• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በደሴ የዳቦ ግራም የቀነሱ ሶስት ዓመት ተፈረደባቸው

January 14, 2013 07:41 am by Editor Leave a Comment

በደሴ ከተማ ግብር ከፋዩ ነጋዴና ግብር ሰብሳቢው ክፍል አልተስማሙም። የከተማዋ ሹመኞች፣ ነጋዴዎች፣ በአነስተኛና ጥቃቅን ንግድ የታቀፉና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ከንቲባውን ሲወቅሱ ተሰማ። በፓርላማ የንግድ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ርምጃ እንደሚወሰድ ጠቁሟል። በግምገማው ማብቂያ ከንቲባው ለፓርላማ አባላቱ ቢሯቸው ክፍት አድርገው እሳቸው ግን አልነበሩም። የጎልጉል ምንጮች እንደሚሉት ግምገማውን ተከትሎ የሚወሰድ ርምጃ ይኖራል። የዳቦ ግራም ቀንሰው የተገኙ ሶስት ዓመት ተፈርዶባቸዋል።

የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት አየር ላይ ያዋለው ዜና በደሴ ከተማ ግምገማና የመስክ ምልከታ የተደረገበትን ዋና ምክንያት አልጠቆመም። በዘገባው እንደተጠቆመው የንግድ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ባካሄደው የመስክ ምልከታ የከተማዋን ከንቲባ የሚያጋልጥ አቤቱታ ቀርቦላቸዋል።

ከደሴ ምክር ቤት አባል አንዱ የሆኑት ሲናገሩ “ከመቀሌ ስኳር በኮንትሮባንድ ጭነው የተያዙ አሉ፤ በነጻ ተለቀቁ” በማለት የፍርድ ሂደቱ ሚዛን የተለያየ መሆኑን አመልክተዋል። ሲያብራሩም “የዳቦ ግራም ቀንሰው በተያዙ ላይ ብቻ ሶስት ዓመት ተፈርዷል” ማለታቸውን ኢቲቪ ባልተለመደ ሁኔታ ይፋ አድርጓል።

ከኮንትሮባንድ ጋር በተያያዘ የህወሃት የቀድሞ ታጋዮችና ለመከላከያ ቅርበት ያላቸው የትግራይ ሰዎች በስፋት የሚሳተፉበት የህገወጥ የንግድ ስራ መሆኑ በስፋት አቤቱታ የሚቀርብበት ችግር ነው። ግብር እና ቀረጥ የሚከፍሉ ነጋዴዎች በኮንትሮባንድ ከሚያስገቡ ህገወጦች ጋር መወዳደር ያልቻሉበት ደረጃ ላይ መድረሳቸውን ጠቅሰው ለሟቹ ጠ/ሚኒስትር በገሃድ መናገራቸው አይዘነጋም።

እስከመተማ እህል በትራክተር በማጓጓዝ በሱዳን በኩል ወደ ኤርትራ ጤፍና የቅባት አህል በኮንትሮባንድ የሚያስተላልፉት “ሻዕቢያ ጠላታችን ነው፤ ሻዕቢያ ህገወጥ ንግድ እያካሄደብን ነው” በማለት ጥይት እስከመተኮስ የደረሱት የህወሃት ሰዎች እንደነበሩም በተደጋጋሚ የተገለጸ ጉዳይ ነው።

ኢቲቪ ቀንጭቦ ያሰማን የደሴ አስተዳደሮች  ያቀረቡት የፍርድ ሂደት  መዛባት ጥያቄ ተከትሎ አስተያየት የሰጡ እንዳሉት “ህግና የህግ የበላይነት ለአንድ አገር ህዝብ መሰረታዊ ዋስትና ነው። ሁሉም ብሔሮች እኩል ናቸው በማለት የሚወተውተው ኢህአዴግ በተቀመጠበት የፍትህ ወንበር ላይ በብሄር እየተለየ እንደሚፈረድ በተደጋጋሚ ይሰማል።እንዲህ ያለው አካሄድ በየትኛውም የህብረተሰብ ክፍል መፈጸሙ ከህጋዊው አሰራር ይልቅ ህገወጡ አካሄድ እየጠነከረ መሄዱን የሚያሳይ መስታዋት ነው”፡፡

ከንግድ ጋር በተያያዘ አለመተማመን መፈጠሩን አስመልክቶ በተደረገ ውይይት የደሴ ንግድ ዘርፍ ፕሬዚዳንት አቶ አረፋይኔ በላይ “በደሴ ከተማ  የነጋዴውን ህብረተሰብ የሚያስተዳደር ስራ አስፈጻሚ የለም። ስለ አዲስ ሪፎርም በተባራሪ ከምንሰማው በስተቀር የተማርነው ነገር የለም ” ሲሉ ተደምጠዋል።

በደሴ ለግብር ክፍያ ተመን መነሻ ከሚሆነው የነጋዴዎች የዕለት ገቢ መዝገብ ዘጠና አምስት ከመቶ ተቀባይነት ሳያገኝ ውድቅ ተደርጓል። ነጋዴዎች የተጭበረበረ የሂሳብ መዝገብ ስለማቅረባቸው ዜናው በዝርዝር ባያስረዳም የቋሚ ኮሚቴው መሪ “ዘጠና አምስት ከመቶ የዕለት ገቢ መዝገብ ውድቅ ሆነ ማለት ምን ማለት ነው? መተማመን አልተቻለም” በማለት የችግሩን ግዝፈት ሲናገሩ በምስል አስደግፎ ኢቲቪ አቅርቧል።

ሶስት ዓይነት የሂሳብ መዝገብ እንዳለ የጠቆሙት የኮሚቴው መሪ፣ ትክክለኛ መዝገብ፣ ኪሳራንና ትርፍን የሚያመዛዝኑበት መዝገብ፣ ግብር ለመክፈል ከጥገኛ የሂሳብ ባለሙያ ጋር በመመሳጠር ባላንሱን ዜሮ አድርጎ የሚያቀርቡት መኖራቸውን አመልክተዋል። በስተመጨረሻም የማስተካከያ ስራ እንደሚሰራ አመልክተዋል።

በደሴ ከተማ የተካሄደው የመስክ ምልከታ ላይ ተደራጅተው በንግድ ስራ የተሰማሩ “የመዋቅር” ሰዎች ከንቲባውን ኮንነዋል። በቀረቡት አቤቱታዎችና ችግሮች ዙሪያ ለመነጋገር የከንቲባው ቢሮ የሄዱት የፓርላማ የንግድ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት ያገኙት ባዶ ቢሮ ነበር። ከንቲባው ለምን ቢሯቸው መገኘትና መወያየት እንዳልፈለጉ የተገለጸ ነገር ባይኖርም፣ ከንቲባ ጀማል ካሳውና እሳቸው የሚመሩት ካቢኔ ከመኮርኮም እንደማያመልጡ ተገምቷል። የኢህአዴግ ባህልና አሰራር እንደሚያመለክተው መኮርኮም ሲፈልግ አስቀድሞ የሚዲያ ሥራ ይሰራል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule