• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሚፈራው መጣ!!

August 5, 2013 09:14 am by Editor 3 Comments

ኢትዮጵያችን ታማለች። ኢትዮጵያችን ተወጣጥራለች። ኢትዮጵያችን በአደገኛ መርዝ ተበክላለች። ኢትዮጵያችን ውስጧ ነፍሯል። ኢትዮጵያችን እየቃተተች ነው። ቆዳዋ ሳስቷል። የሚሰማትና የሚደርስላት ስላጣች የያዘችውን ይዛ ልትነጉድ ከጫፍ ላይ ነች። እናም ቅድሚያ ለመቀመጫ፤ ቅድሚያ ለእምዬ ኢትዮጵያ!! ማጣፊያው ሳያጥር ሁሉም መንገዱን ይመርምር!!

ኢትዮጵያ በጭንቀት ጣር ውስጥ ስለመገኘቷ ማብራሪያ የሚጠይቁ ዜጎች ያሉ አይመስለንም። ምናልባት ሳያውቁ እየተፈረደባቸው ያሉ ህጻናት ካልሆኑ በስተቀር፤ ችግር ፈጣሪውም፣ የችግሩ ሁሉ ሰላባ የሆነው ህዝብ፤ ሁሉም ከበቂ በላይ መረጃ አላቸው። ኢትዮጵያ ህመሟ ወደ “ሚድን ካንሰርነት” መቀየር የሚችል ስለመሆኑ ዜጎች ያለ “ሰበር ዜና” ይረዱታል።

የሚድን ስንል በቀላል አገላለጽ ችግር ፈጣሪው ኢህአዴግ፣ የኢህአዴግ ሾፌር ህወሃት፣ የህወሃት አገልጋዮች፣ በህወሃት የበላይነት ከበሮ የሚደልቁ ወንድምና እህቶች፣ ጊዜ የሚያረጅና እራፊ ሆኖ የሚያልፍ የማይመስላቸው የትዕቢት ውጤቶች፣ ይህንን ሁሉ ታግለን “ዴሞክራሲ እናወርዳለን” የሚሉ ወገኖች በልዩነት “አንድ” በመሆን ኢትዮጵያን ለህዝብ ውሳኔ አሳልፈው መስጠት ሲችሉ ነው።

“የጦርነት አባቱ እኔ ነኝ፣ እኔ ከሌለሁ አገር ትከስማለች፣ ኢትዮጵያ በደም ትታጠባለች፣ እኔ ወደ ሰሜን እሸሻለሁ … ” እያለ የቀን ቅዠት ቃዥቶ እወክላቸዋለሁ የሚላቸውን ወገኖች በስጋት ጤና እየነሳ ያለው ኢህአዴግ፣ በተለይም ህወሃት ቀን በጨመረ ቁጥር በእሳት እየተጫወተ ነውና የራሱ ደጋፊዎች ወደ ሰላም መንገድ እንዲመጣ ሊያስገድዱት ይገባል።

የተናፈናቀሉ፣ ከስራ የተባረሩ፣ በቂም ከነቤተሰቦቻቸው ለልመና የታደረጉ፣ ቤተሰቦቻቸው የታሰሩባቸው፣ የተገደሉባቸው፣ በዘራቸው ሳቢያ የመከራ አረም እንዲመገቡ የተደረጉ፣ የተዘረፉና እየተዘረፉ ያሉ ዜጎች፣ በብሄር እየተተመኑ ከተወዳዳሪነት የተገለሉ ኢትዮጵያዊያኖች፣ እምነታችን ተነካብን የሚሉ የኢትዮጵያ ቤተሰቦች … ብዙ ማለት ይቻላል፤ ሁሉም አምርረዋል። ቁጣቸው ከጫፍ ደርሷል። ደጋግመን እንደምንለው ዛሬ ጊዜው የእርቅና ሰላም የማውረድ በመሆኑ ለሚሰሙ ወገኖች “ቅድሚያ ለእምዬ ኢትዮጵያ” የሚል አደራ እናስተላልፋለን። በተለይ በ1997 የምርጫ ወቅት ኢትዮጵያን ወደተሻለ ቦታ ሊያደርሳት የሚችለውን ወርቃማ ዕድል ከእጁ እንዲያፈተልክ ያደረገው ኢህአዴግ አሁንም ይህንን ወቅት ጊዜው ሳያልፍና ሁኔታዎች ወደነበሩበት የማይመለሱበት ደረጃ ከመድረሳቸው በፊት ሊጠቀምበት ይገባል፡፡ አገር ካለፈች በኋላ ልማት፣ ህዳሴ፣ ውዳሴ፣ ግድብ፣ … አንዳቸውም አይኖሩም!

አንድ ዓመት ያስቆጠረው የሙስሊሞች ጥያቄ በወጉ ካልተያዘ መከራው እንደሚሰፋ አስቀድመን ለፍልፈናል። ከቀን ወደ ቀን እየገፋ የሄደው ተቃውሞ በወጉ ተመርምሮ እናታችን ኢትዮጵያን ለአደጋ በማይጥል መልኩ እልባት እንዲሰጠው አሁንም ደግምን ደጋግመን እናሳስባለን። በግርግር ሳይሆን በማስተዋል “ቅድመ ሁኔታ” ያስቀመጠ የሰላም መንገድ እንዲፈለግ ያገባናል የሚሉ ሁሉ ተግባራዊ እንቅስቃሴ እንዲጀምሩ በቀጣዩ ትውልድ ስም እንጠይቃለን። የ“ድምጻችን ይሰማ” ጥያቄ ድምጽ የማሰማትና የመብት ጥያቄ እስከሆነ በአግባቡ ይመለስ፡፡ ከዚህ ሌላ ጥያቄ ካላቸው ለህዝብ ይፋ ያድርጉ፡፡ የሙስሊሙ ኅብረተሰብ ከኢህአዴግ ጋር ላለፉት ሁለት አሥርተ ዓመታት ሰላማዊ ግንኙነት እንደነበረው ግልጽ ነው – ባለፉት ሥርዓቶች ባልታየ መልኩ በተለያዩ ከተሞች የበርካታ መስጊዶች መሠራትም ሆነ የአምልኮ ሥርዓታቸው መከበር ተጠቃሾች ናቸው፡፡ ታዲያ አሁን የሃይማኖትና የመብት ይከበር ጥያቄያቸው የሥልጣንና ፖለቲካዊ ይዘት ያለው መስሎ ለምን ቀረበ? እስካሁንስ ለምን መፍትሔ ሊገኝለት አልችል አለ?

የሚፈሩና የሚከበሩ የፖለቲካ መሪዎች የሉንም። የምንወዳቸውና ሲናገሩ የምናዳምጣቸው የሃይማኖት መሪዎች ባለቤት መሆን አልቻልንም። ለተግሳጽ አደባባይ የሚወጣ ሽማግሌ የለንም። ከውጪም ከውስጥም  መተማመን ጠፍቷል። የክስረታችን ብዛት ባዶ አስቀርቶናል። የቀረን አንድ ነገር ቢኖር እማማችን ኢትዮጵያ፣ እያቃተተች ያለችው አገራችን ናት። ይህችኑ ቤታችንን ተረባርበን ማዳን ካልቻልን ሁሉም ያከትምና ላናገግም እናዝናለን። በርካታ ንጹሃንን እናጣለን!! እባክችሁ የህወሃት ሰዎች ሁሉንም ጎን እዩት። ወደ ልባችሁ በመመለስ የእርቅን መንገድ ፈልጉ። በውል እንደምትረዱት ነገሮች ሁሉ መልካቸውን የሚቀይሩበት ወቅት ተቃርቧል። እባካችሁን የኢህአዴግ ሰዎች ያለፍርሃቻ እርቅ በቤታችሁ እንዲታወጅ መስዋዕት ሁኑ። ዝምታችሁን ቅበሩና ኢትዮጵያንና ወገኖቻችሁን፣ ልጆቻችሁን፣ ቤተሰቦቻችሁን አድኑ። የህዝብን ጥያቄ መልሱ!

በወጪ አገርም ሆነ በአገር ቤት የምትኖሩ የእርቅ ሃሳብ ባሪያዎች፣ ኢትዮጵያን ለመታደግ የምትፈልጉ ወገኖች ኢትዮጵያ ላይ ከየአቅጣጫው የተረጨውን የጥላቻ መርዝ ለመግፈፍ ተነሱ። ኢትዮጵያን ለማዳን ይሉኝታና ማመንታት ዋጋ የላቸውምና ከተጋረዳችሁበት መጋረጃ ውጡ። የሃይማኖት አባቶች እባካችሁን ንስሃ በመግባትና ህዝቡንም ንስሃ በማስገባት የሰላም አባት ሁኑ። ቀሪ ዘመናችሁን በደስታ ሰክራችሁ ትኖሩ ዘንድ ያጎደፋችሁትን ስማችሁን አድሱ። አገር ከሌለ መብትም ሆነ ዴሞክራሲ፣ ነጻነት አይኖሩም፡፡ አገር ከሌለ ድምጽ አሰሚም ሆነ ድምጽ ሰሚ የለም፡፡ አገር ከሌለ ልማትና ብልጽግና አለመኖር ብቻ ሳይሆን ተደረገ የተባለውም ወዳለመኖር ይቀየራል፤ አገር ከሌለ ማንነት ይቀራል፤ ይህንን ማስጠንቀቅና የዕርቅ ሃሳብ ማቅረብ ዕልቂት ናፋቂነት አይደለም።

ልብ ያለው ያስተውል! ጆሮ ያለው ይስማ! ኢትዮጵያ እየቃተተች ነው። ማጣፊያው ሳያጥር ቅድሚያ ለእምዬ ኢትዮጵያ!!


ይህ ርዕሰ አንቀጽ የ“ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®” አቋም ነው፡፡ (ፎቶ ከፌስቡክ የተገኘ)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Editorial Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. አስቴር says

    August 5, 2013 09:20 pm at 9:20 pm

    ርዕሰ አንቀጻችሁን ወድጃለሁ። ይህንኑ የመሰለ አበራ ልኮልኛል። እዚህ ላይ ተጫኑ። በርቱ።
    http://www.ethiopianchurch.org/editorial2/174-%E1%89%A3%E1%8B%AD%E1%8A%95-%E1%8B%A8%E1%8C%88%E1%89%A3-%E1%8B%90%E1%8B%AD%E1%8A%95-%E1%8A%A0%E1%8B%88%E1%8C%A3.html

    Reply
  2. Mesfin says

    August 15, 2013 06:58 pm at 6:58 pm

    I have the premonition such disaster will happen to Ethiopia and its people. However, most of us have not yet wake up and foresee the danger. You have tried to show to everybody of what kind of disaster is looming towards Ethiopia and Ethiopians. As you have said it if we do not react soon we will perish.

    Reply
  3. abraham says

    January 3, 2014 03:15 pm at 3:15 pm

    ኢትዮጵያ አንተ እንደምትመኝዉ ሳይሆን ከደርግ ሰዉ በላዉ ስርአት ወጥታ ለእድገት የምትራወጥበት ጊዜ ነዉ ያለችዉ ምናልባት ጥያቄህ የስልጣን ከሆነ ካንተዉ ጋር ነኝ ግልጹን ከመናገር ይልቅ እንደ አንድ እዉነታ የሌለዉ ዋሾ መቀባጠር ትርፉ ከትዝብት አያልፍም
    ኢትዮጵያን የሚወድ ሁሉ ለሃገሪቱ ጥቂትም ቢሆን ያበረከተ ሊመሰገን ይገባል አለዚያ በዚህ ባለንበት የዉሸት ዘመን ፎልት ፋይንደር መሆን አገሪቷን ተጠቃሚ ከማድረግ ይልቅ ለጉዳት መዳረግ ነዉ ኢትዮጵያ ስሟ እየተለወጠና ባላት አቅም እያደገች ነዉ ሆኖም ምን ያደርጋል ኢሃዴግ ሆነ እንጂ የሚለዉንስ ምን ትለዋለህ አገር በዚህ መልኩ ከድህነት ትወጣለች ብሎ መጠበቅ አይቻልም

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule