• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሙስሊም ወንድማማች ዕገዳ ተጣለበት

September 24, 2013 10:29 am by Editor Leave a Comment

የካይሮው አስቸኳይ ጉዳዮች ፍርድቤት የሙስሊም ወንድማማችን እና ከእርሱ ጋር ግንኙነት ያላቸውን መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን በሙሉ ከማንኛውም እንቅስቃሴ አገደ፡፡ የመካከለኛው ምስራቅ የዜና አገልግሎትን ጠቅሶ አልጃዚራ እንደገለጸው ዕገዳው መሐመድ ሙርሲ ይመሩት የነበረውን እና ከሙስሊም ወንድማማች ጋር የጠበቀ ግንኙነት ያለውን የእስላማዊው እንቅስቃሴ የፖለቲካ ክንፍ የነጻነትና ፍትሕ ፓርቲንም ሊጨምር ይችላል፡፡

በሕዝብ ድምጽ ሥልጣን የተረከቡትን መሐመድ ሙርሲ በመፈንቅለ መንግሥት ከሥልጣን ከተወገዱ በኋላ የሙስሊም ወንድማማች ደጋፊዎችና ከፍተኛ አመራሮች አሁንም እየታሰሩና እየተገደሉ ይገኛል፡፡

ከፖሊስና፣ ከደኅንነትና ከመፈንቅለ መንግሥቱ ደጋፊዎች ጋር የሚደረገው ውዝግብ ደም አፋሳሽ ከመሆን አልፎ በወንድማማቾቹ እንቅስቃሴ ላይ “የአሸባሪነት” ታርጋ አስለጥፎበታል፡፡

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ባለፈው ወር በተከሰተው ግጭት የሙስሊም ወንድማማች ደጋፊዎች ከ600 በላይ ክርስቲያኖችን መግደላቸውና ቤ/ክናትን ማቃጠላቸው እንደሚገባው አልተዘገበም በማለት አንዳንድ የሚዲያ ተቋማት ወቀሳ ሲያቀርቡ ቆይተዋል፡፡

የሰኞው ዕለት ዕገዳ በአሁኑ ጊዜ በወንድማማች ኅብረቱ ላይ የሚካሄደውን የተፋፋመ ወከባ በሕጋዊ መልኩ ያጠናክረዋል የሚል ግምት እየተሰጠበት ቢሆንም የግብጽ አገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር ግን ሁኔታው እንደዚያ እንዳልሆነ ለአልጃዚራ ዘጋቢ ተናግሯል፡፡ “በአሁኑ ጊዜ እየተካሄዱ ያሉት የተቃውሞ ሰልፎች ሰላማዊ እስከሆኑ ድረስ መቀጠል ይችላሉ፤” ሆኖም የሙርሲን መነሳት በመቃወም አስመስለው የሽብር ተግባር ለመፈጸም የሚፈልጉ ሁሉ የትም ሊያመልጡ እንደማይችሉ አስጠንቅቋል፡፡

85ዓመታትን ያስቆጠረው እስላማዊው እንቅስቃሴ በ1946 በሕግ ታግዶ የነበረ ሲሆን በቅርቡ ሕጋዊነቱን አግኝቶ ወደ ግብጽ ፖለቲካ ውስጥ ከገባ በኋላ የበርካታዎችን ድጋፍ አግኝቷል፡፡ የዚህም ውጤት በዴሞክራሲያዊ መንገድ በግብጽ በቅርቡ በተካሄደው ምርጫ የፓርላማውን አብላጫ ወንበርና የፕሬዚዳንትነቱን መንበር መቆጣጠር ችሏል፡፡

በካይሮው አስቸኳይ ጉዳዮች ፍርድቤት የተላለፈው ውሳኔ የሙስሊም ወንድማማች ማኅበርን፣ በመያድ ስም የተመዘገቡት የሙስሊም ወንድማማች ድርጅቶችን እንዲሁም “ማንኛውም ከሙስሊም ወንድማማች ጋር የተገናኘ ድርጅት ወይም ንብረት ወይም የገንዘብ ዕርዳታ የሚያገኝ ተቋም” ላይ ዕገዳው የተላለፈበት መሆኑን ይናገራል፡፡ ሆኖም በወንድማማቹ ማኅበር ሥር ያሉትን ትምህርትቤቶችና ሆስፒታሎችን ጨምሮ ሌሎች የማኅበራዊ ተቋማት ዕገዳው እንደሚመለከታቸው ግልጽ አልሆነም፡፡

ውሳኔውን አስመልክቶ የወንድማማች ማኅበሩ ከፍተኛ አመራር የሆኑት ኢብራሂም ሙኒር ዕገዳውን “አምባገነናዊ ውሳኔ” ያሉት ሲሆን በዚህም ውሳኔ እንኳን ቢሆን ማኅበሩ እንደማይጠፋ ተናግረዋል፡፡ ሲቀጥሉም “በአላህ ዕርዳታ እንጂ በአል-ሲሲ (የጦር ኃይሎች ዋና ኃላፊ የሆኑትን ጄኔራል አብዱል ፋታህ አል-ሲሲን ማለታቸው ነው) የፍርድቤት ትዕዛዝ የሚፈርስ አይደለም” ብለዋል፡፡

በብያኔው ወቅት ያስቻሉት ዳኛ፤ የማኅበሩ “ገንዘብ፣ ንብረትና ህንጻዎች እንዲወረሱ” ውሳኔ አስተላልፈዋል፡፡ በግብጽ ካቢኔ ገለልተኛ ኮሚቴ ተቋቁሞ ፍርድቤቱ የመጨረሻ ውሳኔ እስኪሰጥ ድረስ አሁን የሚወረሰውን ሃብት እንዲያስተዳድርም ተወስኗል፡፡ ውሳኔውን ይግባኝ ማለት እንደሚቻል አብሮ ተጠቁሟል፡፡

ከአባላቱ በሚገኝ መዋጮ የሚተዳደረው የሙስሊም ወንድማማች ማኅበር “አላህ ዓላማችን፤ ቁርዓን ሕጋችን፤ ነቢዩ መሪያችን፤ ጂሃድ መንገዳችን ናቸው፡፡” በሚሉ መሠረታዊ መመሪያዎች እንደሚተዳደር ይታወቃል፡፡ (ፎቶ: news.yahoo.com)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule