የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቢኒያም ኔታኒያሁ አዛን “መታገስ የማይቻል ጩኸት” እየሆነ መጥቷል በማለት ተናገሩ፡፡ ጉዳዩ ያስቆጣቸው የሙስሊም መሪዎች ንግግሩ በሃይማኖታችን ላይ ማዕቀብ ለመጣል የተቃጣ ነው ብለውታል፡፡ ባለፈው አርብ በእስራኤል ሸንጎ የሊኩድ ፓርቲ አባላት በተገኙበት ኔታኒያሁ ባደረጉት ንግግር በእስራኤል የሚገኙ የአረብ ከተሞች ለአገሪቷ ሕግ መገዛት አለባቸው ብለዋል፡፡ ይህንንም በማድረግ ለአገሪቷና ለማኅበረሰቡ ግዴታቸውን መወጣት አለባቸው በማለት አስታውቀዋል፡፡ “በአብዛኛዎቹ የአረብ ከተሞች ሕግ አይከበርም፤ ይህም አዛን እና ከአንድ በላይ ሚስት ማግባት ተጠቃሽ ናቸው” በማለት ቢኒያም ኔታኒያሁ የተናገሩ ሲሆን ከዚህ አኳያ ከበርካታ መስጊዶች የሚሰማው አዛን “መታገስ የማይቻል ጩኸት እያስከተለ” ስለሆነ መንግሥታቸው ሕግ ሊያወጣ መወሰኑን አስታውቀዋል፡፡ አዛን … [Read more...] about አዛን “መታገስ የማይቻል ጩኸት” እያስከተለ ነው – ኔታኒያሁ
News
የትግራይ ነጋዴዎችን ለመጥቀም አዲስ የበርበሬ አዋጅ በጎጃም
ኢትዮጵያን በነጻ አውጪ ስም እየገዛ ያለው የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሃት) በተለይ በምዕራብ ጎጃም አካባቢ የደነገገው አዲስ የበርበሬ አዋጅ ችግር እያስከተለ መሆኑን የጎልጉል እማኝ ዘጋቢ (ireporter) በላኩልን መረጃ አስታውቀዋል፡፡ እንደ እማኝ ዘጋቢው ከሆነ አዋጁ የወጣው በ2002ዓም ሲሆን በሥራ ላይ መዋል የጀመረው በዚህ ዓመት እንደሆነ ያስረዳሉ፡፡ ይህ በበርበሬ ላይ ብቻ የተደነገገው አዋጅ ዋና ምክንያቱን በውል ለማወቅ የሚያዳግት ቢሆንም እንደ እማኝ ዘጋቢው አስተያየት በርበሬው ወደ ትግራይና አዲስ አበባ የሚላክ በመሆኑ በተለይ የትግራይ ነጋዴዎችን በከፍተኛ ሁኔታ ለመጥቀም ታስቦ እንደሆነ ከሚሰጡት ግምቶች የላቀው መሆኑን ያስረዳሉ፡፡ እማኝ ዘጋቢያችን የላኩልን መረጃ እንዲህ ይነበባል፡- “በአማራ ክልል በምዕራብ ጎጃም ዞን በቡሬ በፍኖተ ሰላም በሺንዲ … [Read more...] about የትግራይ ነጋዴዎችን ለመጥቀም አዲስ የበርበሬ አዋጅ በጎጃም
በኦሮሚያ ከተሞች የሚካሄድ ተቃዉሞ ቀጥሏል
ከተጀመረ ወራትን ያስቆጠረውና ከሁለት መቶ በላይ ሰዎች በጭካኔ ለመገደላቸው መረጃ የሚቀርብበት ሕዝባዊ ንቅናቄ አሁንም በተለያዩ የኦሮሚያ ከተሞች ቀጥሎዋል። ኢህአዴግ በአፈቀላጤዎቹ አማካኝነት "ሰልፍ የወጣ የለም፣ ከተማችን ሰላም ነው፣ የተገደለ የለም፣ . . ." በማለት የማስተባበያ ሙከራው በራሱ ሹሞች ሲጨናገፍ በተደጋጋሚ ይስተዋላል። በሌላ በኩል በፌዴራልና በአግአዚ መራር ሰቆቃ እየደረሰበት ያለው ሕዝብ "ባርነት በቃን፣ ግድያው ይቁም፣ የታሰሩት ይፈቱ፣ . . ." የሚሉ መፈክሮችን እያነገበ ሰላማዊ ተቃውሞውን ቀጥሎዋል። የአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ ባለፉት ሦስት ቀናት የተከሰተውን ያቀረበው ዘገባ ከዚህ በታች ይገኛል። ባለፈው ሐምሌ ወር ከአምቦ ወደ አዲስ አበባ ተወስዶ ታስሮ እንደነበርና ታሞ ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ህክምና ላይ ሳለ ህይወቱ እንዳለፈ የተነገረው ተማሪ አብደታ … [Read more...] about በኦሮሚያ ከተሞች የሚካሄድ ተቃዉሞ ቀጥሏል
በልማት ስም የሚካሄዱ እርምጃዎች ይቁሙ
ተቃዋሚው ሕብረት የኢትዮጵያ ፌድራላዊ አንድነት መድረክ፤ በአገሪቱ እየታየ ያለውን ቀውስና ሌሎች ነባር ችግሮች አስመልክቶ አሳስበውኛል፤ ባላቸው ጉዳዮች ዙሪያ በትላንትናው ዕለት ለጠቅላይ ሚንስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ ግልጽ ደብዳቤ ጽፏል። “የሕዝቦቻችንን ጥቅሞች ማዕከል ያላደረጉና ሕዝብን ያላሳተፉ በልማት ስም የሚካሄዱ እርምጃዎች በአስቸኳይ እንዲቆሙና የሃገሪቱ ሕገ መንግስታዊ ድንጋጌዎች እንዲጠበቁ እንጠይቃለን።” መድረክ። መድረክ መፍትሔ ያላቸውን ባለ አምስት ነጥብ ደብዳቤ መነሻነት የድርጅቱ ሊቀ መንበር ከአሜሪካ ድምጽ ጋር ያደረጉትን ቃለ ምልልስ ከዚህ ያድምጡ። … [Read more...] about በልማት ስም የሚካሄዱ እርምጃዎች ይቁሙ
ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የደረሰው ጥቃት
የጎልጉል እማኝ ዘጋቢ (ireporter) የሆኑ በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የደረሰውን ጥቃት ከፎቶ ጋር አያይዘው ልከውልናል፡፡ ዘጋቢው እንዳሉት ከሆነ እዚያው ተማሪ ሲሆኑ የደረሰውን ሁኔታ በዚህ መልኩ ይገልጹታል፡- “ከትላንት ወዲያ (ማክሰኞ) ማታ ካፌ ተማሪዎች ተቃውሞ ሊያሰሙ ሲሞክሩ ፌዴራሎች በዱላ ጀመሩ፤ ከዚያም ዶርም ገባን፤ ሁላችንንም ዶርም እየገቡ በሩን እየሰበሩ እያወጡን አዳሩን ሲደበድቡን አደሩ፤ እስካሁን የሆነ ብሎክ መግባትም አይቻልም፤ የሞተ ሰው አለ እየተባለ ነው፤ እዚያም መግባት አይቻልም፤ ሌላ ብሎክ ደግሞ እሣት ተያይዞ ነበር፤ ማታ እሣት አደጋ መጥቶ አጠፋው … ወዴት እንሂድ? ወደ አገራችን እንዳንሄድ መንገድ ተዘግቷል፤ ኬላ በሙሉ (ተዘግቷል)፤ ወደ ጊቢም እንዴት እንግባ? ያገኙትን ነው የሚቀጠቅጡት፤ … ” በማለት በዚያ የደረሰውን ጥቃት እንድናሰማላቸው ከፎቶዎች ጋር … [Read more...] about ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የደረሰው ጥቃት
“ለድለላ” ሕወሃት ከፍተኛ የጦር አዛዥነት ሹመት ሊስጥ ነው!
ሕወሃት የከፍተኛ መኮንኖች “የመደለያ” ሹመት ለመስጠት ማቀዱ ተሰማ። አባይ ጸሃዬ ለህዝባዊ ተቃውሞው የተሰጠው መልስ የተለሳለሰ ነው አሉ። ህዝባዊ አመጹ ከቁጥጥሩ ውጭ መሆኑን ኢህአዴግ ይፋ አደረገ። ግርፋት፣ ግድያ፣ እስር፣ እንግልትና ስደት ያሳሰባቸው ስጋታቸውን እየገለጹ ነው። የጎልጉል የአዲስ አበባ ዘጋቢ የመከላከያ መረጃ አቀባዮቹን ጠቅሶ እንዳመለከተው፣ በመከላከያ ሠራዊት ውስጥ አለመግባባቱና መቃቃሩ ከሯል። በሠራዊቱ ውስጥ የአንድ ብሔረሰብ አባላት ፈላጭ ቆራጭነት የፈጠረው ልዩነት መባባሱ አሁን ከተቀጣጠለው ህዝባዊ ቁጣ ጋር ህወሃትን አሳስቦታል። አርዶታል። እንደ ዘጋቢያችን ገለጻ ኢትዮጵያን በተገንጣይ ስም እየመራ ያለው የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር (ሕወሃት) አሁን በኦሮሚያ ክልል የተነሳው ህዝባዊ እምቢተኛነት ወደ ሌላ ክልል እንዳይዛመት ሰግቷል። ለዚህም አንዱ የስጋት … [Read more...] about “ለድለላ” ሕወሃት ከፍተኛ የጦር አዛዥነት ሹመት ሊስጥ ነው!
“ኢያዬ ደበርሳ” – ጩኸቴን አስተላልፍ፤ የሚመራው ህዝባዊ ዓመጽ
አሁን በተለይ በኦሮሚያ የተቀጣጠለው ዓመጽ ከጀርባው አቀጣጣይ ኃይላት እንዳሉበት ህወሃት እየሰበከ ነው። “ጥቂት ጸረ ሰላም ሃይሎች” በማለት ብዙ አካላትን እየከሰሰም ነው። የትኛውን ኦነግ ወይም ኦነጎችን እንደሆነ ባይታወቅም እንዲያው በደፈናው “ኦነግ”ን ይከስሳል። አርበኞች ግንቦት ፯ እና አገር ቤት ያሉ ሰላማዊ ተቀናቃኞችም የአመጹ አቀጣጣይ ተደርገው ተፈርጀዋል። በተገንጣይ ስም አገር የሚገዛው የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር ፍረጃውን ለሚያካሂደው ጭፍጨፋ ህጋዊ ሽፋን ሊያውለው ሆን ብሎ የሚያደርገው እንደሆነ ቢታመንም “እመኑኝ” ሲሉ ኦቦ ቃሉ Oboo Qaalluu የሚሉት ሌላ ነው። ኦቦ ቃሉ ከ25 ዓመት በላይ ኦነግን ያገለገሉና አሁን በስደት አውስትራሊያ የሚኖሩ ናቸው። በቅርቡ ውህደቱን ይፋ ያደርጋል ተብሎ የሚገመተው የኦሮሞ ነጻነት ግንባር [ዩናይትድ] አካል ሆነው እየሰሩ ነው። … [Read more...] about “ኢያዬ ደበርሳ” – ጩኸቴን አስተላልፍ፤ የሚመራው ህዝባዊ ዓመጽ
ኦህዴድ ኢህአዴግን ከዳ
በበርካታ የኦሮሚያ ከተሞች የተቀሰቀሰው ሕዝባዊ ንቅናቄ የኦህዴድን መክዳት የሚያሳይ መሆኑ ተጠቆመ፡፡ ከንቅናቄው ጋር በተያያዘ ህወሃት/ኢህአዴግ ጥቅሙን ለማስከበር የትግራይ ወጣቶችን ለ“ብሔራዊ” ውትድርና እየጠራ መሆኑ ተሰማ፡፡ ሳምንታት ያስቆጠረውና የአዲስ አበባ ማስተር ፕላንን ምክንያት በማድረግ የተነሳው ሕዝባዊ እንቅስቃሴ በመጠኑም ሆነ በዓይነቱ ልዩ እየሆነ መሄዱ ኦህዴድ ኢህአዴግን የመክዳቱ ማስረጃ ነው ሲሉ በኦሮሚያ ጉዳዮች ላይ ለጎልጉል መረጃ የሚያቀብሉ አመራር አስታውቀዋል፡፡ በኢህአዴግ የአንድ ለአምስት ጥርነፋ፤ ስለላ፤ ሕዝባዊ አደረጃጀት፤ ቁጥጥር፤ … መዋቅሮችን ሁሉ አልፎ ይህንን ያህል ሕዝብ ያለአንዳች ከልካይ መውጣቱ አገዛዙ ሕዝቡን ለመጠርነፍ የተጠቀመበት አሠራር መልሶ ራሱን እየጠረነፈው እንደሆነ የሚያሳይ ነው፡፡ ታማኝ ተብሎ የተቀመጠው ካድሬም ሆነ የጥርነፋው … [Read more...] about ኦህዴድ ኢህአዴግን ከዳ
“አንከፋፈልም!” የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች
መንግስት ህዝብ ሳያምንበት ማስተር ፕላኑን ተግባራዊ አደርጋለሁ በማለቱ ተቃውሟቸውን ያሰሙት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እንደማይከፋፈሉና በአንድነት እንደሚቆሙ በሰላማዊ ሰልፍ ገለፁ፡፡ ተማሪዎቹ ዛሬ ታህሳስ 8/2008 ዓ.ም ዩኒቨርሲቲው ግቢ ውስጥ ባደረጉት ሰላማዊ ሰልፍ ‹‹ለአንድነት እንቆማለን፣ አማራን እንወዳለን፣ ጉራጌን እንወዳለን፣… አንከፋፈልም…..›› ሲሉ ከሌሎች ጋር ግጭት ውስጥ እንደማይገቡና በአንድነት እንደሚቆሙ አሳውቀዋል፡፡ ከማስተር ፕላኑ ጋር በተያያዘ በተነሳው ሰፊ ተቃውሞ ጭንቀት ውስጥ የገባው መንግስት ተቃውሞው ‹‹የብሄር ግጭት›› እንዳስነሳ በተደጋጋሚ የገለፀ ሲሆን ይህ የመንግስት ክስ ተቃውሞውን ለማኮላሸት የተወጠነ እንደሆነ ሲገለፅ ቆይቷል፡፡ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችም መንግስት ተቃውሞውን ለማኮላሸት ያቀረበው ክስ መሆኑን በመግለፅ ለአንድነት … [Read more...] about “አንከፋፈልም!” የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች
መንገድ ሲዘጋ የኖረው ህወሃት/ኢህአዴግ መንገድ እየተዘጋበት ነው
ላለፉት ሦስት ሳምንታት የኦሮሞ ብሔረሰብ አባላት ተማሪዎች የአዲስ አበባ እና የፊንፊኔ ዙሪያ የኦሮሚያ ልዩ ዞን የተቀናጀ ማስተር ፕላን ተግባራዊ ይደረጋል መባሉን ሲቃወሙ ሰንብተዋል። የተቃውሞውን ጅምር የሚያትተውን የማርታ ፋን ደር ቮልፍ የአዲስ አበባ ዘገባ ጨምራ፤ ጽዮን ግርማ የዛሬዉን የተቃውሞ ሰልፍ ውሎ የተመለከት ርእሶችን ይዛለች፡፡ (የዜና ዘገባው ያሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ ነው) የተቃውሞው መነሻ "ያለ ተገቢ የገንዘብ ክፍያ ገበሬዎችን የሚያፈናቅል የመሬት ቅርምት ነዉ" የሚል መኾኑ ሲዘገብ ቆይቷል። የጸጥታ ኃይሎች ሰልፈኞቹ ላይ በወሰዱት ርምጃ ቢያንስ አምስት ሰዎች እንደተገደሉ መንግሥት አምኗል። የተቃዋሚ ድርጅት መሪዎች በበኩላቸው የተገደለዉ ሰዉ ቁጥር ስልሳ እንደሚደርስ ተናግረዋል፡፡ የጸጥታ አስከባሪዎች ሕይወት ማለፉም ተገልጿል። የኦሮምኛ ቋንቋ ዝግጅት ክፍል … [Read more...] about መንገድ ሲዘጋ የኖረው ህወሃት/ኢህአዴግ መንገድ እየተዘጋበት ነው