• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የህወሃቱ ሹም ራሳቸውን በራሳቸው ካዱ

July 2, 2016 07:48 am by Editor Leave a Comment

በአዲስ አበባ ከተማ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ሀና ማርያም፣ ፉሪ፣ ማንጎ ጨፌ ሌሎች በክፍለ ከተማው ስር ባሉ መንደሮች ከቤት መፍረስ ጋር በተያያዘ የሰው ሕይወት መጥፋቱ ይታወሳል፡፡ ሁለት ፖሊሶችና አንድ የወረዳው ሥራ አስፈጻሚ ህይወታቸው እንደጠፋ በይፋ ቢነገርም የዚያኑ ያህል ከዚህ ጋር በተያያዘ የተለያዩ መረጃዎች እየወጡ ይገኛሉ፡፡

የአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ ባቀናበረው መረጃ ላይ እንዳመለከተው “መኖሪያ ቤቶቹ ይፈርሳሉ በመባሉ ከአካባቢው ነዋሪዎች የተወሰኑት አቤቱታ እያቀረቡ ባለበት ወቅት የመንግስት አፍራሽ ግብረኃይሎች ቤቱን ለማፍረስ የመብራት ትራንስፎርመር መንቀል እንደጀመሩና በዚህ መካከል ከፍተኛ ግጭት እንደተፈጠር ነዋሪዎች ይናገራሉ”።

ከላይ በተጠቀሱት አካባቢዎች የመኖሪያ ቤቶች በዶዘር በሚፈርሱበት ወቅት ወንዶች በአካባቢው እንዳይጠጉ መከልከሉን ነዋሪዎች ይናገራሉ። ከተነሳው ግጭት ጋር በተያያዘ የአካባቢው ወንዶች እና አባወራዎች ለእስር ተዳርገው አቅመቢስ ህጻናትና ሴቶች ብቻ በግፍ እየተገደዱ ከቤታቸው እንዲወጡ ተደርገዋል፡፡ አንወጣም ያሉትም ቤታቸው ላያቸው እንዲፈርስ በሚደረግበት የመጨረሻ ወቅት ቤታቸውን እየጣሉ እንደወጡ ይናገራሉ፡፡

“የዶዘር ድምጽ እየገፋ ሲመጣ አንድ የ11ዓመት ልጄንና አንድ የ6 ዓመት ልጄን እዚያው ዝናብ ላይ ትቼ የአምስት ቀን ወንድ ልጄን ታቅፌ ሸሽቻለሁ” በማለት በእንባ እየታጠበች የተናገረችው እናት በአሁኑ ሰዓት በጓደኛዋ ቤት ተጠልላ እንደምትገኝ ከቪኦኤ ለቀረበላት ጥያቄ ስትመልስ ተናግራለች፡፡

የየቤተሰቡ አባወራ በአካባቢው እንዳይገን በማድረግ፤ አብዛኛውንም በማሰር በሐምሌ ክረምት መግቢያ ላይ የተደረገው የግፍ አሠራር ምንም እንኳን ቤቶቹ ህገወጥ ናቸው ቢባልም ቢያንስ ለምን በበጋው ወቅት አይደረግም በማለት ነዋሪዎች በምሬት ይጠይቃሉ፡፡

ስማቸው ካሡ ጎዳፋይ መሆኑን እና የወረዳ አንድ ተወካይ መሆናቸውን በትክክል ካረጋገጡ በኋላ የተደወለላቸው demolishedከቪኦኤ መሆኑ ሲነገራቸው ካሱ ጎዳፋይ እንዳልሆኑና ሲመጣ እንደሚነግሩት እርሳቸው ግን የካሡ ወንድም እንደሆኑ የተናገሩት አነጋገራቸው የሚያሳብቅባቸው የህወሃት ሹመኛ፤ ጋዜጠኛ ጽዮን ግርማ እያነጋገረቻቸው ስልኩን ጆሮዋ ላይ ዘግተውባታል፡፡

ይህንን ግፍ የተሞላበት ዘግናኝ አሠራር በተመለከተ ገጣሚ ዮሐንስ ሞላ (Yohanes Molla) ከዚህ ፎቶ ጋር በማያያዝ የሚከተለውን ጽፏል፡- “እንኳን እንዲህ የትም ውጡ ተብሎ፥ ቤት ጣሪያው ተበስቶ ሲያንጠባጥብ እንኳን ይጨንቃል። እንኳን እንዲህ የትም ተበተኑ ተብሎ፥ ካፊያ ጥሎ መጠለያ እስኪያገኙ ድረስም ይጨንቃል። እንኳን እንዲህ በየሜዳው ተወርውሮ፥ ጠና ያለ ነፋስ መጥቶ ቆርቆሮ ሲያንጋጋም ይጨንቃል። እስከመቼ ግን ሕዝብ ላይ እንዲህ ይደረጋል?!”

ድልድይ በማፍረስ “ዝነኝነቱ” የሚታወቀው ህወሃት፤ አሁን እንኳን የሥልጣን መንበር ላይ ሆኖ ማፍረሱ ተያይዞታል፡፡ በላፍቶ አካባቢ የተከሰተው ግን አፍራሽ ሁልጊዜ ሲያፈርስ ብቻ እንደማይኖርና ቀኑ ሲደርስ እርሱም እንደሚፈርስ በማስረጃ የተረጋገጠበት ነው፡፡ (የዜናው ምንጭ: ቪኦኤ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule