• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አዜብ መስፍን ፈርተዋል!!

October 11, 2012 08:16 am by Editor 6 Comments

መለስ የሚያቆላምጧቸው ወ/ሮ አዜብ ለመቀማጠልና ለደኅንነታቸው በመስጋት ቤተመንግሥቱን “አልለቅም” ማለታቸውን የጎልጉል ምንጮች አረጋገጡ። የአዲስ አበባ መረጃ አቀባዮቻችን እንደሚሉት ከሆነ የቀድሞዋ “ቀዳማዊት እመቤት” ሶስት ቪላዎች እንዲያማርጡ ቢለመኑም አሻፈረኝ በማለት ባነሱት የደኅንነት ጥያቄ ገፍተውበታል።

ከህወሓት መከፈል በኋላ አቶ መለስ ህወሓትን በመዳፋቸው ውስጥ ሙሉ በሙሉ መቆጣጠራቸውን ተከትሎ ገንነው የወጡት ወ/ሮ አዜብ የተባረሩት፣ የተባረሩት ደጋፊዎችና የህወሓት ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ ኢህአዴግ ውስጥ ጥርስ የነከሱባቸው ይበረክታሉ። የሥልጣን እርከን በመጣስ ከሚያደርጉት ጣልቃ ገብነት በተጨማሪ ለሚያካሂዱት የንግድ ስራ ሲሉ መመሪያ በመስጠት፣ የማይፈልጉትንና አልታዘዝ የሚሉዋቸውን ባለሥልጣናት በማስገደድ፣ በተለይም ተወላጅ ሳይሆኑ በህወሓት አመራሮች ላይ ሲያሳዩ የነበረው የበላይነት ዛሬ አደጋ እንዳመጣባቸው የዜናው ምንጮች ይናገራሉ።

የመለስን በጠና መታመምና ይፋ ያልተገለጸ ሞት ተከትሎ፣ ከዚያም “የውድ ባለቤታቸው” ህልፈት ይፋ በሆነ ማግስት፣ ብዙ የተወራባቸው ወ/ሮ አዜብ፣ ባለቤታቸውን “ሲሰናበቱ” የባለቤታቸውን የፖለቲካ አቅጣጫ “ውርስ” የማይበረዝ ከሆነ እንደሚገፉበት የተጠቆሙበትን ቃል አቶ ሃይለማርያም በቀጥታ ቃል በቃል መድገማቸው ወ/ሮ አዜብን “አሁንም የሚደፍር የለም” የሚል አስተያየት እንዲሰነዘር አድርጎ ነበር።

በወቅቱ አንደ አንድ ጉሊት ቸርቻሪ፣ ችግር እንደ ገረፋት ቅጠል ሻጭ እናት “ልጆቼን በማሳደግ እፈተናለሁ” በማለት ሲናገሩ መሳለቂያ የሆኑት ወ/ሮ አዜብ ኢህአዴግ ውስጥ እየጋመ ያለው የውስጥ ለውስጥ ኃይል የማሰባሰብ ሩጫ “ደመራው” ወደ የትኛው ወገን እንዳዘነበለ ባልታወቀበት ሁኔታ ተወጥረው ተይዘዋል።

ለጠ/ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ቅርበት ያላቸው ክፍሎች እንደሚሉት ወ/ሮ አዜብ የኃይል ሚዛኑን በበላይነት ከያዙት ክፍሎች ጋር ቢመደቡም በእርሳቸው ጎትጓችነት፣ በባለሃብቶች ጠቋሚነት የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ሃላፊ የሆኑት አቶ ሙክታር ከድር ከኦህዴድ ግምገማ ተርፈው ለወዳጃቸው የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ መላካቸው ታውቋል።

በአቶ ሙክታር ፊርማ ቤተ መንግስት ለቀው እንዲወጡ አንድ ሳምንት የተሰጣቸው ወ/ሮ አዜብ፤ አቶ መለስ በህይወት እያሉ ለተሰናባች ጠ/ሚኒስትር ባስገነቡት የሚኒሊክ ቤተ መንግስት ውስጥ በሚገኝ ቪላ ለመኖር ያቀረቡት ጥያቄ ወደ ጎን ተብሏል። የጎልጉል ዘጋቢ ባገኘው መረጃ መሰረት ወ/ሮ አዜብ ለጊዜው አድራሻው በግልጽ ያልታወቀ ትልቅ ግቢ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል። ሌላ ምንጭ ደግሞ ወ/ሮ አዜብ የሚከራከሩት በታችኛው ቤተ መንግስት (ኢዮቤልዩ) ከፕሬዚዳንት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ ጎን ተጎራብተው ለመኖር እንደሆነ ጠቁመዋል። ሁሉም መረጃዎች እንደሚያስረዱት ወ/ሮ አዜብ ያቀረቡት ጥያቄ ተቀባይነት አለማግኘቱን ነው።

የቀረቡላቸውን ሶስት ቪላዎች “ለደህንነቴ አይመቹም፤ ለፕሮቶኮሌ አይመጥኑም፤ ሰው ይበዛባቸዋል” በሚል ምክንያት ባለመቀበል ወ/ሮ አዜብ ቤተ መንግስቱን የሙጥኝ በማለታቸው ምክንያት አዲሱ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ማለዳ ብስራተ ገብርኤል ከሚገኘው ቤታቸው ሲወጡ፣ ምሽት ላይ ደግሞ ተመልሰው ወደ ቤታቸው ሲገቡ በተፈጠረው የትራፊክ መጨናነቅ ነዋሪዎች መጨናነቃቸውን ሰንደቅ ጽፏል። እርሳቸው ባይፈልጉትም ለደህንነታቸው ሲባል በሚደረገው ጥብቅ ጥበቃ የአካባቢው ሰዎች እንደ ልብ መውጣት መግባት ተስኗቸዋል። ጋዜጣው ወ/ሮ አዜብ ማስጠንቀቂያ እንደተሰጣቸው ማስነበቡ በአቶ በረከትና በወ/ሮዋ መካከል የተፈጠረ ችግር ሊኖር እንደሚችል አመላካች እንደሚሆን፣ አሊያም አቶ በረከት ተቀናቃኞቻቸውን ለማግባባት ወ/ሮ አዜብን የመክዳት እርምጃቸውን ለማሳየት የተጠቀሙበት ሊሆን እንደሚችል አስተያየት ተሰንዝሯል።

ወ/ሮ አዜብ በሚኒስትሮች ደረጃ የሚሰጥ ቤት ቀርቦላቸው እንዲያማርጡ መጠየቃቸውን የጠቆሙት ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ክፍሎች አቶ ሃይለማርያምን “ልፍስፍስ” ይሏቸዋል። አያይዘውም ክብራቸውን ማስጠበቅና ስልጣናቸውን ባግባቡ መገልገል አለመቻላቸው ወደፊት ሊጎዳቸው እንደሚችል በመጠቆም በተለይ ከተለያዩ አቅጣጫዎች ጠንካራ የተሐድሶ ዕርምጃ እንዲወስዱ የሚቀርቡላቸውን መጠነሰፊ ጥያቄዎች የማስፈጸማቸውን ጉዳይ አነጋጋሪ አድርጎታል፡፡

ሟቹ ጠቅላይ ሚኒስትር “ካንደበቷ ትንታግ ይወጣል” በሚል አድናቆትን የሚቸሯቸው ወ/ሮ አዜብ ከደኅንነት ስጋት ጋር በተያያዘ ያነሱት ጥያቄ የተለያየ አስተያየት ቢያስከትልም እስከ ሳምንቱ መጨረሻ ማረፊያቸው እንደሚታወቅ የጎልጉል ምንጮች ጠቁመዋል። አያይዘውም ከሜጋ ማተሚያ ድርጅት ስልጣናቸው ሲነሱ አኩርፈው አረብ አገር ሄደው በአንድ ታዋቂ ባለሃብት ሽምግልና ተመልሰው ሃላፊነታቸውን ተረክበው የነበሩት ወ/ሮ አዜብ ጉሸማው ከበዛባቸው በዚሁ በቀድሞው ሽማግሌያቸው አማካይነት ሃብት ተቆርሶላቸው ህወሓትን “ደህና ሰንብት” ሊሉት እንደሚችሉም ግምት እንዳላቸው ተናግረዋል።

ወ/ሮ አዜብ በትውልድ ቀዬያቸው ነዋሪዎችና አባቶች ክፉኛ የሚወነጀሉና የተወለዱበትን የአማራ ክልል የከዱ እንደሆኑ በመግለጽ የሚቃወሟቸው ጥቂት አይደሉም። የተወለዱበትና እትብታቸው የተቀበረበት ምድር ተቆርሶ ሲወሰድ ዝምታን የመረጡ የዘመኑ “ዮዲት ጉዲት” የሚሉዋቸውም ቁጥራቸው ቀላል አይደለም። በሁሉም ጎን የተወጠሩትና “ስኳር” ይወዳሉ የሚባሉት ወ/ሮ አዜብ ያላቸው አማራጭ አቶ መለስ ከተወዳጇቸው የእስያ አገሮች ወይም ቀደም ሲል ወዳኮረፉበት አረብ አገር የመዛወራቸው ጉዳይ ሚዛን የደፋ ሆኗል። ወዳጆቻቸው ለ“ለባለ ራዕዩ መሪ” ሲሉ አምባሳደር አድርገው ከሾሙዋቸው የሁሉም ትንቢት ፉርሽ ይሆናል። ሁሉም እንደሚስማሙበት ግን ወ/ሮ አዜብ አገር ቤት አይመቻቸውም። እርሳቸውም አውቀውታል – ከቤተ መንግስት ውጪ!!

ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ ለሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Yeshitela says

    October 11, 2012 12:11 pm at 12:11 pm

    I highly appreciate your profesionalism. The news you present keeps us abreast with what is happening in Ethiopia and elsewhere in the world. Thank you and keep on your good work.

    Reply
  2. Ta says

    October 11, 2012 02:35 pm at 2:35 pm

    Good observation, good report. As I see from the news, she may not have power to stay there. But here duties in those days lead her to fear the people whom suffered a lot. Even though, she will have guards around her, how could she live such a simple life like most of us? u see . even she have an opportunity to live in a standardized vila which can be opt to very few people in the country but she didn’t willing to move. If she be in the street of Addis Abeba for an hour, she will see the suffering and inaccessibility of infrastructure for the people as large.

    Concerning PM, I think it not fair to say “ልፍስፍስ”. He might not engaged himself in asking to remove Azeb from the palace and he transferred there. The people around him knows very well and many other people with security and protocol can arrange the issue. In fact, his behavior and religious stand leads him to be reserved in situations. But I advice him to be aggressive and decisive in serious matter regarding national interest and sensitive issues like change of the old dogma of woyanne. Since most of the old system are going to leave the office in 2015, I wish to see a change of system rather than those old people. He must do in this regards strongly.

    Reply
  3. koster says

    October 11, 2012 06:55 pm at 6:55 pm

    Fascist Yodit have every reason to be terrorized because she has been terroizing the Ethiopian people when her fascist husband Meles Zenawi was in power. How can she meet the inhabitants of Wolqait and millions who are languishing under fascist woyane reign of terror.
    She better move to Florida like the other looter who was assistant head of EFFORT – a holding company which constists more than 80 fascist woyane looting enterprises.

    Reply
  4. beniam abera says

    October 13, 2012 04:17 am at 4:17 am

    it was so not good we lose our pry minister it was so sad and I want say some thing
    for his family I’m rely fill sorry for your family and god blase your family!!!

    Reply
    • ,.mm,.m,. says

      October 28, 2012 07:47 pm at 7:47 pm

      U dude , first of all try to learn how spell properly . Koda ke felek erasihin kiber

      Reply
  5. anonymous says

    October 21, 2012 11:54 pm at 11:54 pm

    Simple question to Azeb …..where does your fear of people of Ethiopia comes from.I think your mind is telling you about your evil-deeds of the past.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule