• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በደሴ የዳቦ ግራም የቀነሱ ሶስት ዓመት ተፈረደባቸው

January 14, 2013 07:41 am by Editor Leave a Comment

በደሴ ከተማ ግብር ከፋዩ ነጋዴና ግብር ሰብሳቢው ክፍል አልተስማሙም። የከተማዋ ሹመኞች፣ ነጋዴዎች፣ በአነስተኛና ጥቃቅን ንግድ የታቀፉና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ከንቲባውን ሲወቅሱ ተሰማ። በፓርላማ የንግድ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ርምጃ እንደሚወሰድ ጠቁሟል። በግምገማው ማብቂያ ከንቲባው ለፓርላማ አባላቱ ቢሯቸው ክፍት አድርገው እሳቸው ግን አልነበሩም። የጎልጉል ምንጮች እንደሚሉት ግምገማውን ተከትሎ የሚወሰድ ርምጃ ይኖራል። የዳቦ ግራም ቀንሰው የተገኙ ሶስት ዓመት ተፈርዶባቸዋል።

የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት አየር ላይ ያዋለው ዜና በደሴ ከተማ ግምገማና የመስክ ምልከታ የተደረገበትን ዋና ምክንያት አልጠቆመም። በዘገባው እንደተጠቆመው የንግድ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ባካሄደው የመስክ ምልከታ የከተማዋን ከንቲባ የሚያጋልጥ አቤቱታ ቀርቦላቸዋል።

ከደሴ ምክር ቤት አባል አንዱ የሆኑት ሲናገሩ “ከመቀሌ ስኳር በኮንትሮባንድ ጭነው የተያዙ አሉ፤ በነጻ ተለቀቁ” በማለት የፍርድ ሂደቱ ሚዛን የተለያየ መሆኑን አመልክተዋል። ሲያብራሩም “የዳቦ ግራም ቀንሰው በተያዙ ላይ ብቻ ሶስት ዓመት ተፈርዷል” ማለታቸውን ኢቲቪ ባልተለመደ ሁኔታ ይፋ አድርጓል።

ከኮንትሮባንድ ጋር በተያያዘ የህወሃት የቀድሞ ታጋዮችና ለመከላከያ ቅርበት ያላቸው የትግራይ ሰዎች በስፋት የሚሳተፉበት የህገወጥ የንግድ ስራ መሆኑ በስፋት አቤቱታ የሚቀርብበት ችግር ነው። ግብር እና ቀረጥ የሚከፍሉ ነጋዴዎች በኮንትሮባንድ ከሚያስገቡ ህገወጦች ጋር መወዳደር ያልቻሉበት ደረጃ ላይ መድረሳቸውን ጠቅሰው ለሟቹ ጠ/ሚኒስትር በገሃድ መናገራቸው አይዘነጋም።

እስከመተማ እህል በትራክተር በማጓጓዝ በሱዳን በኩል ወደ ኤርትራ ጤፍና የቅባት አህል በኮንትሮባንድ የሚያስተላልፉት “ሻዕቢያ ጠላታችን ነው፤ ሻዕቢያ ህገወጥ ንግድ እያካሄደብን ነው” በማለት ጥይት እስከመተኮስ የደረሱት የህወሃት ሰዎች እንደነበሩም በተደጋጋሚ የተገለጸ ጉዳይ ነው።

ኢቲቪ ቀንጭቦ ያሰማን የደሴ አስተዳደሮች  ያቀረቡት የፍርድ ሂደት  መዛባት ጥያቄ ተከትሎ አስተያየት የሰጡ እንዳሉት “ህግና የህግ የበላይነት ለአንድ አገር ህዝብ መሰረታዊ ዋስትና ነው። ሁሉም ብሔሮች እኩል ናቸው በማለት የሚወተውተው ኢህአዴግ በተቀመጠበት የፍትህ ወንበር ላይ በብሄር እየተለየ እንደሚፈረድ በተደጋጋሚ ይሰማል።እንዲህ ያለው አካሄድ በየትኛውም የህብረተሰብ ክፍል መፈጸሙ ከህጋዊው አሰራር ይልቅ ህገወጡ አካሄድ እየጠነከረ መሄዱን የሚያሳይ መስታዋት ነው”፡፡

ከንግድ ጋር በተያያዘ አለመተማመን መፈጠሩን አስመልክቶ በተደረገ ውይይት የደሴ ንግድ ዘርፍ ፕሬዚዳንት አቶ አረፋይኔ በላይ “በደሴ ከተማ  የነጋዴውን ህብረተሰብ የሚያስተዳደር ስራ አስፈጻሚ የለም። ስለ አዲስ ሪፎርም በተባራሪ ከምንሰማው በስተቀር የተማርነው ነገር የለም ” ሲሉ ተደምጠዋል።

በደሴ ለግብር ክፍያ ተመን መነሻ ከሚሆነው የነጋዴዎች የዕለት ገቢ መዝገብ ዘጠና አምስት ከመቶ ተቀባይነት ሳያገኝ ውድቅ ተደርጓል። ነጋዴዎች የተጭበረበረ የሂሳብ መዝገብ ስለማቅረባቸው ዜናው በዝርዝር ባያስረዳም የቋሚ ኮሚቴው መሪ “ዘጠና አምስት ከመቶ የዕለት ገቢ መዝገብ ውድቅ ሆነ ማለት ምን ማለት ነው? መተማመን አልተቻለም” በማለት የችግሩን ግዝፈት ሲናገሩ በምስል አስደግፎ ኢቲቪ አቅርቧል።

ሶስት ዓይነት የሂሳብ መዝገብ እንዳለ የጠቆሙት የኮሚቴው መሪ፣ ትክክለኛ መዝገብ፣ ኪሳራንና ትርፍን የሚያመዛዝኑበት መዝገብ፣ ግብር ለመክፈል ከጥገኛ የሂሳብ ባለሙያ ጋር በመመሳጠር ባላንሱን ዜሮ አድርጎ የሚያቀርቡት መኖራቸውን አመልክተዋል። በስተመጨረሻም የማስተካከያ ስራ እንደሚሰራ አመልክተዋል።

በደሴ ከተማ የተካሄደው የመስክ ምልከታ ላይ ተደራጅተው በንግድ ስራ የተሰማሩ “የመዋቅር” ሰዎች ከንቲባውን ኮንነዋል። በቀረቡት አቤቱታዎችና ችግሮች ዙሪያ ለመነጋገር የከንቲባው ቢሮ የሄዱት የፓርላማ የንግድ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት ያገኙት ባዶ ቢሮ ነበር። ከንቲባው ለምን ቢሯቸው መገኘትና መወያየት እንዳልፈለጉ የተገለጸ ነገር ባይኖርም፣ ከንቲባ ጀማል ካሳውና እሳቸው የሚመሩት ካቢኔ ከመኮርኮም እንደማያመልጡ ተገምቷል። የኢህአዴግ ባህልና አሰራር እንደሚያመለክተው መኮርኮም ሲፈልግ አስቀድሞ የሚዲያ ሥራ ይሰራል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule