• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሰሞኑ “የኦሮምያ ግርግር” ግራ ገብቶኛል

January 7, 2016 05:43 am by Editor 1 Comment

በሁለት ደረጃ የሚቀርቡ ጥያቄዎች አሉኝ፤–

አንድ፡– ግርግሩ የኦሮምያ ነው? ወይስ የኢትዮጵያ? ወይስ ኦሮምያ ከኢትዮጵያ ተለይቷል?

ሁለት፡– የኢትዮጵያ የመሬት ጉዳይ ኦሮሞዎችን ብቻ የሚመለከት ነው? ወይስ የኢትዮጵያን ሕዝብ በሙሉ?

አንደኛ፣ ግልጽ ከሆነው እውነት እንነሣ፤ ኦሮምያ ከኢትዮጵያ አልተለየም፤ ስለዚህም ግርግሩ የኢትዮጵያ ነው እንጂ የኦሮምያ አይደለም፤ ጥንቱኑ ለማጋጨት የተሰጠውን ስያሜ በስምነቱ ከማጽደቅ በላይ ለታቀደው ዓላማ አመቺ መሣሪያ ማድረግ ነው፤ ይህ ደግሞ በቅድሚያ መሸነፍን የሚያረጋግጥ በመሆኑ ከወያኔ በቀር ደጋፊ ያለው አይመስለኝም፤ ቁርጠኛ ትግል ቁርጠኛ ዓለማና ቁርጠኛ ስልት ያስፈልገዋል፤ ስለዚህም ቁርጠኛ መሪ ያስፈልገዋል፤ የሕመሙን መርዝ እየተጎነጩ ከሕመሙ ፈውስ ለማግኘት አይቻልም፤

ግርግሩ የኦሮሞ ከተባለ ሁለት ውጤቶች ይከተላሉ፤

አንዱ ውጤት ከኦሮሞ በቀር ሌላውን ሕዝብ አያገባውም ማለት ይሆናል፤

ሁለተኛው ውጤት የልዩነቱ ባለቤቶችና ተፋላሚዎች ኦሮሞዎችና ወያኔዎች ብቻ ናቸው ማለት ነው፤ ይህ ትልቅ አደጋ አለበት፡፡

አደጋው ወደሁለተኛው ጥያቄ ይመራናል፤ ገብቶኝ እንደሆነ የግርግሩ ምክንያት ሁለት ናቸው፤ አንዱ ከቤት-ንብረት መፈናቀል ነው፤ የዜግነት መብትና መገለጫ የሆነውን መሬት ማጣት ነው፤ ሁለቱም መሰረታዊ የሆኑ የኢትዮጵያዊነትን የዜግነት መብቶች ሚደፈጥጡ ናቸው፤ ልብ በሉ የኦሮሞን የዜግነት መብቶች ይደፈጥጣል አላልኩም፤ የኢትዮጵያውያንን ሁሉ መሠረታዊ መብቶች የሚደፈጥጥ ነው፤ ይህ የማያጠራጥር እውነት ነው፤ ይህንን ከተቀበልን ጉዳዩ የኦሮሞ ብቻ አይደለም፤ ግርግሩም የኦሮሞ ብቻ አይደለም፡፡

ትልቁ አደጋ ያሁንን ግርግር የኦሮምያ ብቻ ካደረግነው ወደፊት ያው ጉዳይ በሌሎች ጎሣዎች መሀከል ሊነሣ ነው፤ ሌሎች ግርግሮች ሊያስፈልጉ ነው፡፡

ጉዳዩ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ከሆነ ትግሉም የኢትዮጵያ ሕዝብ በሙሉ ነው፡፡

ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም
ታኅሣሥ 2008

(ምንጭ: Mesfin Wolde-Mariam Blog)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    January 11, 2016 11:10 pm at 11:10 pm

    አዎን! ግርግሩ ግራ ያጋባል….!?
    (ግርግር ለሥልጣን ያመቻል ግን ጭቆናን ለውጦ ጨቋኝን ያቀያይር እንደሆን እንጂ መፍትሔ አይሆንም።)
    (፩) – ግርግሩ የኦሮምያ ነው? ወይስ የኢትዮጵያ?
    ** ሠልፈኛው ለብቻ!..ፖለቲካ ተንታኙ ለብቻ! ነፃ አውጭው ለብቻ!… ግራ የገባውና ያልገባው ለብቻ!..የገባውና መግቢያ የሚፈልገው ለብቻ! …ሳይገባው ግራ የሚያጋባው ለብቻ! መግለጫው(መላጫው) ለብቻ!ግራ ተጋብቶ የሚያግባበው ለብቻ! ማስፈራሪያና ዛቻ አዘል ፅሑፍ የሚለቀው ለብቻ! አንድንት ኅብርት አሁን በአስቸኳይ ዋ! በኋላ የሚሉና እንደ ኢህአዴግ አስበው እንደ ዲሞክራሲያዊ ብሔርተኛ ተውነው ብሔራዊ አመፅ የተጠናበረባቸው…. በቋንቋና ብሔር ተኮር በመፈቃቀድና መፈቃቀር በደስታ ኖረው ከፌደራል መንግስት በጉርብትና እንኖራለን እንጂ በፌደራል ሥርዓት አንመራም የሚሉ!?(ኦሮምያ ከኢትዮጵያ ተለይቷል?) በአትድረሱብንና በድረሱልን መካከል ያለው ውዥንብር፣ይህ በበኩሌ የራስን ድክመት በሌላው ለጥፎ መጯጯህ(የጨረባ ተስካር) በጭራሽ ሊታረምም ሊወገድም ያልቻለ የዓርባ ዓመት አዙሪት ነው።
    ** አንደኛው “የጋኔልና የሰይጣን የጥንቆላና መልክተኛ ሰልፍ” ሲል ሌላው “የቡዳ ፓለቲካ” ሲል ያደምቀዋል። ሕገመንግስቱ ይከበር ሲሉ ይጮሃሉ…ትነአግ/ኢህአዴግ እያስከበርኩ ነው ሲል ሌላው ተነስቶ ተከፋፈልን ተለያየን ይልና ያለቅሳል…ያላቅሳል፡ከተማ ሲስፋፋ ማንነታችን ይጠፋል ባሕልና ቋንቋችን ይበከላል ሲል ይፎክራል! ወዲያው ቋንቋችን የፌደራል የሥራ ቋንቋ ይሁን ያለ ውድድር ምክር ቤቱም ፖለቲካል ኢኮኖሚውም እኛ ካልገባን ቃል የተገባልን ልዩ ጥቅማጥቅማችን ይከበር ይላል ። ‘ልዩነታችን ውበታችን’ ሲባል ሁሉም ይጨፍራል!! ቀጥሎ አንከፋፈልም አናሳ ብሔር በትልቅ ብሔር አይገዛም! ይላል…ይህ የእኛ ያም የእኛ! ‘ሐጎስን’ ንቀለው ‘ቶላን’ ትከለው ሲል ሌላው የእኔ ቱ ነው? የእነሱ የእኔ አደለምን ማለት ነው!? ሲል የተነሱበትን ንፋስ እረስተው ሌላ እሳት ጭረው ቀጠሉ… ሁሉም በክልሉ በቋንቋው ‘ተከልሎና ተከልክሎ’ የመፈክሩ መልዕክት እንኳ ለጎረቤቱ ሳይገባው ሕፃናት ከፊት አሰልፎ ሕዝባዊ ንቅናቄ በፍልጥ እነጨትና ድንጋይ ወታደሩን መተነፋፋሻ አሳጣው አተረማመሰው!አርበደበደው!(ልክ ተስፋዬ ግበረእባብና ጀዋር ሙድ!)ነፃ አውጭው ምንሊክ ቤተመንግስት ሊቆጣጠር ፳ ኪሜ ቀረው! ታይቶም፣ ተሰምቶም፣ የማይታወቅ አብዮት (እራስን ማድነቅ! )እና መጃጃል። ታዲያማ እነ አጅሬዎችም (ሙስና መሮች፣አድርባዮች፣አውርቶአደሮች፣ኪራይ ሰብሳቢዎች፣ ቤተሰባዊ ደላሎች ስለ ሚ/ሩ ብለው መፈረም አቅም ያላቸው) ይችን ይዘው ጦራቸውን ጭነው ከተፍ አሉ የድሃ ልጅ በባዶ ሆዱ ኢላማ ሆነ ማን ተጠተቀመ?…. “ያልታደለች አፍሳ ለቀመች”
    …” ግርግሩ የኦሮሞ ከተባለ ሁለት ውጤቶች ይከተላሉ፤ አንዱ ውጤት ከኦሮሞ በቀር ሌላውን ሕዝብ አያገባውም ማለት ይሆናል፤ ሁለተኛው ውጤት የልዩነቱ ባለቤቶችና ተፋላሚዎች ኦሮሞዎችና ትነአግ/ ህወአት ብቻ ናቸው ማለት ነው፡ ይህ ትልቅ አደጋ አለበት፡፡(፩) ከቤት-ንብረት መፈናቀል(፪) የዜግነት መብትና መገለጫ የሆነውን መሬት ማጣት ሁለቱም መሰረታዊ የሆኑ የኢትዮጵያዊነትን የዜግነት መብቶች የሚደፈጥጡ ናቸው።ግርግሩን የኦሮሞ ብቻ ማድርግ ጥንቱኑ ለማጋጨት የተሰጠውን ስያሜ በስምነቱ ከማጽደቅ በላይ ለታቀደው ዓላማ አመቺ መሣሪያ ማድረግ ነው፤ ይህ ደግሞ በቅድሚያ መሸነፍን የሚያረጋግጥ በመሆኑ ከትነአግ/ኢህአዴግ በቀር ደጋፊ ያለው አይመስለኝም፤ ጉዳዩ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ከሆነ ትግሉም የኢትዮጵያ ሕዝብ በሙሉ መሆኑ ታምኖበት ቁርጠኛ ትግል! ቁርጠኛ ዓለማ! ቁርጠኛ ስልት! ቁርጠኛ መሪ ያስፈልገዋል።አራት ነጥብ።
    **” የሕመሙን መርዝ እየተጎነጩ ከሕመሙ ፈውስ ለማግኘት አይቻልም ሲባል “ሲፈጀኝ በማንኪያ ሳይፈጀኝ በጄ” ዘላቂ ትግልና ዘላቂ አስተማማኝ ለውጥ ማግኘት በጭራሽ አይቻልም። በሁለቱም ጎራ “ልታስጠብብ ሄዳ አሰፍታ መጣች!” እንዳይሆን አደራ! አደራ! ስለ ሀገረ ኢትዮጵያ ሠላም የሚያስቡ ሠላም ይክረሙ!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የሲኖዶሱ ውዝግብ አካሄድና መጪው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ February 6, 2023 02:03 am
  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule