• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሙስሊም ወንድማማች ዕገዳ ተጣለበት

September 24, 2013 10:29 am by Editor Leave a Comment

የካይሮው አስቸኳይ ጉዳዮች ፍርድቤት የሙስሊም ወንድማማችን እና ከእርሱ ጋር ግንኙነት ያላቸውን መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን በሙሉ ከማንኛውም እንቅስቃሴ አገደ፡፡ የመካከለኛው ምስራቅ የዜና አገልግሎትን ጠቅሶ አልጃዚራ እንደገለጸው ዕገዳው መሐመድ ሙርሲ ይመሩት የነበረውን እና ከሙስሊም ወንድማማች ጋር የጠበቀ ግንኙነት ያለውን የእስላማዊው እንቅስቃሴ የፖለቲካ ክንፍ የነጻነትና ፍትሕ ፓርቲንም ሊጨምር ይችላል፡፡

በሕዝብ ድምጽ ሥልጣን የተረከቡትን መሐመድ ሙርሲ በመፈንቅለ መንግሥት ከሥልጣን ከተወገዱ በኋላ የሙስሊም ወንድማማች ደጋፊዎችና ከፍተኛ አመራሮች አሁንም እየታሰሩና እየተገደሉ ይገኛል፡፡

ከፖሊስና፣ ከደኅንነትና ከመፈንቅለ መንግሥቱ ደጋፊዎች ጋር የሚደረገው ውዝግብ ደም አፋሳሽ ከመሆን አልፎ በወንድማማቾቹ እንቅስቃሴ ላይ “የአሸባሪነት” ታርጋ አስለጥፎበታል፡፡

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ባለፈው ወር በተከሰተው ግጭት የሙስሊም ወንድማማች ደጋፊዎች ከ600 በላይ ክርስቲያኖችን መግደላቸውና ቤ/ክናትን ማቃጠላቸው እንደሚገባው አልተዘገበም በማለት አንዳንድ የሚዲያ ተቋማት ወቀሳ ሲያቀርቡ ቆይተዋል፡፡

የሰኞው ዕለት ዕገዳ በአሁኑ ጊዜ በወንድማማች ኅብረቱ ላይ የሚካሄደውን የተፋፋመ ወከባ በሕጋዊ መልኩ ያጠናክረዋል የሚል ግምት እየተሰጠበት ቢሆንም የግብጽ አገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር ግን ሁኔታው እንደዚያ እንዳልሆነ ለአልጃዚራ ዘጋቢ ተናግሯል፡፡ “በአሁኑ ጊዜ እየተካሄዱ ያሉት የተቃውሞ ሰልፎች ሰላማዊ እስከሆኑ ድረስ መቀጠል ይችላሉ፤” ሆኖም የሙርሲን መነሳት በመቃወም አስመስለው የሽብር ተግባር ለመፈጸም የሚፈልጉ ሁሉ የትም ሊያመልጡ እንደማይችሉ አስጠንቅቋል፡፡

85ዓመታትን ያስቆጠረው እስላማዊው እንቅስቃሴ በ1946 በሕግ ታግዶ የነበረ ሲሆን በቅርቡ ሕጋዊነቱን አግኝቶ ወደ ግብጽ ፖለቲካ ውስጥ ከገባ በኋላ የበርካታዎችን ድጋፍ አግኝቷል፡፡ የዚህም ውጤት በዴሞክራሲያዊ መንገድ በግብጽ በቅርቡ በተካሄደው ምርጫ የፓርላማውን አብላጫ ወንበርና የፕሬዚዳንትነቱን መንበር መቆጣጠር ችሏል፡፡

በካይሮው አስቸኳይ ጉዳዮች ፍርድቤት የተላለፈው ውሳኔ የሙስሊም ወንድማማች ማኅበርን፣ በመያድ ስም የተመዘገቡት የሙስሊም ወንድማማች ድርጅቶችን እንዲሁም “ማንኛውም ከሙስሊም ወንድማማች ጋር የተገናኘ ድርጅት ወይም ንብረት ወይም የገንዘብ ዕርዳታ የሚያገኝ ተቋም” ላይ ዕገዳው የተላለፈበት መሆኑን ይናገራል፡፡ ሆኖም በወንድማማቹ ማኅበር ሥር ያሉትን ትምህርትቤቶችና ሆስፒታሎችን ጨምሮ ሌሎች የማኅበራዊ ተቋማት ዕገዳው እንደሚመለከታቸው ግልጽ አልሆነም፡፡

ውሳኔውን አስመልክቶ የወንድማማች ማኅበሩ ከፍተኛ አመራር የሆኑት ኢብራሂም ሙኒር ዕገዳውን “አምባገነናዊ ውሳኔ” ያሉት ሲሆን በዚህም ውሳኔ እንኳን ቢሆን ማኅበሩ እንደማይጠፋ ተናግረዋል፡፡ ሲቀጥሉም “በአላህ ዕርዳታ እንጂ በአል-ሲሲ (የጦር ኃይሎች ዋና ኃላፊ የሆኑትን ጄኔራል አብዱል ፋታህ አል-ሲሲን ማለታቸው ነው) የፍርድቤት ትዕዛዝ የሚፈርስ አይደለም” ብለዋል፡፡

በብያኔው ወቅት ያስቻሉት ዳኛ፤ የማኅበሩ “ገንዘብ፣ ንብረትና ህንጻዎች እንዲወረሱ” ውሳኔ አስተላልፈዋል፡፡ በግብጽ ካቢኔ ገለልተኛ ኮሚቴ ተቋቁሞ ፍርድቤቱ የመጨረሻ ውሳኔ እስኪሰጥ ድረስ አሁን የሚወረሰውን ሃብት እንዲያስተዳድርም ተወስኗል፡፡ ውሳኔውን ይግባኝ ማለት እንደሚቻል አብሮ ተጠቁሟል፡፡

ከአባላቱ በሚገኝ መዋጮ የሚተዳደረው የሙስሊም ወንድማማች ማኅበር “አላህ ዓላማችን፤ ቁርዓን ሕጋችን፤ ነቢዩ መሪያችን፤ ጂሃድ መንገዳችን ናቸው፡፡” በሚሉ መሠረታዊ መመሪያዎች እንደሚተዳደር ይታወቃል፡፡ (ፎቶ: news.yahoo.com)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule