• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሰሞኑ “የኦሮምያ ግርግር” ግራ ገብቶኛል

January 7, 2016 05:43 am by Editor 1 Comment

በሁለት ደረጃ የሚቀርቡ ጥያቄዎች አሉኝ፤–

አንድ፡– ግርግሩ የኦሮምያ ነው? ወይስ የኢትዮጵያ? ወይስ ኦሮምያ ከኢትዮጵያ ተለይቷል?

ሁለት፡– የኢትዮጵያ የመሬት ጉዳይ ኦሮሞዎችን ብቻ የሚመለከት ነው? ወይስ የኢትዮጵያን ሕዝብ በሙሉ?

አንደኛ፣ ግልጽ ከሆነው እውነት እንነሣ፤ ኦሮምያ ከኢትዮጵያ አልተለየም፤ ስለዚህም ግርግሩ የኢትዮጵያ ነው እንጂ የኦሮምያ አይደለም፤ ጥንቱኑ ለማጋጨት የተሰጠውን ስያሜ በስምነቱ ከማጽደቅ በላይ ለታቀደው ዓላማ አመቺ መሣሪያ ማድረግ ነው፤ ይህ ደግሞ በቅድሚያ መሸነፍን የሚያረጋግጥ በመሆኑ ከወያኔ በቀር ደጋፊ ያለው አይመስለኝም፤ ቁርጠኛ ትግል ቁርጠኛ ዓለማና ቁርጠኛ ስልት ያስፈልገዋል፤ ስለዚህም ቁርጠኛ መሪ ያስፈልገዋል፤ የሕመሙን መርዝ እየተጎነጩ ከሕመሙ ፈውስ ለማግኘት አይቻልም፤

ግርግሩ የኦሮሞ ከተባለ ሁለት ውጤቶች ይከተላሉ፤

አንዱ ውጤት ከኦሮሞ በቀር ሌላውን ሕዝብ አያገባውም ማለት ይሆናል፤

ሁለተኛው ውጤት የልዩነቱ ባለቤቶችና ተፋላሚዎች ኦሮሞዎችና ወያኔዎች ብቻ ናቸው ማለት ነው፤ ይህ ትልቅ አደጋ አለበት፡፡

አደጋው ወደሁለተኛው ጥያቄ ይመራናል፤ ገብቶኝ እንደሆነ የግርግሩ ምክንያት ሁለት ናቸው፤ አንዱ ከቤት-ንብረት መፈናቀል ነው፤ የዜግነት መብትና መገለጫ የሆነውን መሬት ማጣት ነው፤ ሁለቱም መሰረታዊ የሆኑ የኢትዮጵያዊነትን የዜግነት መብቶች ሚደፈጥጡ ናቸው፤ ልብ በሉ የኦሮሞን የዜግነት መብቶች ይደፈጥጣል አላልኩም፤ የኢትዮጵያውያንን ሁሉ መሠረታዊ መብቶች የሚደፈጥጥ ነው፤ ይህ የማያጠራጥር እውነት ነው፤ ይህንን ከተቀበልን ጉዳዩ የኦሮሞ ብቻ አይደለም፤ ግርግሩም የኦሮሞ ብቻ አይደለም፡፡

ትልቁ አደጋ ያሁንን ግርግር የኦሮምያ ብቻ ካደረግነው ወደፊት ያው ጉዳይ በሌሎች ጎሣዎች መሀከል ሊነሣ ነው፤ ሌሎች ግርግሮች ሊያስፈልጉ ነው፡፡

ጉዳዩ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ከሆነ ትግሉም የኢትዮጵያ ሕዝብ በሙሉ ነው፡፡

ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም
ታኅሣሥ 2008

(ምንጭ: Mesfin Wolde-Mariam Blog)

Filed Under: Opinions Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    January 11, 2016 11:10 pm at 11:10 pm

    አዎን! ግርግሩ ግራ ያጋባል….!?
    (ግርግር ለሥልጣን ያመቻል ግን ጭቆናን ለውጦ ጨቋኝን ያቀያይር እንደሆን እንጂ መፍትሔ አይሆንም።)
    (፩) – ግርግሩ የኦሮምያ ነው? ወይስ የኢትዮጵያ?
    ** ሠልፈኛው ለብቻ!..ፖለቲካ ተንታኙ ለብቻ! ነፃ አውጭው ለብቻ!… ግራ የገባውና ያልገባው ለብቻ!..የገባውና መግቢያ የሚፈልገው ለብቻ! …ሳይገባው ግራ የሚያጋባው ለብቻ! መግለጫው(መላጫው) ለብቻ!ግራ ተጋብቶ የሚያግባበው ለብቻ! ማስፈራሪያና ዛቻ አዘል ፅሑፍ የሚለቀው ለብቻ! አንድንት ኅብርት አሁን በአስቸኳይ ዋ! በኋላ የሚሉና እንደ ኢህአዴግ አስበው እንደ ዲሞክራሲያዊ ብሔርተኛ ተውነው ብሔራዊ አመፅ የተጠናበረባቸው…. በቋንቋና ብሔር ተኮር በመፈቃቀድና መፈቃቀር በደስታ ኖረው ከፌደራል መንግስት በጉርብትና እንኖራለን እንጂ በፌደራል ሥርዓት አንመራም የሚሉ!?(ኦሮምያ ከኢትዮጵያ ተለይቷል?) በአትድረሱብንና በድረሱልን መካከል ያለው ውዥንብር፣ይህ በበኩሌ የራስን ድክመት በሌላው ለጥፎ መጯጯህ(የጨረባ ተስካር) በጭራሽ ሊታረምም ሊወገድም ያልቻለ የዓርባ ዓመት አዙሪት ነው።
    ** አንደኛው “የጋኔልና የሰይጣን የጥንቆላና መልክተኛ ሰልፍ” ሲል ሌላው “የቡዳ ፓለቲካ” ሲል ያደምቀዋል። ሕገመንግስቱ ይከበር ሲሉ ይጮሃሉ…ትነአግ/ኢህአዴግ እያስከበርኩ ነው ሲል ሌላው ተነስቶ ተከፋፈልን ተለያየን ይልና ያለቅሳል…ያላቅሳል፡ከተማ ሲስፋፋ ማንነታችን ይጠፋል ባሕልና ቋንቋችን ይበከላል ሲል ይፎክራል! ወዲያው ቋንቋችን የፌደራል የሥራ ቋንቋ ይሁን ያለ ውድድር ምክር ቤቱም ፖለቲካል ኢኮኖሚውም እኛ ካልገባን ቃል የተገባልን ልዩ ጥቅማጥቅማችን ይከበር ይላል ። ‘ልዩነታችን ውበታችን’ ሲባል ሁሉም ይጨፍራል!! ቀጥሎ አንከፋፈልም አናሳ ብሔር በትልቅ ብሔር አይገዛም! ይላል…ይህ የእኛ ያም የእኛ! ‘ሐጎስን’ ንቀለው ‘ቶላን’ ትከለው ሲል ሌላው የእኔ ቱ ነው? የእነሱ የእኔ አደለምን ማለት ነው!? ሲል የተነሱበትን ንፋስ እረስተው ሌላ እሳት ጭረው ቀጠሉ… ሁሉም በክልሉ በቋንቋው ‘ተከልሎና ተከልክሎ’ የመፈክሩ መልዕክት እንኳ ለጎረቤቱ ሳይገባው ሕፃናት ከፊት አሰልፎ ሕዝባዊ ንቅናቄ በፍልጥ እነጨትና ድንጋይ ወታደሩን መተነፋፋሻ አሳጣው አተረማመሰው!አርበደበደው!(ልክ ተስፋዬ ግበረእባብና ጀዋር ሙድ!)ነፃ አውጭው ምንሊክ ቤተመንግስት ሊቆጣጠር ፳ ኪሜ ቀረው! ታይቶም፣ ተሰምቶም፣ የማይታወቅ አብዮት (እራስን ማድነቅ! )እና መጃጃል። ታዲያማ እነ አጅሬዎችም (ሙስና መሮች፣አድርባዮች፣አውርቶአደሮች፣ኪራይ ሰብሳቢዎች፣ ቤተሰባዊ ደላሎች ስለ ሚ/ሩ ብለው መፈረም አቅም ያላቸው) ይችን ይዘው ጦራቸውን ጭነው ከተፍ አሉ የድሃ ልጅ በባዶ ሆዱ ኢላማ ሆነ ማን ተጠተቀመ?…. “ያልታደለች አፍሳ ለቀመች”
    …” ግርግሩ የኦሮሞ ከተባለ ሁለት ውጤቶች ይከተላሉ፤ አንዱ ውጤት ከኦሮሞ በቀር ሌላውን ሕዝብ አያገባውም ማለት ይሆናል፤ ሁለተኛው ውጤት የልዩነቱ ባለቤቶችና ተፋላሚዎች ኦሮሞዎችና ትነአግ/ ህወአት ብቻ ናቸው ማለት ነው፡ ይህ ትልቅ አደጋ አለበት፡፡(፩) ከቤት-ንብረት መፈናቀል(፪) የዜግነት መብትና መገለጫ የሆነውን መሬት ማጣት ሁለቱም መሰረታዊ የሆኑ የኢትዮጵያዊነትን የዜግነት መብቶች የሚደፈጥጡ ናቸው።ግርግሩን የኦሮሞ ብቻ ማድርግ ጥንቱኑ ለማጋጨት የተሰጠውን ስያሜ በስምነቱ ከማጽደቅ በላይ ለታቀደው ዓላማ አመቺ መሣሪያ ማድረግ ነው፤ ይህ ደግሞ በቅድሚያ መሸነፍን የሚያረጋግጥ በመሆኑ ከትነአግ/ኢህአዴግ በቀር ደጋፊ ያለው አይመስለኝም፤ ጉዳዩ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ከሆነ ትግሉም የኢትዮጵያ ሕዝብ በሙሉ መሆኑ ታምኖበት ቁርጠኛ ትግል! ቁርጠኛ ዓለማ! ቁርጠኛ ስልት! ቁርጠኛ መሪ ያስፈልገዋል።አራት ነጥብ።
    **” የሕመሙን መርዝ እየተጎነጩ ከሕመሙ ፈውስ ለማግኘት አይቻልም ሲባል “ሲፈጀኝ በማንኪያ ሳይፈጀኝ በጄ” ዘላቂ ትግልና ዘላቂ አስተማማኝ ለውጥ ማግኘት በጭራሽ አይቻልም። በሁለቱም ጎራ “ልታስጠብብ ሄዳ አሰፍታ መጣች!” እንዳይሆን አደራ! አደራ! ስለ ሀገረ ኢትዮጵያ ሠላም የሚያስቡ ሠላም ይክረሙ!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
Copyright © 2026 · Goolgule