• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

መሬት ነጠቃ ለአሜሪካ ም/ቤት ሊቀርብ ነው

April 8, 2013 09:08 am by Editor 4 Comments

በመጪው ሰኞ ሚያዚያ7፤2005ዓም (April 15፣ 2013) በአፍሪካ ስለሚደረገው የመሬት ነጠቃ አስመልክቶ የአሜሪካ ም/ቤት የፖሊሲ አውጪዎችና በጉዳዩ ላይ የሚሟገቱ የሰብዓዊ መብት ተከራካሪዎችን እንዲሁም ባለሙያዎችን ሃሳብ ለማዳመጥ ስብሰባ መጥራቱ ታወቀ፡፡

በአሜሪካ የተወካዮች ምክርቤት በአፍሪካ፣ በዓለምአቀፍ ጤና፣ በዓለምአቀፍ የሰብዓዊ መብቶችና ዓለምአቀፋዊ ድርጅቶች ንዑስኮሚቴ ሊቀመንበር የሆኑት ክሪስ ስሚዝ ከፍተኛ አማካሪና የአፍሪካ ኤክስፐርት የሆኑት ግሬጎሪ ሲምፐኪንስ ስብሰባውን እንደሚመሩትም ከወጣው መረጃ ለመረዳት ተችሏል፡፡

በአፍሪካ የሚካሄደውን የመሬት ነጠቃ አስመልክቶ በተጠራው ስብሰባ ላይ መግለጫ ከሚሰጡት አፍሪካውያን መካከል ጋናዊው ምሁር ዶ/ር ጆርጅ አዪቴ የሚገኙበት ሲሆን ከኢትዮጵያ ብቸኛው ተጠቃሽ የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶ ናቸው፡፡ ከኦክላንድ ተቋም ጋር በመሆን አቶ ኦባንግ የሚመሩት የጋራ ንቅናቄ በቅርቡ በአማርኛ ተተርጉሞ ይፋ የሚሆነውን ጥናታዊ ዘገባ ማዘጋጀቱ ይታወቃል፡፡ ይህንኑ በመሬት ነጠቃ ላይ የተዘጋጀውን ዘገባ የጠቀሰው የስብሰባው መጥሪያ በጉዳዩ ላይ አኢጋን ያከናወነውን የምርመራ ሪፖርት ጠቅሷል፡፡

በአሁኑ ጊዜ በተለያዩ የሥራ ጉዳዮች ላይ በመጠመድ በዋሺንግተን ዲሲ ከተማ የሚገኙትን አቶ ኦባንግን ጎልጉል በስልክ ባነጋገረበት ወቅት እንደተናገሩት ድርጅታቸው መነሻውንና መድረሻውን እንዲሁም የሚያከናውነውን ተግባራት በዕቅድ የሚፈጽም መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ የጋራ ንቅናቄው ለዚህ ዕውቅናና ስብሰባ መጠራቱ በራሱ ታላቅ ድል መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ የሰላማዊ ትግል ከወረቀት የማያልፍና የአቤቱታ ማስፈረም (የፔቲሽን) ትግል ብቻ እንዳልሆነ በቅርቡ ሕንድ በመሄድ በዚሁ የመሬት ነጠቃ ጉዳይ ላይ ያደረጉት ስብሰባና ውይይት በኢንቨስትመንት ስም በኢትዮጵያ መሬት እየዘረፉ ላሉት ኩባንያዎች ከፍተኛ ችግር እንደፈጠረባቸው እንደማስረጃ ጠቅሰዋል፡፡

ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ካለበት ድርጅታዊና አገራዊ ግዴታ አኳያ የአሜሪካ ምክርቤት ሕግ አውጪ አካላትን በኢትዮጵያ ስላለው ሁኔታ እያሳወቀና እየወተወተ መሆኑን የተናገሩት አቶ ኦባንግ፤ በተለይ በቅርቡ የሚካሄደውን ምርጫ፣ የፖለቲካ እስረኞችን ሁኔታ፣ ከየቦታው እየተፈናቀሉ ያሉትን ዜጎች፣ አፋኝ የሆኑትን የመያድና የጸረ-ሽብርተኝነት ሕጎችን እንዲሁም የመንደር ምስረታንና አስገድዶ ማስፈርን በተመለከተ በርካታ ጉዳዮች በተጠናከረ ሁኔታ እየሠራበት እንደሆነ በተለይ ለጎልጉል ገልጸዋል፡፡ በመጪው ሰኞ በሚደረገው ስብሰባ የሚገኘውን ውጤት ካሁኑ በግልጽ ለመናገር ባይቻልም ስብሰባው ከላይ ከተጠቀሱት ጉዳዮች አንዱ እንደመሆኑ ወደፊት በምክርቤት ለሚደረጉ ውሳኔዎች እንደ ግብዓት እንደሚያገለግል አስታውቀዋል፡፡  

በአፍሪካ እየተካሄደ ስላለው የመሬት ነጠቃ 11የአፍሪካ አገራትን የሚወክሉ 11 ድርጅቶች ኅብረት በመፍጠር ተጽዕኖ ከማድረግ እስከ ፖሊሲ ማስቀየር ሥራ እየሠሩ መሆናቸውና ከእነዚህም ድርጅቶች መካከል ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ አንዱ መሆኑ ይታወቃል፡፡

የሰኞው ስብሰባ መርሃግብር ይህንን ይመስላል፡፡

THE LAND-GRAB ISSUE IN AFRICA

A Discussion with Advocates & Policymakers

Monday, April 15 at 2:00PM

U.S. CONGRESS: Rayburn House Office Building

(45 Independence Avenue SW, Washington, DC)

 A SHORT DOCUMENTARY ON LAND GRABBING WILL BE SCREENED

Land grabbing is becoming the single most combative issue in Africa. It involves large-scale land acquisitions by foreign countries and corporations for farming, biofuels, logging and minerals. Unlike land acquisitions in the United States and Europe where purchasers pay the fair market values for land, in Africa unscrupulous deals are displacing thousands of farmers and leaving local communities in abject poverty, while government officials benefit from land sales and leases.

PANALISTS

 BINTA TERRIER

Ms. Terrier is Co-Founder and Executive Director of Partnership League for Africa’s Development (PLAD). PLAD was created to focus on education, health, land-rights and agriculture as the cornerstone to address the human rights problem in Africa. Educated as an economist she is becoming a leading female voice for Africa’s development and governance.

DR. GEORGE AYITTEY

Dr. Ayittey is a distinguished Economist and Professor at the American University, Washington, DC. He is the founder and chair of the Free Africa Foundation and an associate scholar at the Foreign Policy Research Institute. Dr. Ayittey has championed the argument that: Africa is poor because she is not free, that the primary cause of African poverty is less a result of the oppression and mismanagement by colonial powers, but rather a result of modern oppressive native autocrats.

OBANG METHO

Mr. Metho is Executive Director of the SMNE (www.solidaritymovement.org), a social justice movement of diverse Ethiopians that joint-sponsored with the think tank, Oakland Institute, to produce the Ethiopian portion of the comprehensive investigative report, Understanding Land Investment Deals in Africa, published in June 2011. Mr. Obang is a human rights activist who tirelessly advocates for human rights, justice, freedom and environment, enhanced accountability in politics and peace in Africa for over 10 years.

RICK JACOBSON

Mr. Jacobson works on land grab issues in Africa as a Team Leader for International Forest Policy and Environmental Governance for Global Witness.

MODERATOR: GREGORY SIMPKINS

Mr. Simpkins is an Africa Expert and Senior Advisor, to Congressman Chris Smith the Chairman of the U.S. House Subcommittee on Africa, Global Health, Global Human Rights and International Organizations.

Questions: please contact: Binta@allafr.org 301-802-2233 or kwame@rebeccaproject.org 202-406-0911


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Teshale says

    April 10, 2013 11:33 pm at 11:33 pm

    Obang, God bless you. You have such a skill to find your way into important international fora where our concern can receive international attention. I wish we had a handful of activists like you with the dedication and skill to work for our country. If only we had a few people like you who mean what they say and work for it relentlessly and diligently.

    Reply
  2. Birhanu kebede says

    April 11, 2013 10:45 am at 10:45 am

    Dear Mr. Obang, you have been doing extraordinary jobs. Ethiopians have been displaced from their land and the Amhara people in particular are suffering from hunger. Their land has been leasing to foreigners.We Ethiopians have to unite to bring peace, democracy and justice for our country.

    God bless Ethiopia.

    Reply
  3. Solomon says

    April 14, 2013 07:09 am at 7:09 am

    Ato Obang, you are doing great and we have to expand our participation with you. I like your strategy and professionalism. Hope you will come to Calgary and address your effort and encourage all Ethiopians to join hand in hand wit you. We are hoping change from the policy of US towards Ethiopia.

    Reply
    • Abatu Seife says

      April 15, 2013 11:20 am at 11:20 am

      Mr. Obang, I appreciate your extensive and well strategized effort to bring out in the open the horrendous oppression and genocidal criminal activities that is being perpetuated in Ethiopia and very much wish to cooperate and pull our resources together in our joint struggle, for our Ethiopian people, on our part globally spearheaded by SHENGO. Please let us exchange telephone numbers and mailing addresses.

      We are going to hold our 2nd Annual Conference in Washington DC on July 2 to 5, 2013, and I would be honored to be your guest. My P.O.Box is 6793, Arlington VA, 22206

      God Bless You.

      Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am
  • የኦነግ ሸኔ አባላትን ዕድሜ ለማሳጠር የጂፒኤስ ቴክኖሎጂ ጥቅም ላይ እየዋለ ነው December 7, 2020 12:38 am
  • የቆሰሉ ወታደሮች በጠቅላይ ሚኒስትሩ ተጎበኙ December 6, 2020 11:41 pm
  • “ከዚህ በኋላ ይዘን እንታገላለን እንጂ ሠጥተን አንጠይቅም” ኮሎኔል ደመቀ December 2, 2020 12:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule