• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

መሬት ነጠቃ ለአሜሪካ ም/ቤት ሊቀርብ ነው

April 8, 2013 09:08 am by Editor 4 Comments

በመጪው ሰኞ ሚያዚያ7፤2005ዓም (April 15፣ 2013) በአፍሪካ ስለሚደረገው የመሬት ነጠቃ አስመልክቶ የአሜሪካ ም/ቤት የፖሊሲ አውጪዎችና በጉዳዩ ላይ የሚሟገቱ የሰብዓዊ መብት ተከራካሪዎችን እንዲሁም ባለሙያዎችን ሃሳብ ለማዳመጥ ስብሰባ መጥራቱ ታወቀ፡፡

በአሜሪካ የተወካዮች ምክርቤት በአፍሪካ፣ በዓለምአቀፍ ጤና፣ በዓለምአቀፍ የሰብዓዊ መብቶችና ዓለምአቀፋዊ ድርጅቶች ንዑስኮሚቴ ሊቀመንበር የሆኑት ክሪስ ስሚዝ ከፍተኛ አማካሪና የአፍሪካ ኤክስፐርት የሆኑት ግሬጎሪ ሲምፐኪንስ ስብሰባውን እንደሚመሩትም ከወጣው መረጃ ለመረዳት ተችሏል፡፡

በአፍሪካ የሚካሄደውን የመሬት ነጠቃ አስመልክቶ በተጠራው ስብሰባ ላይ መግለጫ ከሚሰጡት አፍሪካውያን መካከል ጋናዊው ምሁር ዶ/ር ጆርጅ አዪቴ የሚገኙበት ሲሆን ከኢትዮጵያ ብቸኛው ተጠቃሽ የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶ ናቸው፡፡ ከኦክላንድ ተቋም ጋር በመሆን አቶ ኦባንግ የሚመሩት የጋራ ንቅናቄ በቅርቡ በአማርኛ ተተርጉሞ ይፋ የሚሆነውን ጥናታዊ ዘገባ ማዘጋጀቱ ይታወቃል፡፡ ይህንኑ በመሬት ነጠቃ ላይ የተዘጋጀውን ዘገባ የጠቀሰው የስብሰባው መጥሪያ በጉዳዩ ላይ አኢጋን ያከናወነውን የምርመራ ሪፖርት ጠቅሷል፡፡

በአሁኑ ጊዜ በተለያዩ የሥራ ጉዳዮች ላይ በመጠመድ በዋሺንግተን ዲሲ ከተማ የሚገኙትን አቶ ኦባንግን ጎልጉል በስልክ ባነጋገረበት ወቅት እንደተናገሩት ድርጅታቸው መነሻውንና መድረሻውን እንዲሁም የሚያከናውነውን ተግባራት በዕቅድ የሚፈጽም መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ የጋራ ንቅናቄው ለዚህ ዕውቅናና ስብሰባ መጠራቱ በራሱ ታላቅ ድል መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ የሰላማዊ ትግል ከወረቀት የማያልፍና የአቤቱታ ማስፈረም (የፔቲሽን) ትግል ብቻ እንዳልሆነ በቅርቡ ሕንድ በመሄድ በዚሁ የመሬት ነጠቃ ጉዳይ ላይ ያደረጉት ስብሰባና ውይይት በኢንቨስትመንት ስም በኢትዮጵያ መሬት እየዘረፉ ላሉት ኩባንያዎች ከፍተኛ ችግር እንደፈጠረባቸው እንደማስረጃ ጠቅሰዋል፡፡

ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ካለበት ድርጅታዊና አገራዊ ግዴታ አኳያ የአሜሪካ ምክርቤት ሕግ አውጪ አካላትን በኢትዮጵያ ስላለው ሁኔታ እያሳወቀና እየወተወተ መሆኑን የተናገሩት አቶ ኦባንግ፤ በተለይ በቅርቡ የሚካሄደውን ምርጫ፣ የፖለቲካ እስረኞችን ሁኔታ፣ ከየቦታው እየተፈናቀሉ ያሉትን ዜጎች፣ አፋኝ የሆኑትን የመያድና የጸረ-ሽብርተኝነት ሕጎችን እንዲሁም የመንደር ምስረታንና አስገድዶ ማስፈርን በተመለከተ በርካታ ጉዳዮች በተጠናከረ ሁኔታ እየሠራበት እንደሆነ በተለይ ለጎልጉል ገልጸዋል፡፡ በመጪው ሰኞ በሚደረገው ስብሰባ የሚገኘውን ውጤት ካሁኑ በግልጽ ለመናገር ባይቻልም ስብሰባው ከላይ ከተጠቀሱት ጉዳዮች አንዱ እንደመሆኑ ወደፊት በምክርቤት ለሚደረጉ ውሳኔዎች እንደ ግብዓት እንደሚያገለግል አስታውቀዋል፡፡  

በአፍሪካ እየተካሄደ ስላለው የመሬት ነጠቃ 11የአፍሪካ አገራትን የሚወክሉ 11 ድርጅቶች ኅብረት በመፍጠር ተጽዕኖ ከማድረግ እስከ ፖሊሲ ማስቀየር ሥራ እየሠሩ መሆናቸውና ከእነዚህም ድርጅቶች መካከል ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ አንዱ መሆኑ ይታወቃል፡፡

የሰኞው ስብሰባ መርሃግብር ይህንን ይመስላል፡፡

THE LAND-GRAB ISSUE IN AFRICA

A Discussion with Advocates & Policymakers

Monday, April 15 at 2:00PM

U.S. CONGRESS: Rayburn House Office Building

(45 Independence Avenue SW, Washington, DC)

 A SHORT DOCUMENTARY ON LAND GRABBING WILL BE SCREENED

Land grabbing is becoming the single most combative issue in Africa. It involves large-scale land acquisitions by foreign countries and corporations for farming, biofuels, logging and minerals. Unlike land acquisitions in the United States and Europe where purchasers pay the fair market values for land, in Africa unscrupulous deals are displacing thousands of farmers and leaving local communities in abject poverty, while government officials benefit from land sales and leases.

PANALISTS

 BINTA TERRIER

Ms. Terrier is Co-Founder and Executive Director of Partnership League for Africa’s Development (PLAD). PLAD was created to focus on education, health, land-rights and agriculture as the cornerstone to address the human rights problem in Africa. Educated as an economist she is becoming a leading female voice for Africa’s development and governance.

DR. GEORGE AYITTEY

Dr. Ayittey is a distinguished Economist and Professor at the American University, Washington, DC. He is the founder and chair of the Free Africa Foundation and an associate scholar at the Foreign Policy Research Institute. Dr. Ayittey has championed the argument that: Africa is poor because she is not free, that the primary cause of African poverty is less a result of the oppression and mismanagement by colonial powers, but rather a result of modern oppressive native autocrats.

OBANG METHO

Mr. Metho is Executive Director of the SMNE (www.solidaritymovement.org), a social justice movement of diverse Ethiopians that joint-sponsored with the think tank, Oakland Institute, to produce the Ethiopian portion of the comprehensive investigative report, Understanding Land Investment Deals in Africa, published in June 2011. Mr. Obang is a human rights activist who tirelessly advocates for human rights, justice, freedom and environment, enhanced accountability in politics and peace in Africa for over 10 years.

RICK JACOBSON

Mr. Jacobson works on land grab issues in Africa as a Team Leader for International Forest Policy and Environmental Governance for Global Witness.

MODERATOR: GREGORY SIMPKINS

Mr. Simpkins is an Africa Expert and Senior Advisor, to Congressman Chris Smith the Chairman of the U.S. House Subcommittee on Africa, Global Health, Global Human Rights and International Organizations.

Questions: please contact: Binta@allafr.org 301-802-2233 or kwame@rebeccaproject.org 202-406-0911


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Teshale says

    April 10, 2013 11:33 pm at 11:33 pm

    Obang, God bless you. You have such a skill to find your way into important international fora where our concern can receive international attention. I wish we had a handful of activists like you with the dedication and skill to work for our country. If only we had a few people like you who mean what they say and work for it relentlessly and diligently.

    Reply
  2. Birhanu kebede says

    April 11, 2013 10:45 am at 10:45 am

    Dear Mr. Obang, you have been doing extraordinary jobs. Ethiopians have been displaced from their land and the Amhara people in particular are suffering from hunger. Their land has been leasing to foreigners.We Ethiopians have to unite to bring peace, democracy and justice for our country.

    God bless Ethiopia.

    Reply
  3. Solomon says

    April 14, 2013 07:09 am at 7:09 am

    Ato Obang, you are doing great and we have to expand our participation with you. I like your strategy and professionalism. Hope you will come to Calgary and address your effort and encourage all Ethiopians to join hand in hand wit you. We are hoping change from the policy of US towards Ethiopia.

    Reply
    • Abatu Seife says

      April 15, 2013 11:20 am at 11:20 am

      Mr. Obang, I appreciate your extensive and well strategized effort to bring out in the open the horrendous oppression and genocidal criminal activities that is being perpetuated in Ethiopia and very much wish to cooperate and pull our resources together in our joint struggle, for our Ethiopian people, on our part globally spearheaded by SHENGO. Please let us exchange telephone numbers and mailing addresses.

      We are going to hold our 2nd Annual Conference in Washington DC on July 2 to 5, 2013, and I would be honored to be your guest. My P.O.Box is 6793, Arlington VA, 22206

      God Bless You.

      Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሤራ አክሻፊው ጎንደር ለሦስተኛ ጊዜ ታሪክ ሠራ May 10, 2023 09:25 am
  • ማር በከፍተኛ ደረጃ የኮንትሮባንድ ሰለባ ሆኗል May 9, 2023 09:24 am
  • ኦነግ በኦሮሚያ ሪፈረንደም እንዲካሄድ መጠየቁ ለሰላም ንግግሩ ዕንቅፋት ሆነ May 4, 2023 01:12 am
  • መረጃ ቲቪ ያጋራው አሳሳች መረጃ May 2, 2023 12:37 pm
  • “ከፈጣሪ በታች መከላከያ የሁላችን ዋስ ጠበቃ ነው፤ ትልቅ ይቅርታ እንጠይቃለን” April 13, 2023 10:19 am
  • በትግራይ የ”ልጆቻችን የት ናቸው?” ጥያቄ እየተሰማ ነው April 13, 2023 08:56 am
  • በትህነግ የፈረሰው የአክሱም ኤርፖርት ያስከተለው ዘርፈብዙ ኪሣራ April 13, 2023 03:21 am
  • “የከተማው ነዋሪ በመሰላቸቱ ተፈናቃዮች ከፍተኛ የምግብ ችግር” ገጥሟቸዋል April 12, 2023 09:23 am
  • ከዕድሜ ልክ እስከ 20 ዓመት ቅጣት ተበይኖባቸዋል April 11, 2023 02:58 pm
  • የኡጋንዳ የክልሎች ሚኒስትር በቆርቆሮ ሌብነት ተጠርጥረው ታሰሩ April 10, 2023 03:59 pm
  • ታከለ ከተነሳ በኋላ የመዐድን ሌቦች እየተያዙ ነው April 6, 2023 02:53 pm
  • አገር ለማተራመስ ያለመ የምሁራን፣ የሚዲያ ባለቤቶችና አክቲቪስቶች ህቡዕ ቡድን ተያዘ April 4, 2023 10:07 am
  • በ10 ዓመት ውስጥ ከ44 ቢሊየን ዶላር በላይ ሸሽቷል April 4, 2023 09:26 am
  • አየር ጨብጦ አሁን ያለውን መንግሥት ከሥልጣን ልቀቁ አይሆንም March 29, 2023 09:47 am
  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule