• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከእሁድ እስከ እሁድ

January 21, 2013 10:42 am by Editor 2 Comments

በደቡብ ኦሞ የነዳጅ ፍለጋ ጉድጓድ ቁፋሮ ተጀመረ

በደቡብ ኦሞ ጨው ባህር አካባቢ የነዳጅ ፍለጋ ሥራ በማካሄድ ላይ የሚገኘው ታሎው ኦይል የተሰኘው የእንግሊዝ ኩባንያ የመጀመሪያው የሆነውን የፍለጋ ጉድጓድ ቁፋሮ ከትናንት በስቲያ ጀመረ፡፡ ቁፋሮው የተካሄደው በደቡብ ክልል በደቡብ ኦሞ ዞን በዳሰነች ወረዳ ከኦሞራቴ ከተማ 15 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ነው፡፡ የነዳጅ ፍለጋ ቁፋሮ የተጀመረው 18 ወራት የዘለቀ የሴይስሚክ (በመሬት የድምፅ ሞገድ በሚከናወን) ጥናትና 18,000 ኪሎ ሜትር በሸፈነ የአውሮፕላን የግራቪቲ ጥናት ከተከናወነ በኋላ እንደሆነ ኩባንያው ገልጿል፡፡ የአየር ጥናቱ በዓለም ላይ ከተከናወኑት ሰፊ ጥናቶች ውስጥ ይመደባል ተብሏል፡፡ ጥናቶቹ በደቡብ ኦሞ ዞን የመጀመሪያው የነዳጅ ፍለጋ ጉድጓድ የት አካባቢ መቆፈር እንዳለበት ያመላከቱ እንደሆነ ኩባንያው አስታውቋል ሲል የዘገበው ሪፖርተር ነው።

የመጀመሪያው የፍለጋ ጉድጓድ (Wild Cat Well) ሳቢሳ አንድ በመባል የተሰየመ ሲሆን፣ ሳቢሳ ማለት በደቡብ ኦሞ ዞን ጨው ባህር አካባቢ የምትገኝ የወፍ ዝርያ ናት፡፡ የመጀመሪያው የነዳጅ ፍለጋ ጉድጓድ በወፏ ስም ተሰይሟል፡፡

የታሎው ኦይል ኢትዮጵያ ዋና ኃላፊ አቶ ጴጥሮስ አበበ ኩባንያው ካካሄዳቸው የጂኦሎጂ ጥናቶች የተገኙ መረጃዎችን ከተተነተኑ በኋላ፣ ቦታ ተመርጦ ቁፋሮ መጀመሩን ገልጸዋል፡፡ ቁፋሮውን እያከናወነ ያለው ኦጄክ የተሰኘ የፖላንድ ኩባንያ መሆኑን ያስረዱት አቶ ጴጥሮስ “አሁን የተጀመረው የነዳጅ ማፈላለግ ቁፋሮ በደቡብ ኦሞ ዞን ነዳጅ ስለመኖሩ የሚፈትሽ ሲሆን ውጤቱንም በወራት ውስጥ ማወቅ ይቻላል” ብለዋል፡፡ አክለውም በተያዘው የአውሮፓውያን ዓመት ሁለት ተጨማሪ የነዳጅ ጉድጓዶችን በዞኑ ለመቆፈር እንደታቀደ ገልጸዋል፡፡

ታሎው ኦይል የነዳጅ ፍለጋ ሥራውን ሲያከናውን ከማዕድን ሚኒስቴርና ከሌሎች የመንግሥት አካላት እንዲሁም አጋሮች ጋር በቅርበት በመሥራት ላይ እንደሆነ ኩባንያው አስታውቋል፡፡ ታሎው ኦይል መቀመጫው ለንደን የሆነ የግል የነዳጅ ፍለጋና ምርት የሚያከናውን ድርጅት ሲሆን በለንደን፣ በአየርላንድና በጋና ስቶክ ኤክስቼንጅ የተመዘገበ ኩባንያ ነው፡፡

ታሎው በጋና ከፍተኛ መጠን ያለው የነዳጅ ዘይት አግኝቷል፡፡ ከአራት ዓመት በፊት በኡጋንዳ አልበርት ቤዚን ተመሳሳይ መጠን ያለው የነዳጅ ከምችት አግኝቷል፡፡ ባለፈው ዓመት ታሎው በኬንያ ቱርካና ቤዚን የነዳጅ ክምችት ማግኘቱም ሪፖርተር አስታውሷል።

ግብጽእያስፈራራችነው

ካርቱምና ግብጽ ፊርማቸውን ያላኖሩበት የናይል ተፋሰስ አገሮች ስምምነት ዋጋ የሌለው መሆኑን አስታወቀች። የህዳሴ ግድብንም መጎነታተል ጀምራለች። የግብጽ የውሃ ሃብትና መስኖ ሚኒስትር ዶ/ር መሐመድ ባሃራ ከቻይና ዜና ወኪል ዡንዋ ጋር 12/2/2013 ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንዳስታወቁት የናይል ተፋሰስ አገሮች የሚያካሂዱት ማናቸውም ፕሮጀክቶች ግብጽን በአሉታዊ መልኩ የሚነካ ከሆነ አገራቸው ዝም አትልም።

(ፎቶ: saving water)

የግብጽ ውሃ ኮታ መቀነሱን ያስታወቁት ሚኒስትሩ ቻይና ለናይል የላይኛው ተፋሰስ አገሮች ከውሃ ፕሮጀክቶች ጋር በተያያዘ የምትሰጠው ርዳታ ግብጽን የሚጎዳ መሆን እንደሌለበት ማረጋገጥ እንዳለበት አሳስበዋል። የአባይ ተፋሰስ አገሮች ሙሉ በሙሉ በውሃው አጠቃቀም ዙሪያ አዲስ በተረቀቀው ስምምነት ላይ ፊረርማቸውን ያኖሩ ሲሆን ግብጽና ካርቱም አልፈረሙም። ካርቱም ለመፈረም መዘጋጀቷን በይፋ አስታውቃ ነበር።የኢትዮጵያ መንግስት በበኩሉ በአባይ ወንዝ ጉዳይ መጠቀም መብት ለድርድር እንደማይቀርብ፣ አሁን የተጀመረው ፕሮጀክትም ግብጽን እንደማይጎዳ በባለሙያዎች አስጠንቶ ማቅረቡ አይዘነጋም። ከሶስት ወር በኋላ የሚቀርብ የግብጽ ባለሙያዎች የተካተቱበት ጥናት እንደሚኖር መገለጹም የሚታወስ ነው።

ቴዲ ደቡብ አፍሪካ በኢትዮጵያመለያ

ስለፍቅር ሲባል፣ ስለ ጸብ ካወራን ተሳስተናል፤

አንድ ላይ ሆነን ተለያይተናል፤

አተናል እውነት ነው ተቸግረን ብዙ አይተናል፤

የመጣነው መንገድ ያሳዝናል …፤

ቴዲ በሚሰረስሩት ስንኞቹ መድረክ ላይ ሆኖ ያዜማል፤ ይጠበባል። ስንኝ ቋጥሮ ይፈታል። ስሜትን ያምሳል። ልብ ብለው ሲያዳምጡት የህሊናን በር ዘልቀው የሚገቡ ግጥሞቹ ስሜትን ይፈነቅላሉ። “ … አመመኝ፣ አመመኝ፣ ያኔ ገና ውስጤን አመመኝ፣ ውስጤን አመመኝ” ብሎ ልብ የሚያስለቅሰው ቴዲ ከነሙሉ ባንዱ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ቡድን መለያ ለብሶ በደቡብ አፍሪካ ወገኖቹ ፊት “አሃሃ … ወሬ” ሲል ያድናቆት ጩኸት ወርዶለታል።

የሚያደርገውን የሚያውቀው፣ ሙያውን ያላሻቀጠውና ከወቅት ጋር የሚደወረው ቴዲ የኢትዮጵያችን አምባሳደር ሆኖ

አተናል እውነት ነው ተቸግረን ብዙ አይተናል፤

የመጣነው መንገድ ያሳዝናል … እያለ ጥበብ ፈልፍሎ ስሜትን ሲቆላ ባመሸበት መድረክ የታየው ስሜት ኢትዮጵያን ሰው አያሳጣሽ የሚያሰኝ እንደነበር በስፍራው የተገኙ ተናግረዋል። ቴዲ አፍሮ ስለታሪክ፣ ስለ እምነት፣ ስለ እትብት፣ ስለ ምድራችን በሚያትተው ዜማው “ቀስተደመና ነው የለበስኩት ጥበብ የያዝኩት አርማ” እያለ አገርን አጉልቶ አሳይቷል።

ለዋሊያዎቹ “ኢትዮጵያ ቅደሚ”

ሁለት ዓይነት ባንዲራ ለአንድ አገር?

ጠንካራ ብሄራዊ ቡድን እንዳልገነባች የተነገረላት ደቡብ አፍሪካ በደገሰችው 13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ላይ የሚሳተፉት የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን አባላት ተሸልመው፣ ተደራጅተውና ነቅተው “ልማታዊ ተጫዋች ” ተደረገው ሲያበቁ ውድድሩ ከሚካሄድበት አገር ገብተዋል።

ጥር 21 ቀን የመጀመሪያ ጨዋታቸውን የሚያደርጉት ዋሊያዎቹ በደቡብ አፍሪካ በሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ዘንድ ከፍተኛ ድጋፍ ይደረግላቸዋል። ይህም ለጨዋታው ሃይል እንደሚሆን ይገመታል። ከብሄራዊ ቡድኑ መሰረታዊ ተልኮ ውጪ አቶ መለስን ለማስታወስ በሚል ለማከናወን የታሰቡት ጉዳዮች የቡድኑን ስነልቦና እንዳያበላሽው ግን ተፈርቷል።ኢሳት ከደቡብ አፍሪካ በስልክ ያነጋገረቸው ፍርሃቻቸውን በማስጠንቀቂያ አስተላልፈዋል።በደቡብ አፍሪካ ሁለት ብሄራዊ መዝሙር፣ ሁለት ዓይነት ሠንደቅዓላማና ሁለት ዓይነት ደጋፊዎች ለአንድ አገር ብሄራዊ ቡድን በማዘጋጀት ኢትዮጵያ ልዩ ታሪክ ልታስመዘግብ ትችል ይሆናል። ጨዋታውን አስመልክቶ አቶ ሃይለማርያም ደሰለኝ “ማለፋችሁ በራሱ በቂ ነው። የምትችሉትን የኳስ ጥበብ አሳዩና ተመለሱ። ዋንጫ ባንጠላም …” በማለት ከአቅም በላይ ምኞት እንዳይኖር አስቀድመው አሳስበዋል። ኢትዮጵያ በፊፋ ሰንጠረዥ 110ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች።

የከተራ በዓል  ተከበረ፣ ሙስሊሞች ትብብር አደረጉ

በመላው የኦርቶዶክስ ክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ ታላቅ ዋጋና ክብር የሚሰጠው የከተራ በዓል ጥር 11 ቀን 2005 ዓ ም ተከብሯል። ምዕመናን በየአጥቢያቸው በሚገኙና ባመቻቸው አድባራት በመገኘት ታቦት በማጀብ በዝምሬና በሽብሸባ በዓሉን ሲያደምቁ ታይተዋል። የቤተክርስቲያን መሪዎች፣ ዲያቆናት፣ ዘማሪዎችና ካህናት በደብር አልባሳት ተውበው ክብረ በዓሉን አድምቀዋል። የእምነቱ ቤተሰቦች ጎዳና ሞልተው፣ ጎዳና አስውበውና አጊጠው በዕልልታ ታቦት በመሸኘትና መልሶ በማስገባት ስርዓተ አምልኳቸውን አከናውነዋል።

(ፎቶ: Facebook: I Love Wollo)

በመላው አገሪቱ የሚከበረው የጥምቀት በዓል አስመልክቶ ጥር አስራ አንድ ቀን የአሜሪካ ሬዲዮ አማርኛ ፕሮግራም ባስተላለፈው ዘገባ አንድ የሙስሊም እምነት ተከታይ ሴት አቅርቦ ነበር። በእለቱ የሙስሊሞች “የድምጻችን ይሰማ” ጥያቄ አንደኛ ዓመት የሚታሰብበት ቀን ቢሆንም ለክርስቲያን ወንድምና እህቶች ሲሉ ታላቁን የአንዋር መስጊድ አለመጠቀማቸውን እንግዳዋ ይፋ አድርጋለች። ይህንን ያደረጉት ከአንዋር መስጊድ ጎን ካለው ራጉኤል ቤተክርስቲያን ታቦት ሲወጣ ችግር እንዲፈጠር የታሰበውን ተንኮል ለማምከንና በስፍራው ትርምስ እንዳይፈጠር ለመላው ሙስሊሞች በተላለፈ መልዕክት ምክንያት ነው። እንዲህ ያለው የኖረ መከባበር በርካቶችን አስደስቷል።

“ለ3ኛ ጊዜ ጥምቀትን ተከትሎ የሚካሄደው የኢትዮጵያን በጎንደር የባህል ፌስቲቫል ቀዝቀዝ ባለሁኔታ መከበሩን ዘጋቢያችን ከስፍራው ገልጿል” በማለት ኢሣት ዘግቧል፡፡ “በሲምፖዚየሙ ላይ አቶ በረከት ስምኦን ፤የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትሩ አቶ አሚን አብዱልቃድር፣ የስነምግባርና ጸረሙስና ኮሚሽነሩ አቶ ዓሊ ሱሌይማን እና ሌሎች ከፍተኛ ባለስልጣናት መገኘታቸው” ኢሣት ጨምሮ አስታውቋል፡፡

ኑሮ እንደተሰቀለ ነው፤ ግሽበት 12.9 በመቶ ደረሰ ተባለ

ባለፈው ታህሳስ ወር የነበረው የዋጋ ግሽበት ባለፈው አመት ከነበረው 35.9 በመቶ ወደ 12.9 በመቶ መውረዱን ፥ የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር የኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሀጂ ኢብሳ ተናግረዋል። የዋጋ ግሽበትን ለመቆጣጠር በገንዘብ አቅርቦቱ ላይ ጥብቅ ቁጥጥር መደረጉ፣ የበጀት ጉድለት አነስተኛ እንዲሆንና ጉድለቱም ከብሄራዊ ባንክ በሚገኝ ብድር ሳይሆን በኢኮኖሚ ወስጥ ከሚንቀሳቀሰው ገንዘብ በመሸፈኑ ለዋጋ ንረቱ መቀነስ እንደ ምክንያትነት ተጠቅሷል።

ቀደም ሲል ወደ ሀገር ውስጥ የገባ 8 ሚሊዮን ኩንታል ስንዴ ፣ 2.5 ሚሊዮን ኩንታል ስኳርና 25 ሺህ ቶን ዘይት ለህብረተሰቡ እንዲቀርብና ገበያ እንዲረጋጋ ማስቻሉን፣ 15ሺ ሊትር ዘይትና 2 ሚሊዮን ኩንታል ስንዴ በመጋዝን ላይ እንደሚገኝ፣ እንዲሁም በያዝነው ወር መጨረሻም 4 ሚሊዮን ኩንታል ስንዴና 252 ሺህ ኩንታል ስኳር ሀገር ውስጥ በማስገባት በቀጣይ እንደሚፋፈል ዳይሬክተሩ ተናግረዋል። በመንግስት በኩል ይህ መግለጫ ቢሰጥም ኑሮው ባለበት እንደተሰቀለና ህዝብ በኑሮው ያገኘው ለውጥ እንደሌለ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እየተናገሩ ነው። አንዳንዶች አቅርቦቱ መሻሻሉን አሁን ከሚካሄደው የአካባቢ ምርጫ ጋር አያይዘውታል። (ዘገባው የተወሰደው ከፋና ብሮድካስቲንግ የጥር 10 ፣ 2005 ዜና ላይ ነው።)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. emamudin akmel says

    January 21, 2013 12:21 pm at 12:21 pm

    we found arealy good information in your site,,,thank’s 4 your info.

    Reply
  2. koster says

    January 21, 2013 07:01 pm at 7:01 pm

    What is going on in Ethiopia is not development but looting as was the case in JELZIN Russia. Woyane ethnic fascists and their collaborators are enriching themselves by looting and 10 or 20% inflation is not their problem. It is the poor Ethiopians who are languishing under woyane ethnic fascists looting and terrorizing.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule