አሁን ላይ ጃዋር የፖለቲካ ምሕዋሩን ስቶ የሚሄድበትን መንገድ የማያውቅ ሆኗል። በዚህ ኪሣራ ውስጥ ተስፋ ሰጪ ሆኖ ያገኘው የሥራ ማቆም አድማ መጥራት ነው። እስካሁን ያልተሳኩ የሥራ ማቆም አድማዎችን ጠርቷል፤ በሌሎችም ባልተጋበዘባቸው ጥሪዎችም ድንኳን ሰብሮ በመግባት ደጋሾቹን ድግሱን አምክኖባቸዋል። ግን አላረፈም፤ አሁንም ሌላ ጥሪ አድርጓል፤ ይኼኛውን ግን እሱ የሌለበት ለማስመሰል ምሥጢራዊ ለማድረግ እየሞከረ ነው። ልደቱ አያሌው የሽግግር መንግሥት የዘርፉ ባለሙያ በመሆን የክብር ዶክትሬት እንዲሰጠው ተግቶ እየሠራ እንዳለው ጃዋርም በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ብቸኛው የዘርፉ ባለሙያ እየሆነ መጥቷል። አዲስ ሪፖርተር፤ ጃዋር [“ከመምህራን ማሕበር ጋር በታህሳስ ወር አመጽ ለማስነሳት ተስማምተናል” ማለቱን ማሕበሩ ነቀፈ፤] በሚል ርዕስ ያወጣው የዜና ዘገባ ይህንኑ የሚጠቁም ነው። … [Read more...] about በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ
የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ
* "እኛ የገባነው ልናፈርሰው ነው" ሕዝቅኤል ገቢሣ በሰላማዊ ትግል መንግሥት ለመጣል ማቀዱን አስታውቆ ሃያ አንድ ቦርድ አባላትን ሰይሞ የሰነበተው የ-አብሮነት ማኅበር ሰባት ሥራ አስፈጻሚዎችን መምረጡ ታወቀ። ማኅበሩ “ለቦርድ አባላት” በሚል ባሰራጨው የ“እንኳን ደስ አላችሁ” መልዕክት አቶ ልደቱ፣ ከአማራ የማኅበሩ ፕሬዚዳንትና ሊቀመንበር ሆነዋል። መቅደስ አዳነ ከወላይታ (ምክትል)፣ አሸናፊ አብርሃም ከደቡብ (ጸሐፊ)፣ ሙሉጌታ ዘለቀ ከአማራ (ገንዘብ ያዥ)፣ የሕዝብ ግንኙነት ኦፊሰር ሕዝቅኤል ገቢሣ /በተለይ እንግሊዘኛና ትግርኛ ጠንቀቀው ስለሚያውቁ/ ከኦሮሞ፣ የድርጅት አስተባባሪ እስማኤል ጎርሴ ከሶማሌ፣ የውጭ ግንኙነት ኦፊሰር መስፍን አየነው ከትግራይ መመረጣቸው ይፋ አድርጓል። ቀደም ሲል ምርጫው ከመደረጉ በፊት የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴው አባላቶች ሕቡዕ እንደሚሆኑ … [Read more...] about የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ
“የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል
ሼትል ትሮንቮል “መንግሥቱ ኃይለማሪያም ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በስደት ክሚኖሩበት ሀራሬ ደወሉለት፣ ሰላም ጓድ አንተም እንደ እኔ በወያኔ ተቸግረሃል፣ እባክህን እኔ እንዳደረኩት ወደ ሃራሬ እንዳትሰደድ ምክንያቱም ወያኔዎቹ አንተን ፍለጋ ሃራሬ ሲመጡ እኔንም ይውስዱኛል” በማለት ዝነኛ ጆክ ትዊት አድረገው የነበሩ ሰው ናቸው። አዲስ ሪፖርተር – የኖርዌይ ፕሮፌሰር ሼትል ትሮንቮል “ነጩ ወያኔ” በሚል ስያሜ ይጠራሉ። የትህነግ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ያህል በትህነግ ጉዳይ ወሳኝ ሰው ነበሩ። ዛሬም ድረስ አፍቃሪ ትህነግነታቸው ባይቀየርም የመከፋፈሉ ወጀብ እርሳቸውንም የናጣቸው ይመስላል። በትግራይ የተካሄደውን ምርጫ መቀሌ ተገኝተው “ሕጋዊ ነው” በማለት ያጸደቁና የተሟገቱ ናቸው። በተለይም በኅልውናው ጦርነት ወቅት ለትግራይ ታጣቂ ኃይሎች TDF የሚል የወል ስም ማውጣታቸውን … [Read more...] about “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል
አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው
አምስተርዳም ይካሄዳል ተብሎ በውጭ አገር በሚኖሩ በተለያዩ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች የተሰራጨው የሽግግር መንግሥት ምስረታ ጉባኤ ከአሜሪካ ወደ አምስተርዳም ያመራው አሜሪካ ጥያቄውን ባለመቀበሏ መሆኑ ተሰማ። ስብሰባው ከጀርባው ሆነው የሚመሩትና ሻዕቢያና ሌሎች ፍላጎት ያላቸው የሚታወቁ አካላት እንደሆኑም እየተነገረ ነው። የቀድሞ የትህነግ አመራርና አሁን ላይ “ቪዥን ኢትዮጵያ” ከሚባለው አደረጃጀት ጋር እየሠሩ ያሉት አቶ ግደይ ዘርዓጽዮን በግል የኢሜል አድራሻቸው “ለስብሰባው ተዘጋጁበት” ሲሉ ያሰራጩት ሰነድ ጉባዔው ለምን ወደ አምስተርዳም እንደተዛወረ፣ ወይም አምስተርዳም ለምን እንደተመረጠች አያስረዳም። ይህንኑ አስመልክተን ተጋባዥ ከሆኑት መካከል የአዲስ ሪፖርተር የዋሽንግቶን ተባባሪ ያነጋገራቸው “ቅድሚያ ዕቅዱ ስብሰባውን በአሜሪካ ለማድረግ ነበር፤ ምላሹ ጥሩ ባለመሆኑ ወደ … [Read more...] about አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው
በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ
* “ዳህላክ ነው ቤቴ”፤ “ደሞ በዓባይ (ድርድር) ከሞከሩንማ” ኢትዮጵያ ላይ ተረባርበው የነበሩ፣ ኢትዮጵያ ላይ ፍትሕ በማዛባት ዘምተው የነበሩ፣ ኢትዮጵያን ማሳጣት የዕለት ተዕለት ተግባራቸው የሆነ ወዘተ ሚዲያ አውታሮች “ኢትዮጵያ ኑክሊየር ታጠቀች” በማለት ለታላቁ የዓባይ ግድብ አድናቆታቸውን ቸረዋል። በጨለማ ውስጥ ለሚኖሩ ብርሃን ያዩ ዘንድ ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያ በራሷ ልጆችና ኪስ ይህን “ክስተት" የተባለ ፕሮጀክት ስታስመርቅ የተሰማው ታሪክ በዜጎች ዘንድ ሁሉ ከዳር እስከዳር ልዩ ስሜትን ዘርቷል። አስራ አምስት ሺህ ዜጎች የጠላት ተልዕኮ በተቀበሉ ቅጥረኞች ወጥመድ ማለቃቸው ግድቡ በኢትዮጵያዊያን፣ ጉልበት፣ ገንዘብና ዕውቀት ብቻ ሳይሆን አጥንትና ደም ጭምር የተገነባ፣ የታተመ የኢትዮጵያዊያን ሁሉ ማኅተባቸው እንደሆነ እዚያው ሥፍራው ላይ ሆነው ሁሉንም ያዩና የታዘቡ … [Read more...] about በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ
ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው
ሰሞኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ 2.5 ቢሊዮን ዶላር የሚያወጣውን፤ በ4 ወራት ይጠናቀቃል የተባለውን እና 3 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ማዳበሪያ በዓመት ማምረት ይችላል ተብሎ የተነገረለትን የማዳበሪያ (የዩሪያ) ፋብሪካ ለመገንባት ከዳንጎቴ ግሩፕ ጋር ስምምነት ሲፈረም በሰጡት አጭር መግለጫ ፋብሪካው እንደ ዓባይ ግድብ እንደማይሆን ተናግረው ነበር። ይህ ፕሮጀክት “በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የሚመራ ስራቴጂክ ፕሮጀክት ነው፤ በከፍተኛ ዲሲፒሊንና ቁጥጥር የሚደረግ ነው፤ እንደ ሕዳሴ ግድብ ሜጋ ፕሮጀክት ነው፤ ሕዳሴ ላይ የነበረው ስህተት እዚህ አይደገምም፤ በጥንቃቄና በጥናት የተጀመረ ፕሮጀክት ነው፤ በዕውቀትና በጥንቃቄ ብቻ ነው የሚመራው፤ ምክንያቱም አንድ ፕሮጀክት መጀመራችን ሳይሆን በጥንቃቄ ካልመራነው ተጨማሪ ኃብትና ጊዜ ስለሚያባክን እንደዚህ ዓይነት ስህተት … [Read more...] about ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው
መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ
* “ዓለም እያዘነብን እየሳቀብን ነው አንድ እንሁን” - ዘመነ ካሤ አርበኛ ዘመነ ካሴ “ዓለም እያዘነብንም እየሳቀብንም ነው” በማለት “መተው ነገሬን ከተተው" እንደሚባለው በመተው "አንድ እንሁን" የሚል ጥሪ አሰማ። ፋኖ ኢትዮጵያን ሠርቶ ምስራቅ አፍሪካን ያረጋጋል ብሏል፤ አንድነት ለመፍጠር “አንድ ማንኪያ ቅንነት” ነው የሚያስፈልገው አለ። በጎጃም እና በደቡብ ጎንደር የተሰማራው የአገር መከላከያ በበኩሉ ስም፣ ቦታና ኃላፊነት ጠቅሶ በፋኖ እንቅስቃሴ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱን አስታውቋል። የዘመነ መልዕክት የተሰራጨው የመከላከያ መረጃዎች እኩል ቀን ነሐሴ 16 በሪፖርት መልክ ይፋ ከሆነ በኋላ ነው። "የዕለቱ መልዕክት" በሚል የአማራ ፋኖ በጎጃም መሪ ዘመነ ካሴ "በቃ መተው እንልመድ" ሲል የተለያዩትን የፋኖ አመራሮችና አደረጃጀቶች ዘርዝሮ " ... አንድ መሆን አለበት" … [Read more...] about መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ
ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው
* ከደመቀ መኮንን ጋር የተበቀ ግንኙነት ያላቸው ባለሃብቶች መመለስ “ከዚያስ” አስብሏል * ባለሃብቶቹ በፋኖ ስም ለሚንቀሳቀሰው ሚዲያ በሙሉ “ዩኤስኤይድ” ናቸው በውል የሚታወቁ የጎጃም ባለሃብቶች ከፋኖ ጋር በተያያዘ አስቀድመው ሀገር ለቀው መውጣታቸው ይታወሳል። እነዚሁ ክፍሎች ናቸው ወደ አገራቸው ለመመለስ እንቅስቃሴ ማድረጋቸው የተሰማው። ከቀድሞው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ጋር ጥብቅ ግንኙነት ያላቸው የጎጃም ባለሃብቶች ተመልሶ ወደ አገር ቤት መግባት “ከዚያስ?” የሚል ጥያቄ አስነስቷል። በፋኖ ስም የሚንቀሳቀሰውን ሚዲያ በመደገፍ የሚታወቁትና “የሚዲያው ዩኤስኤይድ” በሚል ቅጽል ስም የሚጠሩት ባለሃብቶች ከተመለሱ የብዙዎቹ የሚዲያ እንቅስቃሴዎች የሚከስም ይሆናል ተብሏል። ወደ አገር ቤት ለመመለስ እየተንቀሳቀሱ ያሉት ባለሃብቶች ከፋኖ ጀርባ ሆነው በፋይናንስና … [Read more...] about ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው
የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ
* ይግባኝ ለማለት ወደ ፖለቲካው መመለስ የግድ ሆኖበታል በአሜሪካ የጥገኝነት ማመልከቻ ያስገባው አቶ በቀለ ገርባ የስደት ፈቃድ ማመልከቻው ውድቅ ተደረገ። በድጋሚ እንዲታይለት ይግባኝ መጠየቁም ታውቋል። ዳግም ወደ ፖለቲካ ተሳትፎ የተመለሰውም በዚህ ሳቢያ እንደሆነ ተመልክቷል። ከእስር ከተፈታ በኋላ ምስጋና ለማቅረብ ወደ አሜሪካ ከጃዋር ጋር ያመራው አቶ በቀለ በምስጋና ጉዞው ወቅት ከአቶ ጃዋር ሲራጅ መሐመድ ጋር ባለመግባባት መለያየቱና ይህ አለመግባባት አዲስ አበባ እያሉ የተጀመረ እንደነበር ጉዳዩን የሚያውቁ ማስታወቃቸው አይዘነጋም። በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ በግል እና በፓርቲ ደረጃ ተሳታፊ የነበረው አቶ በቀለ ገርባ ከፓርቲው የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) በመልቀቅ በአሜሪካ ጥገኝነት መጠየቁን ይፋ ያደረው ራሱ በቢቢሲ በኩል ነበር። ወደ አሜሪካ ከመጣ … [Read more...] about የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ
ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ
ሰሞኑን ሞዐ ተዋሕዶ አየሩን ሞልቶታል። በተለይ በቅርቡ ከሞዐ ተዋሕዶ አመራሮች መካከል አንዱ የሆኑት አቶ ፋንታኹን ዋቄ የሰጡት ቃለ ምልልስ ወደኋላ ሄደን ብዙ ነገሮችን እንድንዳስስ የሚያስደርግ ሆኗል። የዛሬ ሦስት ዓመት በቀነኒሳ ሆቴል ዶ/ር ወንደሰን በሚመራው ስብሰባ መግለጫ በሰጡበት ወቅት የተናገሩትና ሰሞኑን የተሰማውን ጉዳይ ባጭሩ ለማስቀመጥ እንሞክራለን። ይህንን በማድረግም የሞዐ ተዋሕዶን ሁኔታ ለየት ባለ ሁኔታ ለማየት እንሞክራለን፤ እንደተባለው ሞዐ ሃሳብ የሚያመጣና ወደ ሕዝቡ የሚያሰርጽ ንቅናቄ ነው? ወይስ ሌላ ተልዕኮ አለው? የሚለውን በንጽጽር እናያለን። የዛሬ ሦስት ዓመት አካባቢ በቀነኒሳ ሆቴል ከተካሄደው የሞዐ ተዋሕዶ ስብሰባ በኋላ የማኅበረ ቅዱሳን ሚዲያ ከሶስት የሞዐ ተዋሕዶ አመራሮች ጋር ውይይት አድርጎ ነበር። በውይይቱ የተገኙት መምህር ገብረመድኅን እንየው፣ … [Read more...] about ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ









