• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የዳምጠው አየለ ጥሪ!!

October 15, 2012 12:01 am by Editor 2 Comments

“ሰው ናፈቀኝ፣ ልጆቼና አገሬ ታወሱኝ፣ ባህሌና ልማዴ የት ገባ….?” የሚሉት የአንድ ስደተኛ ጥያቄዎች ለመቶ አለቃ ዳምጠው አየለ ተረት ሆነውበታል። አርቲስት ዳምጠው አየለ ከሁርሶ የመኮንኖች ማሰልጠና ማዕከል የመኮንንነት ትምህርት ተከታትሏል። ለሰላሳ ሁለት ዓመታት በምድር ጦር የሙዚቀኛ ሻለቃ አገልግሏል። በተለይም በባህላዊና አገር በሚያሞካሹ ዜማዎቹ የሚወደደው ዳምጠው አገሩን፣ ሁለት ልጆቹንና ባለቤቱን ጥሎ በስደት ኖርዌይ ከገባ ሰባት ዓመታት አሳልፏል። የስልሳ ሶስት ዓመቱ ዳምጠው ያጋጠመውን ጊዚያዊ ችግር አስመልክቶ ከጎልጉል የአውሮፓ ዘጋቢ ጋር ቃለ ምልልስ አድርጓል። ዳምጠው ችግር እንዳጋጠመው ሲሰማ አስቸኳይ ድጋፍ ላደረጉ ወገኖች፣ ድርጅቶች፣ ማህበሮች፣ ላደረጋችሁት በአርአያነት የሚጠቀስ ተግባር የዝግጅት ክፍላችን በዚህ አጋጣሚ ለማመስገን ይወዳል።

“… አዎ፤ እኔም ራሴን እጠይቀዋለሁ። ጀግና ሲወድቅ አይቻለሁ። የጦር ሜዳ መከራና እሳት አይቻለሁ። ባልዋጋም በኦጋዴንና በሳህል ግንባር ኤርትራ ተገኝቼ የመከራን ወጋገን ተመልክቻለሁ። ጀግና ወድቆ ሲነሳ ማየቴ ትዝ ይለኛል። ምንም እንኳን በርካታ የክፉ ቀን መቋቋሚያ ልምድ ቢኖረኘም ካቅሜ በላይ ሆነብኝ። ችግር እንዳይፈታኝ አጥብቆ የያዘኝ የኑሮ ልምዴና ወታደርነቴ እያደር ላላ። እድሜዬ እየገፋ ሲሄድ ነው መሰል ባባሁ። በጀርባዬ ተኝቼ ኮርኒስ እያየሁ ልጆቼንና ባለቤቴን በማሰላሰል ደከመኝ። አስባለሁ፣ አወጣለሁ፣ አወርዳለሁ ለውጥ የለም። አናቴ ጋለ። ደም ግፊት ያዘኝ። ሌላውም ተከተለኝ። ታመምኩ። እኔ ተቆንጥጬ ያደኩ፣ ለባህሌና ላገሬ ልዩ ክብር ያለኝ ሰው ነኝ። የአገሬ ሽታ ይመጣብኛል። ከብቶች ሽታቸው ይናፍቀኛል… ታዲያ ይህንን ሁሉ አጥቼ እንዴት የምታውቀኝ የድሮው ዳምጠው ልሆን እችላለሁ?”

ጎልጉል፦ ስሜት የሚነካ ዜና ሰማን፤
ዳምጠው፦ በርግጥ ተገደድሁ። በሌላ በኩል ደግሞ ፈጣሪ ደግ ነው። በኖርዌይ ወገኖቼ ኮርቻለሁ። ደረሱልኝ። ደገፉኝ። አበረታቱኝ። በህይወት ዘመኔ አልረሳውም።

ጎልጉል፦ ምን ገጠመህ?
ዳምጠው፦ ስደት ጠባሳው ቀላል አይደለም። የውስጥ ስሜቴን አጣሁት። ታመምኩ። ልጆቼና ባለቤቴ ራቡኝ። ሰባት ዓመት ናፍቆት ለበለበኝ። ባዶ ቤት ታቅፌ ገፋሁት። ዓመታት በተቆጠሩ ቁጥር ቤተሰቦቼን የማይበት ተስፋዬ አለቀ። ቀደም ሲል ኦስሎ እያለሁ ወንድምና እህት የሆኑኝን የኦስሎ ወገኖች እየተቀላቀልኩ ብቸኛነትን መቋቋም ችዬ ነበር። ከሶስት ዓመት በፊት የመኖሪያ አድራሻዬን ቀየርኩ።

ጎልጉል፦ ለምን?
ዳምጠው፦ ኦስሎ እያለሁ እርዳታ በማገኝበት ስርዓት ውስጥ አልነበርኩም። በዛ መልኩ መቀጠል ስላልነበረብኝ እየተደገፍኩ ለመኖር ባቀረብኩት ጥያቄ መሰረት ወደ ዮቪክ ተዛወርኩ። ላለፉት ሶስት ዓመታት ብቻን ትልቅ ቤት ታቅፌ ገፋሁት። የሚያናግረኝ አልነበረም። ከትምህርት ቤት ስመለስ ብቻዬን ቤት ውስጥ ስቀመጥ ከቀን ወደ ቀን ብቸኛነቱ ጎዳኝ። በሽተኛ ሆንኩ። ሁኔታው እየከፋ ሲሄድ ሃኪሜ የአገሩ ሰዎች በብዛት በሚኖሩበት አካባቢ መኖር አለበት በማለት ወደ ኦስሎ ተዛወርኩ።

ጎልጉል፦ መልካም አጋጣሚ ሆነልህ ማለት ነዋ?
ዳምጠው፦ ነበር። ምን ያደርጋል መካከል ላይ ያላሰብኩት ነገር ተፈጠረ። ደነገጥኩ። ለማስተካከል ብሞክርም አልሆነም…

ጎልጉል፦ ምን ገጠመህ?
ዳምጠው፦ አዲስ የገባሁበት ኮሙና (የመኖሪያ ቦታ) ድጋፍ የሚያደርግልኝ ከሶስት ወር በኋላ መሆኑንን አረዳኝ። በየወሩ ሲደረግልኝ የነበረው ድጋፍ እንደማይቀጥል አስታወቁኝ። ስራ የለኝም። ገቢ የለኝም። አገኝ ከነበረው ገቢ ልጆቼንና ቤተሰቦቼን ስለምረዳ ተቀማጭ የለኝም። ስለዚህ ውሳኔው አስደነገጠኝ። ራሴን ከፎቅ ላይ በመወርወር ለማጥፋት ወስኜ ነበር። /ንግግሩን ገታ፤ ሲቃ ያዘው/ በመካከሉ የዘወትር የክፉ ቀን ደራሽ ሆኑት ዶ/ር ሙሉ ዓለም ደረሱ… መናገር አልችልም…

ጎልጉል፦ ዶ/ር ሙሉ ዓለም ማን ናቸው?
ዳምጠው፦ በኖርዌይ የሚኖሩ ወገን ናቸው። በድንገት ህይወቴን ታደጉ። የወር ቤት ኪራይ ከኪሳቸው ከፈሉ። እስከመጨረሻው እንደሚረዱኝ አረጋገጡልኝ። ተረጋግቼ እርዳታ እስከማገኝ እንድኖር መከሩኝ። ኖርዌይ ወንድምና እህቶች እንደማይተውኝ፣ እንደማይጥሉኝ በተደጋጋሚ አስረዱኝ። ዶ/ር ሙሉ አለም ለስደተኞች ቀድሞ በመድረስ የሚታወቁ ውድ የወገን ፍቅር ያላቸው ሰው ናቸው። እድሜ ይሰጣቸው ዘንድ ከመመኘት ውጪ የምለው የለኝም። እርሳቸውን ለአብነት ጠቀስኩ እንጂ ኖርዌይ ያሉ ወገኖች ችግር ላይ መሆኔን ከሰሙበት ጊዜ ጀምሮ አልተለዩኝም።

ጎልጉል፦ ወታደር ነህ? ብዙ የህይወት ተሞክሮ አለህ። እንዴት በቀላሉ እጅህን ሰጠህ?
ዳምጠው፦ ውትድርና መከራን መሸከም የሚያስችል ልምድና ተሞክሮ የሚያጎናጽፍ ሙያ ነው። ሰላሳ ሁለት ዓመት በውትድርና ጦር ሰራዊት ቤት ኖሬያለሁ። እንዳልከው ለችግር እጄን መስጠት አልነበረብኝም። የኔ ግን ተደራረበ። በሰው ተከቦ መኖር የለመድኩ ሰው ነበርኩ። አርቲስት እንደመሆኔ ከሰው ተገልዬ አላውቅም። ኖርዌይ ከመጣሁ ሰባት ዓመት ሞላኝ። በተለይ ያለፉት ሶስት ዓመታት ሰው ራበኝ። ተጨዋች ነኝ። ሰው አጣሁ። ከማን ጋር ላውራ? ከማን ጋር ናፍቆቴን ልጋራ? ቤተሰቦቼ ጋር በደወልኩ ቁጥር ስልክ ዘግቼ አለቅሳለሁ። እንባዬ ይወርዳል። ከቤት እንዳልወጣ በረዶ ነው። ወጥቼስ የት እሄዳለሁ? አድሜዬ ገፋ። አሁን ስድሳ ሶስት ዓመት ሞላኝ። በሽተኛ ሆንኩ። ቤተሰቦቼን ሳላይ ባዶ ቤት ህይወቴ ቢያልፍስ? እላለሁ።

ጎልጉል፦ ቤተሰቦችህን ለማስመጣት ሞክረሃል?
ዳምጠው፦ ስልክ ስደውል ባለቤቴና ልጆቼ የሚጠይቁኝ ይህንኑ ነው። ሌሎች ቤተሰቦቻቸውን ይወስዳሉ። አንተ ምን ሆነክ ነው ይሉኛል። ሁሌ የምሰጣቸው መልስ መልሶ ያሳምመኛል። የተሰጠኝ የጥገኝነት ፈቃድ ቤተሰቦቼን ማስመጣት ያስችለኛል።

ጎልጉል፦ ከተፈቀደ ችግሩ ምንድን ነው?
ዳምጠው፦ ስራ የለህም ነው የሚሉት። በርግጥ ስራ የለኝም። አሁን ኦስሎ ወንድሞችና እህቶች ስራ እንዳገኝ እየተሯሯጡ ነው። በዚህ አጋጣሚ ለኖርዌይ ኢትዮጵያዊያን ህብረትና መደጋገፍ ያለኝን አክብሮት ለመግለጽ እፈልጋለሁ።

ጎልጉል፦ በኖርዌይ ያለው መቀራረብና መተጋገዝ በመልካም ጎኑ የሚያነሱት በርካቶች ናቸው። መልካም ፈቃዳቸው ከሆነ ዶ/ር ሙሉ ዓለምን ወይም የሚመለከታቸውን እንጋብዛለን። አንተ ግን ቤተሰቦችህን ለማስመጣት ከተከለከልክ ለምን በህግ አትጠይቅም?
ዳምጠው፦ ገንዘብ ያስፈልጋል። በዚህ አጋጣሚ በህግ አግባብ ሊረዱኝ የሚፈልጉ ካሉ ደስተኛ መሆኔን ለመግለጽ እወዳለሁ።

ጎልጉል፦ ባለሙያ ነህ። ለምን በሙያህ እየሰራህ ጠቅመህ ለመጠቀም አልሞከርክም?
ዳምጠው፦ አንዱ በሽታዬ እሱ ነው። በሃዘን፣ በናፍቆት፣ በብቸኝነት፣ በወገን ርሃብ፣ በአገር ፍቅር፣ በሚስት ርሃብ፣ በልጆች ፍቅር ችጋር፣ በብሶት፣ ራሱ ስለስደት፣ ስለ ባህል ረሃብ፣ ስለ አየር ንብረት ወዘተ ስሜቶቼ በተፈራረቁ ቁጥር በእውነተኛ ስሜት ውስጥ ሆኜ ያዘጋጀኋቸው ስራዎች አሉኝ። በርካታ ስራዎች አሉኝ። ብቻዬን ኦና ቤት ውስጥ ሆኜ ያዜምኳቸው እውነተኛ ስሜቶቼ አሉ። ግን ከማን ጋር ልስራቸው? ኖርዌይ የተሟላ ሁኔታ የለም። ስለዚህ ልምዴንና ስራዎቼን ለወገኖቼ ሳላካፍል ማለፌን ሳስበው እታመማለሁ። ህመሜ ከቀን ወደቀን እየጨመረ በሽተኛ አደረገኝ። ከቤተሰብ ረሃብ ጋር ተዳምሮ ውስጤን አሳሳው። እናም መልስ የሌለው ጥያቄ ነው። በአሁኑ ደረጃ እኔ ሰባራ ነኝ።

ጎልጉል፦ ከዚህ ቀደም በሙያህ እንድትሰራ የሚረዱህ ማግኘትህን ተናግረህ ነበር …
ዳምጠው፦ ተናግሬ ነበር። በተደጋጋሚ ቃል የገቡልኝ ነበሩ። አሜሪካና ካናዳ ሄጄ መሰራት እንድችል ስፖንሰር እናደርግሃለን ያሉ ወገኖች ነበሩ። እስካሁን በተግባር የሆነ ነገር የለም። አይመችም ጊዜው አስቸጋሪ ነው። ወደፊት የምናየው ይሆናል። እድሜ ካለ ማለቴ ነው። ሞት ቀጠሮ የለውም። (ሳቀ… ) በሙያዬ እንድሰራ ለሚረዱኝ ሁሉ አድራሻዬን አንተ ዘንድም እንደሚገኝ እገልጻለሁ። የረሱኝም ካስታወሱኝ አለሁ።

ጎልጉል፦ ፈሪ ሆነሃል?
ዳምጠው፦ ያልተነካ ግልግል ያውቃል እንደሚባለው ወግ ሆነብኝ። አስበው ማታ ማታ ኦና ቤት ተቀምጬ የልጆቼ ድምጽ ይሰማኝል። ባለቤቴ የምትጠራኝ ይመስለኛል። በእንዲህ ዓይነት ሁኔታ ሰባት ዓመት ቀላል አይደለም። በተለይ ያለፉትን ሶስት ዓመታት ያሳለፍኩት እንደ መንፈስ ብቻዬን እያወራሁ ነው። መኝታ ቤት አላውቅም። አልጋ አላውቅም።

ጎልጉል፦ የት ትተኛለህ?
ዳምጠው፦ መኝታ ቤት ተኝቼ አላውቅም። ቲቪ እያየሁ ሲደክመኝ እዛው አርፋለሁ። ምን አለኝና መኝታ ቤት አርፋለሁ? መኝታ ቤት የምገባው ልብስ ለመቀየር ነው።

ጎልጉል፦ በሙያህ አሁን ብቁ ነኝ ትላለህ?
ዳምጠው፦ እንግዲህ በቅርቡ ስዊድንና ጣሊያን በተካሄደ የኢሳት ገንዘብ ማሰባሰቢያ ዝግጅት ላይ የናፈቀኝን መድረክ አግኝቻለሁ። የተዋጣለት ስራ መስራቴን መስክረውልኛል። እኔ በመሳሪያ በተሞረደ ድምጽ አልሰራም። ድምጼም ሙያዬም የተፈጥሮ ነው። በየትኛውም ወቅት ስራ ከተባልኩ ዝግጁ ነኝ።

ጎልጉል፦ በዛው ለምን አልቀጠልክም?
ዳምጠው፦ ዝግጅት ሲኖራቸው ይጠሩኛል። እኔም አገራዊ ሃላፊነቴን እወጣለሁ። ስለ አገርና ባህል ሳንጎራጉር ደስ ይለኛል። ለኔ ስለ አገር ከመዝፈን በላይ የሚያስደስተኝ ነገር የለም። አገሬን ተነጥቄያለሁ። እያንጎራጎርኩ ተራራውን፣ አየሩን ፣ ባህሉን፣ ወጉን፣ ሠንደቅ ዓላማውን፣ ህዝቡን ሳናግር እኮራለሁ። ከገንዘብ በላይ አርቲስት ሃብቱ ህዝብ ነው። ራሳችንን ካላረከስን ህዝብ አይጥለንም። ኖርዌይ ያገኘሁት ይህንኑ ክብር ነው።

ጎልጉል፦ የሙያ ባልደረቦችህን ታገኛለህ?
ዳምጠው፦ አረጋኸኝ ወራሽ ይደውልልኛል። ሻምበልም ደውሎልኝ ያውቃል። በተረፈ አገር ቤት ካሉት ጋር ተገናኝተን አናውቅም።

ጎልጉል፦ አብሮ ስለመስራት አልተነጋገራችሁም?
ዳምጠው፦ ላይመቻቸው ይችላል። ታማኝ በየነን ላገኘው ሞክሬ አልቻልኩም። በርካታ የአገር ጉዳዮችን ስለሚያንቀሳቅስ አይመቸውም። ወደፊት ላገኘው እሞክራለሁ።

ጎልጉል፦ የሰርግ ዘፈን ትችላለህ?
ዳምጠው፦ ልታገባ ነው? ወይስ ስራ አገኘህልኝ? በሚገባ እሰራለሁ።

ጎልጉል፦ ቢያንስ በባህላዊ መሳሪያ ባለህበት አገር ሰርግ ለምን አትሰራም?
ዳምጠው፦ እኔ መሳሪያ መጫወት አልችልም። የሚያመቻች ከተገኘ እኔ በድምጼ ድፍን ስካንዲቪያንን እያካለልን መስራት እንችላለን። ለሰርግ ዘፈንና ለስክስታውማ ባለቤቱ ነበርኩ፡፡

ጎልጉል፦ ጥሬ ስጋ ካልበላህ አትጫወትም ይባላል?
ዳምጠው፦ ስጋ ትወዳለህ ለማለት ፈልገህ ከሆነ አዎ ጥሬ ስጋ እወዳለሁ። የስጋ ዘርፉንም ጠንቅቄ አውቃለሁ። ብልቷን ባይነት ባይነት አጥርቼ አውቃለሁ። የዛሬን አያድርገውና ጾም ካልሆነ ያለ ስጋ አልበላም ነበር። ስጋ መቆረጥ ስለማውቅ ትልልቅ ሰዎች ስጋ አብሬያቸው እንድበላ ይጎትቱኝ ነበር። የምን ስጋ አነሳህብኝ?

ጎልጉል፦ ለትዝታ ነው? ከቤተሰብህ ባንተ የወጣ አለ?
ዳምጠው፦ ልጄ እንደኔ ነው አሉ። አስራ ሁለት ዓመት ሲሆነው ጥዬው ወጣሁ አሁን አስራ ዘጠኝ ዓመቱ ነው።

ጎልጉል፦ ስታገኘው ምን ትለዋለህ?
ዳምጠው፦ ምክሬ አንድ ነው። እኔ ባለመማሬ ተጎድቻለሁ። ቋንቋ ይቸግራል። አስተርጓሚ ሰው እያስቸገርኩ ነው። ተማር አለበለዚያ ዋጋ የለህም እለዋለሁ። በደወልኩ ቁጥር ስለ ድንቁርና ሳልነግረው አላልፍም። ገፍቼ አለመማሬ ያንገበግበኛል። ፈጣሪ የልቤን ተረድቶ በልጆቼ ሊክሰኝ ያሰበ ይመስለኛል። ጥሩ ደረጃ ላይ ነው። የደረጃ ተማሪ ነው።

ጎልጉል፦ የማውቅህ ዳምጠው አልመሰልከኘም?
ዳምጠው፦ አዎ፤ እኔም ራሴን እጠይቀዋለሁ። ጀግና ሲወድቅ አይቻለሁ። የጦር ሜዳ መከራና እሳት አይቻለሁ። ባልዋጋም በኦጋዴንና በሳህል ግንባር ኤርትራ ተገኝቼ የመከራን ወጋገን ተመልክቻለሁ። ጀግና ወድቆ ሲነሳ ማየቴ ትዝ ይለኛል። ምንም እንኳን በርካታ የክፉ ቀን መቋቋሚያ ልምድ ቢኖረኘም ካቅሜ በላይ ሆነብኝ። ችግር እንዳይፈታኝ አጥብቆ የያዘኝ የኑሮ ልምዴና ወታደርነቴ እያደር ላላ። እድሜዬ እየገፋ ሲሄድ ነው መሰል ባባሁ። በጀርባዬ ተኝቼ ኮርኒስ እያየሁ ልጆቼንና ባለቤቶቼን በማሰላሰል ደከመኝ። አስባለሁ፣ አወጣለሁ፣ አወርዳለሁ ለውጥ የለም። አናቴ ጋለ። ደም ግፊት ያዘኝ። ሌላውም ተከተለኝ። ታመምኩ። እኔ ተቆንጥጬ ያደኩ፣ ለባህሌና ላገሬ ልዩ ክብር ያለኝ ሰው ነኝ። የአገሬ ሽታ ይመጣብኛል። ከብቶች ሽታቸው ይናፍቀኛል… ታዲያ ይህንን ሁሉ አጥቼ እንዴት የምታውቀኝ የድሮው ዳምጠው ልሆን እችላለሁ?

ጎልጉል፦ ምግብ መስራት ትችላለህ?
ዳምጠው፦ (ሳቅ) ልታሰለጥነኝ ነው? ወይስ …

ጎልጉል፦ በተደጋጋሚ “የጋን ውስጥ መብራት ሆኛለሁ” ስትል ትደመጣለህ፤
ዳምጠው፦ የገለጽኩት መሰለኝ። አንድ የኪነት ባለሙያ ለሁሉም ነገር ስሜቱ ቅርብ ነው። በተፈራረቁብኝ ስሜቶች ውስጥ ሆኜ ያዘጋጀኋቸው በርካታ ስራዎች አሉ። ስለ አገር፣ ስለ ስደት፣ ስለ ሰው ርሃብ፣ ስለ ልጆች ናፍቆት፣ ስለ ትዳር ጓደኛ ፍቅር ርሃብ፣ ስለ ብቸኛነት፣ ስለ ቅዠት፣ ስለ ሃሳብ ጎርፍ በራሴ ስሜት ውስጥ ያለፉ እውነታዎችን ሰብሳቤያለሁ። በሙያዬም ቢሆን በቂ ምስክር ያለኝ ነኝ። ይህንን ሁሉ ነገር ይዤ ማለፍ አልፈልግም። ለሌሎች ማስተላለፍ አለብኝ። በተለይ ለአገሬና ለመጪው ትውልድ የሚሆን ስራ መስራት እፈልጋለሁ። ለዚህ ነው የጋን ውስጥ መብራት ሆኛለሁ የምለው። የተሸከምኩትን ስለማውቅ ነው። ውለታቸውን ዘርዝሬ በማልጨርሰው በኖርዌይ ወገኖቼ ስም አንድ ነገር ባደርግ ደስ ይለኛል።

ጎልጉል፦ የቀድሞ ሰራዊት ሲባል ትቆጣለህ። ለምን?
ዳምጠው፦ እኔ እስከማውቀው የኢትዮጵያ አለኝታ ነበር፣ ግዳጁን በአግባቡ ሲወጣ የነበረ። ወደፊት ታሪክና ጊዜ ይፋ የሚያወጣው ግፍ የተፈጸመበት ታማኝ ሰራዊት ነበር። ጨዋና በሙያው የተከበረ ሰራዊት ነበር። ብቃቱንና አገር ወዳድነቱን በግፍ እንዲበተን ከተደረገ በኋላም አሳይቷል። ይህ ሰራዊት ምንጊዜም የሚረሳ አይደለም። የቀድሞ፣ የደርግ ወዘተ ብለው ሲጠሩት ደስ አይለኝም። አግባብም አይደለም። በዚህ ብናበቃስ?

ጎልጉል፦ አሁን ስላለህበት ሁኔታ ንገረኝና እንሰነባበት?
ዳምጠው፦ አሜሪካና ካናዳ፣ በተለይም አሜሪካ ያሉት ኢትዮጵያዊያን ወገኖች ቁጥራቸውና ከፍተኛ ስለሆነ፣ ይህንኑ በመረዳት ቃል የገቡልኝ ችግሬን ተመልክተው ስሞት ከሚያለቅሱ ከወዲሁ የሚችሉትን ቢያደርጉልኝ፣ ስፖንሰር አፈላልገው ቢወስዱኝ ስል እማጸናለሁ። አሁን ያለሁት በኖርዌይ ወንድሞችና እህቶች እጅ ነው። ስደተኞቹ ወገኖቼ እየረዱኝ ነው። ስራ ፍለጋ እደከሙልኝ ነው። ሙሉ በሙሉ ህይወቴን እየመሩልኝ ነው። ለሶስትና አራት ወር ሌላ አማራጭ የለም። በዚህ አጋጣሚ በኖርዌይ ያሉትን ወገኖች ዘርዝሬ አልችልም ምስጋናዬ ይድረሳችሁ። ልዑል እግዚአብሄር ውለታችሁን ይክፈለው። ክፉ ምኞት በተመኘሁበት ሰዓት የደረስክልኝ ዶ/ር ሙሉ አለም ከልቤ ላመሰግንህ እወዳለሁ። ያንተን ልዩ የሚያደርገው ምናልባትም ይህንን ምስጋና የማቅረብ እድል ሳላገኝ ከክፉ ምኞቴ ጋር ቀርቼ ቢሆንስ በሚል በየዋህነት ሳስበው መኖሬ ስለሚደንቀኝ ነው። ቀና አሳቢነት ለራስ ቢሆንም ሳላመሰግን ማለፍ ባለመቻሌ ስምህን ጠቅሻለሁ። ለኖርዌይ ወገኖች ሁሉ ከልብ አመሰግናለሁ። አሳልፋችሁናልና ምስጋናዬ ታላቅ ነው።

(ለንባብ ያመች ዘንድ ከአርቲስት ዳምጠው ጋር ያደረግነውን ቃለ ምልልስ እንደ አስፈላጊነቱ ቅደም ተከተሉን ማቀያየራችንን እንገልጻለን። አርቲስት ዳምጠው አየለ ቃለ ምልልስ ለማድረግ ስላደረገልን ትብብር ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ምስጋናችንን እናቀርባለን።)

ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ ለሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Interviews

Reader Interactions

Comments

  1. Engeda says

    October 13, 2012 11:00 pm at 11:00 pm

    “Reincarnation and the Purpose of Our Lives, it is only when we can connect with the bigger picture that we can understand that even the most difficult and painful things we all go through our in lives are there for our highest good and to help us attain another level in our spiritual growth.”

    Reply
  2. Fasil says

    October 17, 2012 12:04 pm at 12:04 pm

    Why didn’t he come back to his country, if the situation is as he said. Does he have some problem with the regime. his families, friends and others who know him should ask the concerned authorities for an appology so that he can easily return to his country and live with his beloved family. he is an ordinary citizen (he is not a member of ONLF, Ginbot 7 or anything similar). Unless, he commited some type of crime, I don’t think its very difficult for him to return.

    God be with Damtew

    Reply

Leave a Reply to Fasil Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በሆሩ ጉዱሩ ወለጋ ዞን የጉደኔ ጫላ ሲበሬ ቀበሌ ነዋሪዎች በኦነግ ሸኔ ላይ ጀብዱ ፈፀሙ August 11, 2022 03:04 pm
  • በኢትዮጵያ ግብርና ላይ ግብጽ ለዓመታት የፈጸመችው ሤራ August 10, 2022 10:58 am
  • የስሪ ላንካው “FamilyCracy” – ከመዓቱ እስከ ተውኔቱ August 8, 2022 09:45 am
  • “አበበ እንጂ መቼ ሞተ!”          July 19, 2022 04:57 pm
  • ሸኔ አመራሮቹንና ጠንካራ ይዞታዎቹን እያጣ ነው July 19, 2022 01:55 am
  • የወልቃይት አማራ የተሰቃየባቸው የትህነግ 15 ድብቅ እስር ቤቶች! July 18, 2022 03:13 pm
  • ገቢ የማያስገኙ የዜና ርዕሶች July 17, 2022 05:36 pm
  • “ዛሬ ‘ኃያል ነን’ የሚሉ ሀገራት ኢትዮጵያ ላይ በሚዲያ /በመረጃ/፣ በዲፕሎማሲ፣ በሳይበር እና በተልእኮ የተቀነባበረ ‘ግራጫ ጦርነት’ እያካሄዱባት ነው” ጠ/ሚ ዐቢይ July 7, 2022 10:03 am
  • የኦሮሞ ልሂቃንና ፖለቲከኞች በአማራ ተወላጆች ላይ እየደረሰ ያለውን “የዘር ማጥፋት” ወንጀል እንዲያወግዙት አብን ጠየቀ July 6, 2022 01:38 pm
  • “አማራን ኦሮሚያ ውስጥ የመግደል እና የመጨፍጨፍ እቅድ የኦነግ ሳይሆን የኦሮሚያ ብልጽግና ነው” አቶ ሃንጋሳ July 6, 2022 01:53 am
  • “በኢትዮጵያዊያን የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ በመግባት ሀገሪቱን ማተራመስ አለብን” አይማን አብድልአዚዝ ግብጻዊው ፖለቲከኛ July 5, 2022 12:57 pm
  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule