ ምልከታ የከተማዋን ከንቲባ የሚያጋልጥ አቤቱታ ቀርቦላቸዋል።

ከደሴ ምክር ቤት አባል አንዱ የሆኑት ሲናገሩ “ከመቀሌ ስኳር በኮንትሮባንድ ጭነው የተያዙ አሉ፤ በነጻ ተለቀቁ” በማለት የፍርድ ሂደቱ ሚዛን የተለያየ መሆኑን አመልክተዋል። ሲያብራሩም “የዳቦ ግራም ቀንሰው በተያዙ ላይ ብቻ ሶስት ዓመት ተፈርዷል” ማለታቸውን ኢቲቪ ባልተለመደ ሁኔታ ይፋ አድርጓል።

ከኮንትሮባንድ ጋር በተያያዘ የህወሃት የቀድሞ ታጋዮችና ለመከላከያ ቅርበት ያላቸው የትግራይ ሰዎች በስፋት የሚሳተፉበት የህገወጥ የንግድ ስራ መሆኑ በስፋት አቤቱታ የሚቀርብበት ችግር ነው። ግብር እና ቀረጥ የሚከፍሉ ነጋዴዎች በኮንትሮባንድ ከሚያስገቡ ህገወጦች ጋር መወዳደር ያልቻሉበት ደረጃ ላይ መድረሳቸውን ጠቅሰው ለሟቹ ጠ/ሚኒስትር በገሃድ መናገራቸው አይዘነጋም።

እስከመተማ እህል በትራክተር በማጓጓዝ በሱዳን በኩል ወደ ኤርትራ ጤፍና የቅባት አህል በኮንትሮባንድ የሚያስተላልፉት “ሻዕቢያ ጠላታችን ነው፤ ሻዕቢያ ህገወጥ ንግድ እያካሄደብን ነው” በማለት ጥይት እስከመተኮስ የደረሱት የህወሃት ሰዎች እንደነበሩም በተደጋጋሚ የተገለጸ ጉዳይ ነው።

ኢቲቪ ቀንጭቦ ያሰማን የደሴ አስተዳደሮች  ያቀረቡት የፍርድ ሂደት  መዛባት ጥያቄ ተከትሎ አስተያየት የሰጡ እንዳሉት “ህግና የህግ የበላይነት ለአንድ አገር ህዝብ መሰረታዊ ዋስትና ነው። ሁሉም ብሔሮች እኩል ናቸው በማለት የሚወተውተው ኢህአዴግ በተቀመጠበት የፍትህ ወንበር ላይ በብሄር እየተለየ እንደሚፈረድ በተደጋጋሚ ይሰማል።እንዲህ ያለው አካሄድ በየትኛውም የህብረተሰብ ክፍል መፈጸሙ ከህጋዊው አሰራር ይልቅ ህገወጡ አካሄድ እየጠነከረ መሄዱን የሚያሳይ መስታዋት ነው”፡፡

ከንግድ ጋር በተያያዘ አለመተማመን መፈጠሩን አስመልክቶ በተደረገ ውይይት የደሴ ንግድ ዘርፍ ፕሬዚዳንት አቶ አረፋይኔ በላይ “በደሴ ከተማ  የነጋዴውን ህብረተሰብ የሚያስተዳደር ስራ አስፈጻሚ የለም። ስለ አዲስ ሪፎርም በተባራሪ ከምንሰማው በስተቀር የተማርነው ነገር የለም ” ሲሉ ተደምጠዋል።

በደሴ ለግብር ክፍያ ተመን መነሻ ከሚሆነው የነጋዴዎች የዕለት ገቢ መዝገብ ዘጠና አምስት ከመቶ ተቀባይነት ሳያገኝ ውድቅ ተደርጓል። ነጋዴዎች የተጭበረበረ የሂሳብ መዝገብ ስለማቅረባቸው ዜናው በዝርዝር ባያስረዳም የቋሚ ኮሚቴው መሪ “ዘጠና አምስት ከመቶ የዕለት ገቢ መዝገብ ውድቅ ሆነ ማለት ምን ማለት ነው? መተማመን አልተቻለም” በማለት የችግሩን ግዝፈት ሲናገሩ በምስል አስደግፎ ኢቲቪ አቅርቧል።

ሶስት ዓይነት የሂሳብ መዝገብ እንዳለ የጠቆሙት የኮሚቴው መሪ፣ ትክክለኛ መዝገብ፣ ኪሳራንና ትርፍን የሚያመዛዝኑበት መዝገብ፣ ግብር ለመክፈል ከጥገኛ የሂሳብ ባለሙያ ጋር በመመሳጠር ባላንሱን ዜሮ አድርጎ የሚያቀርቡት መኖራቸውን አመልክተዋል። በስተመጨረሻም የማስተካከያ ስራ እንደሚሰራ አመልክተዋል።

በደሴ ከተማ የተካሄደው የመስክ ምልከታ ላይ ተደራጅተው በንግድ ስራ የተሰማሩ “የመዋቅር” ሰዎች ከንቲባውን ኮንነዋል። በቀረቡት አቤቱታዎችና ችግሮች ዙሪያ ለመነጋገር የከንቲባው ቢሮ የሄዱት የፓርላማ የንግድ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት ያገኙት ባዶ ቢሮ ነበር። ከንቲባው ለምን ቢሯቸው መገኘትና መወያየት እንዳልፈለጉ የተገለጸ ነገር ባይኖርም፣ ከንቲባ ጀማል ካሳውና እሳቸው የሚመሩት ካቢኔ ከመኮርኮም እንደማያመልጡ ተገምቷል። የኢህአዴግ ባህልና አሰራር እንደሚያመለክተው መኮርኮም ሲፈልግ አስቀድሞ የሚዲያ ሥራ ይሰራል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የሲኖዶሱ ውዝግብ አካሄድና መጪው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ February 6, 2023 02:03 am
  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule