• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሰሞኑ “የኦሮምያ ግርግር” ግራ ገብቶኛል

January 7, 2016 05:43 am by Editor 1 Comment

በሁለት ደረጃ የሚቀርቡ ጥያቄዎች አሉኝ፤–

አንድ፡– ግርግሩ የኦሮምያ ነው? ወይስ የኢትዮጵያ? ወይስ ኦሮምያ ከኢትዮጵያ ተለይቷል?

ሁለት፡– የኢትዮጵያ የመሬት ጉዳይ ኦሮሞዎችን ብቻ የሚመለከት ነው? ወይስ የኢትዮጵያን ሕዝብ በሙሉ?

አንደኛ፣ ግልጽ ከሆነው እውነት እንነሣ፤ ኦሮምያ ከኢትዮጵያ አልተለየም፤ ስለዚህም ግርግሩ የኢትዮጵያ ነው እንጂ የኦሮምያ አይደለም፤ ጥንቱኑ ለማጋጨት የተሰጠውን ስያሜ በስምነቱ ከማጽደቅ በላይ ለታቀደው ዓላማ አመቺ መሣሪያ ማድረግ ነው፤ ይህ ደግሞ በቅድሚያ መሸነፍን የሚያረጋግጥ በመሆኑ ከወያኔ በቀር ደጋፊ ያለው አይመስለኝም፤ ቁርጠኛ ትግል ቁርጠኛ ዓለማና ቁርጠኛ ስልት ያስፈልገዋል፤ ስለዚህም ቁርጠኛ መሪ ያስፈልገዋል፤ የሕመሙን መርዝ እየተጎነጩ ከሕመሙ ፈውስ ለማግኘት አይቻልም፤

ግርግሩ የኦሮሞ ከተባለ ሁለት ውጤቶች ይከተላሉ፤

አንዱ ውጤት ከኦሮሞ በቀር ሌላውን ሕዝብ አያገባውም ማለት ይሆናል፤

ሁለተኛው ውጤት የልዩነቱ ባለቤቶችና ተፋላሚዎች ኦሮሞዎችና ወያኔዎች ብቻ ናቸው ማለት ነው፤ ይህ ትልቅ አደጋ አለበት፡፡

አደጋው ወደሁለተኛው ጥያቄ ይመራናል፤ ገብቶኝ እንደሆነ የግርግሩ ምክንያት ሁለት ናቸው፤ አንዱ ከቤት-ንብረት መፈናቀል ነው፤ የዜግነት መብትና መገለጫ የሆነውን መሬት ማጣት ነው፤ ሁለቱም መሰረታዊ የሆኑ የኢትዮጵያዊነትን የዜግነት መብቶች ሚደፈጥጡ ናቸው፤ ልብ በሉ የኦሮሞን የዜግነት መብቶች ይደፈጥጣል አላልኩም፤ የኢትዮጵያውያንን ሁሉ መሠረታዊ መብቶች የሚደፈጥጥ ነው፤ ይህ የማያጠራጥር እውነት ነው፤ ይህንን ከተቀበልን ጉዳዩ የኦሮሞ ብቻ አይደለም፤ ግርግሩም የኦሮሞ ብቻ አይደለም፡፡

ትልቁ አደጋ ያሁንን ግርግር የኦሮምያ ብቻ ካደረግነው ወደፊት ያው ጉዳይ በሌሎች ጎሣዎች መሀከል ሊነሣ ነው፤ ሌሎች ግርግሮች ሊያስፈልጉ ነው፡፡

ጉዳዩ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ከሆነ ትግሉም የኢትዮጵያ ሕዝብ በሙሉ ነው፡፡

ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም
ታኅሣሥ 2008

(ምንጭ: Mesfin Wolde-Mariam Blog)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    January 11, 2016 11:10 pm at 11:10 pm

    አዎን! ግርግሩ ግራ ያጋባል….!?
    (ግርግር ለሥልጣን ያመቻል ግን ጭቆናን ለውጦ ጨቋኝን ያቀያይር እንደሆን እንጂ መፍትሔ አይሆንም።)
    (፩) – ግርግሩ የኦሮምያ ነው? ወይስ የኢትዮጵያ?
    ** ሠልፈኛው ለብቻ!..ፖለቲካ ተንታኙ ለብቻ! ነፃ አውጭው ለብቻ!… ግራ የገባውና ያልገባው ለብቻ!..የገባውና መግቢያ የሚፈልገው ለብቻ! …ሳይገባው ግራ የሚያጋባው ለብቻ! መግለጫው(መላጫው) ለብቻ!ግራ ተጋብቶ የሚያግባበው ለብቻ! ማስፈራሪያና ዛቻ አዘል ፅሑፍ የሚለቀው ለብቻ! አንድንት ኅብርት አሁን በአስቸኳይ ዋ! በኋላ የሚሉና እንደ ኢህአዴግ አስበው እንደ ዲሞክራሲያዊ ብሔርተኛ ተውነው ብሔራዊ አመፅ የተጠናበረባቸው…. በቋንቋና ብሔር ተኮር በመፈቃቀድና መፈቃቀር በደስታ ኖረው ከፌደራል መንግስት በጉርብትና እንኖራለን እንጂ በፌደራል ሥርዓት አንመራም የሚሉ!?(ኦሮምያ ከኢትዮጵያ ተለይቷል?) በአትድረሱብንና በድረሱልን መካከል ያለው ውዥንብር፣ይህ በበኩሌ የራስን ድክመት በሌላው ለጥፎ መጯጯህ(የጨረባ ተስካር) በጭራሽ ሊታረምም ሊወገድም ያልቻለ የዓርባ ዓመት አዙሪት ነው።
    ** አንደኛው “የጋኔልና የሰይጣን የጥንቆላና መልክተኛ ሰልፍ” ሲል ሌላው “የቡዳ ፓለቲካ” ሲል ያደምቀዋል። ሕገመንግስቱ ይከበር ሲሉ ይጮሃሉ…ትነአግ/ኢህአዴግ እያስከበርኩ ነው ሲል ሌላው ተነስቶ ተከፋፈልን ተለያየን ይልና ያለቅሳል…ያላቅሳል፡ከተማ ሲስፋፋ ማንነታችን ይጠፋል ባሕልና ቋንቋችን ይበከላል ሲል ይፎክራል! ወዲያው ቋንቋችን የፌደራል የሥራ ቋንቋ ይሁን ያለ ውድድር ምክር ቤቱም ፖለቲካል ኢኮኖሚውም እኛ ካልገባን ቃል የተገባልን ልዩ ጥቅማጥቅማችን ይከበር ይላል ። ‘ልዩነታችን ውበታችን’ ሲባል ሁሉም ይጨፍራል!! ቀጥሎ አንከፋፈልም አናሳ ብሔር በትልቅ ብሔር አይገዛም! ይላል…ይህ የእኛ ያም የእኛ! ‘ሐጎስን’ ንቀለው ‘ቶላን’ ትከለው ሲል ሌላው የእኔ ቱ ነው? የእነሱ የእኔ አደለምን ማለት ነው!? ሲል የተነሱበትን ንፋስ እረስተው ሌላ እሳት ጭረው ቀጠሉ… ሁሉም በክልሉ በቋንቋው ‘ተከልሎና ተከልክሎ’ የመፈክሩ መልዕክት እንኳ ለጎረቤቱ ሳይገባው ሕፃናት ከፊት አሰልፎ ሕዝባዊ ንቅናቄ በፍልጥ እነጨትና ድንጋይ ወታደሩን መተነፋፋሻ አሳጣው አተረማመሰው!አርበደበደው!(ልክ ተስፋዬ ግበረእባብና ጀዋር ሙድ!)ነፃ አውጭው ምንሊክ ቤተመንግስት ሊቆጣጠር ፳ ኪሜ ቀረው! ታይቶም፣ ተሰምቶም፣ የማይታወቅ አብዮት (እራስን ማድነቅ! )እና መጃጃል። ታዲያማ እነ አጅሬዎችም (ሙስና መሮች፣አድርባዮች፣አውርቶአደሮች፣ኪራይ ሰብሳቢዎች፣ ቤተሰባዊ ደላሎች ስለ ሚ/ሩ ብለው መፈረም አቅም ያላቸው) ይችን ይዘው ጦራቸውን ጭነው ከተፍ አሉ የድሃ ልጅ በባዶ ሆዱ ኢላማ ሆነ ማን ተጠተቀመ?…. “ያልታደለች አፍሳ ለቀመች”
    …” ግርግሩ የኦሮሞ ከተባለ ሁለት ውጤቶች ይከተላሉ፤ አንዱ ውጤት ከኦሮሞ በቀር ሌላውን ሕዝብ አያገባውም ማለት ይሆናል፤ ሁለተኛው ውጤት የልዩነቱ ባለቤቶችና ተፋላሚዎች ኦሮሞዎችና ትነአግ/ ህወአት ብቻ ናቸው ማለት ነው፡ ይህ ትልቅ አደጋ አለበት፡፡(፩) ከቤት-ንብረት መፈናቀል(፪) የዜግነት መብትና መገለጫ የሆነውን መሬት ማጣት ሁለቱም መሰረታዊ የሆኑ የኢትዮጵያዊነትን የዜግነት መብቶች የሚደፈጥጡ ናቸው።ግርግሩን የኦሮሞ ብቻ ማድርግ ጥንቱኑ ለማጋጨት የተሰጠውን ስያሜ በስምነቱ ከማጽደቅ በላይ ለታቀደው ዓላማ አመቺ መሣሪያ ማድረግ ነው፤ ይህ ደግሞ በቅድሚያ መሸነፍን የሚያረጋግጥ በመሆኑ ከትነአግ/ኢህአዴግ በቀር ደጋፊ ያለው አይመስለኝም፤ ጉዳዩ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ከሆነ ትግሉም የኢትዮጵያ ሕዝብ በሙሉ መሆኑ ታምኖበት ቁርጠኛ ትግል! ቁርጠኛ ዓለማ! ቁርጠኛ ስልት! ቁርጠኛ መሪ ያስፈልገዋል።አራት ነጥብ።
    **” የሕመሙን መርዝ እየተጎነጩ ከሕመሙ ፈውስ ለማግኘት አይቻልም ሲባል “ሲፈጀኝ በማንኪያ ሳይፈጀኝ በጄ” ዘላቂ ትግልና ዘላቂ አስተማማኝ ለውጥ ማግኘት በጭራሽ አይቻልም። በሁለቱም ጎራ “ልታስጠብብ ሄዳ አሰፍታ መጣች!” እንዳይሆን አደራ! አደራ! ስለ ሀገረ ኢትዮጵያ ሠላም የሚያስቡ ሠላም ይክረሙ!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm
  • የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት? January 23, 2025 03:41 pm
  • ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ? January 23, 2025 03:04 pm
  • የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተወልደ አስተዳደር ዘመን ለተሠራ ስህተት 425ሺ ዶላር ተቀጣ December 14, 2024 01:44 am
  • በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል November 27, 2024 12:09 pm
  • የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን እንዲያርም ጥብቅ መመሪያ ተሰጠው November 27, 2024 11:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule