• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የህወሃቱ ሹም ራሳቸውን በራሳቸው ካዱ

July 2, 2016 07:48 am by Editor Leave a Comment

በአዲስ አበባ ከተማ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ሀና ማርያም፣ ፉሪ፣ ማንጎ ጨፌ ሌሎች በክፍለ ከተማው ስር ባሉ መንደሮች ከቤት መፍረስ ጋር በተያያዘ የሰው ሕይወት መጥፋቱ ይታወሳል፡፡ ሁለት ፖሊሶችና አንድ የወረዳው ሥራ አስፈጻሚ ህይወታቸው እንደጠፋ በይፋ ቢነገርም የዚያኑ ያህል ከዚህ ጋር በተያያዘ የተለያዩ መረጃዎች እየወጡ ይገኛሉ፡፡

የአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ ባቀናበረው መረጃ ላይ እንዳመለከተው “መኖሪያ ቤቶቹ ይፈርሳሉ በመባሉ ከአካባቢው ነዋሪዎች የተወሰኑት አቤቱታ እያቀረቡ ባለበት ወቅት የመንግስት አፍራሽ ግብረኃይሎች ቤቱን ለማፍረስ የመብራት ትራንስፎርመር መንቀል እንደጀመሩና በዚህ መካከል ከፍተኛ ግጭት እንደተፈጠር ነዋሪዎች ይናገራሉ”።

ከላይ በተጠቀሱት አካባቢዎች የመኖሪያ ቤቶች በዶዘር በሚፈርሱበት ወቅት ወንዶች በአካባቢው እንዳይጠጉ መከልከሉን ነዋሪዎች ይናገራሉ። ከተነሳው ግጭት ጋር በተያያዘ የአካባቢው ወንዶች እና አባወራዎች ለእስር ተዳርገው አቅመቢስ ህጻናትና ሴቶች ብቻ በግፍ እየተገደዱ ከቤታቸው እንዲወጡ ተደርገዋል፡፡ አንወጣም ያሉትም ቤታቸው ላያቸው እንዲፈርስ በሚደረግበት የመጨረሻ ወቅት ቤታቸውን እየጣሉ እንደወጡ ይናገራሉ፡፡

“የዶዘር ድምጽ እየገፋ ሲመጣ አንድ የ11ዓመት ልጄንና አንድ የ6 ዓመት ልጄን እዚያው ዝናብ ላይ ትቼ የአምስት ቀን ወንድ ልጄን ታቅፌ ሸሽቻለሁ” በማለት በእንባ እየታጠበች የተናገረችው እናት በአሁኑ ሰዓት በጓደኛዋ ቤት ተጠልላ እንደምትገኝ ከቪኦኤ ለቀረበላት ጥያቄ ስትመልስ ተናግራለች፡፡

የየቤተሰቡ አባወራ በአካባቢው እንዳይገን በማድረግ፤ አብዛኛውንም በማሰር በሐምሌ ክረምት መግቢያ ላይ የተደረገው የግፍ አሠራር ምንም እንኳን ቤቶቹ ህገወጥ ናቸው ቢባልም ቢያንስ ለምን በበጋው ወቅት አይደረግም በማለት ነዋሪዎች በምሬት ይጠይቃሉ፡፡

ስማቸው ካሡ ጎዳፋይ መሆኑን እና የወረዳ አንድ ተወካይ መሆናቸውን በትክክል ካረጋገጡ በኋላ የተደወለላቸው demolishedከቪኦኤ መሆኑ ሲነገራቸው ካሱ ጎዳፋይ እንዳልሆኑና ሲመጣ እንደሚነግሩት እርሳቸው ግን የካሡ ወንድም እንደሆኑ የተናገሩት አነጋገራቸው የሚያሳብቅባቸው የህወሃት ሹመኛ፤ ጋዜጠኛ ጽዮን ግርማ እያነጋገረቻቸው ስልኩን ጆሮዋ ላይ ዘግተውባታል፡፡

ይህንን ግፍ የተሞላበት ዘግናኝ አሠራር በተመለከተ ገጣሚ ዮሐንስ ሞላ (Yohanes Molla) ከዚህ ፎቶ ጋር በማያያዝ የሚከተለውን ጽፏል፡- “እንኳን እንዲህ የትም ውጡ ተብሎ፥ ቤት ጣሪያው ተበስቶ ሲያንጠባጥብ እንኳን ይጨንቃል። እንኳን እንዲህ የትም ተበተኑ ተብሎ፥ ካፊያ ጥሎ መጠለያ እስኪያገኙ ድረስም ይጨንቃል። እንኳን እንዲህ በየሜዳው ተወርውሮ፥ ጠና ያለ ነፋስ መጥቶ ቆርቆሮ ሲያንጋጋም ይጨንቃል። እስከመቼ ግን ሕዝብ ላይ እንዲህ ይደረጋል?!”

ድልድይ በማፍረስ “ዝነኝነቱ” የሚታወቀው ህወሃት፤ አሁን እንኳን የሥልጣን መንበር ላይ ሆኖ ማፍረሱ ተያይዞታል፡፡ በላፍቶ አካባቢ የተከሰተው ግን አፍራሽ ሁልጊዜ ሲያፈርስ ብቻ እንደማይኖርና ቀኑ ሲደርስ እርሱም እንደሚፈርስ በማስረጃ የተረጋገጠበት ነው፡፡ (የዜናው ምንጭ: ቪኦኤ)

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
Copyright © 2026 · Goolgule