• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

Editor

“ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ

December 14, 2022 09:59 am by Editor 1 Comment

“ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ

ድሮ ገና ከዓመታት በፊት በ12 ዓመቱ ነበር ሰውን የመርዳት ፅንስ በትንሽ ልቡ ውስጥ የተጸነሰው። ሳድግ የራሴ የበጎ አድራጎት ድርጅት ኖሮኝ ሰዎችን እረዳለሁ እያለ ያወራ ነበር። የእድሜ አቻዎቹ ዶክተር፣ ኢንጅነር፣ ፓይለትና ሌሎችም እሆናለሁ በሚሉበት ለጋ እድሜ የሱ ትንሽ ልብ መሻት አድጎ ሰውን መርዳት መቻል ነበር። ዛሬም በሕይወት ጉዞው ላይ በብዙ ካደገም በኋላ የየቀን ንግግሩ የዘወትር ውዳሴው “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የሚል ቃል ነው። ሰው ስለሆነ ብቻ ሰው ይረዳልና። የራስን ሕይወት ትቶ ስለሰው በሚኖረው ባሕሪው ከሰዎች መካከል ይለያል። የሥጋ ሕመሙ የነፍሱን ቁስል በሻረለት መልካም ሥራው ይታወቃል። ድንቅ የመልካምነት ምሳሌ፣ የመቻል አብነት፤ የደግ ልብ ጌታ ነው። የጥሩዎች ዕንቁ የደጎች አውራ ነው። ብዙዎች በተለያዩ ጊዜያት ደጋችን ነህ ሲሉ በይፋ … [Read more...] about “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ

Filed Under: Middle Column, Social Tagged With: Binyam Belete, Macedonia

“የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “

December 13, 2022 10:30 am by Editor Leave a Comment

“የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “

የኢትዮጵያ ሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም የፌዴራል ሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን በተሿሚዎች፣ በተመራጮች ወይም በመንግሥት ሠራተኞች ላይ እያከናወነ ያለው የሀብት ምዝገባ መረጃ ለሕዝብ ይፋ እንዲያደርግ ጠይቋል። በ2002 ዓ/ም በወጣው የሀብት ማሳወቂያና ምዝገባ አዋጅ ቁጥር 668/2002 ድንጋጌ መሠረት፦* የአገሪቱ ፕሬዚዳንት፣* ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣* ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣* ሚኒስትሮች፣* ሚኒስትር ዴኤታዎች፣* ኮሚሽነሮች፣* ምክትል ኮሚሽነሮች፣* ዋና ዳይሬክተሮች፣* ምክትል ዋና ዳይሬክተሮች፣ እንዲሁም ሌሎች የመንግሥት ሠራተኞች ሀብታቸውን እንዲያስመዘግቡ ግዴታ ጥሎባቸዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም ባወጣው መግለጫ፣ ግለሰቦቹ ለኮሚሽኑ ያስመዘገቡትን ሀብት መረጃ በሚስጥር መያዝና ለሕዝብ ይፋ አለማድረግ ከአዋጁ ጋር  የሚፃረር ድርጊት እንደሆነ … [Read more...] about “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “

Filed Under: Left Column, News Tagged With: Ethiopia Institution of the Ombudsman, operation dismantle tplf

የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ

December 13, 2022 09:42 am by Editor Leave a Comment

የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ

በአሁኑ ወቅት በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች ለሚከሰቱ ግጭቶችና የሰላም እጦት ችግሮች ሙስና ዋነኛው መንስኤ መሆኑን ትራንስፓረንሲ ኢትዮጵያ አስታወቀ። ባለፈው ዓመት በተካሄደው ጥናት መሰረት ኢትዮጵያ በሙስና ከዓለም 87ኛ ደረጃ ላይ እንደነበረች ተጠቁሟል። የትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳሙኤል ካሳሁን ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደተናገሩት፤ ሙስና በኢትዮጵያ እየተከሰቱ ላሉ ግጭቶችና የሰላም እጦቶች ዋነኛ መንስኤ ነው። ኢትዮጵያ የተለያዩ የጸረ ሙስና ስምምነቶችን ብታደርግም፤ የጸረ ሙስና ትግሉን የሚያጠናክሩ ተቋማት አለመኖራቸው ውጤታማ ስራ እንዳይሰራ ምክንያት ሆኗል ነው ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ። በኢትዮጵያ እየተከሰቱ ያሉ ግጭቶችና የሰላም እጦቶች በአንድም ሆነ በሌላ ከሙስና ጋር የተያያዙ እንደሆኑ የተናገሩት አቶ ሳሙኤል፤ ሙስናና ብልሹ … [Read more...] about የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: corruption, operation dismantle tplf, transparency international

ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ

December 13, 2022 09:26 am by Editor Leave a Comment

ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ

በ2014 ዓ.ም. ብቻ ከኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ላይ በተሰረቀ 756 ቶን ብረት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ እንዳጋጠመው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ። በተቋሙ የምስራቅ ሪጅን ዳይሬክተር አቶ ጋሻው እንድሪያስ እንደገለጹት፥ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሚያስተዳድራቸው የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ላይ ተደጋጋሚ ስርቆት እየተፈፀመ ነው። በ2014 ዓ.ም ብቻ 24 የሚደርሱ ከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ የብረት ማማዎች ሙሉ ለሙሉ ተቆርጠው የወደቁ ሲሆን የብረትና የኮንዳክተር ዘረፋ እንደተፈጸመባቸው እና በቁጥር 30 ሺህ 257 የሚሆኑ የተለያዩ የታወር ብረቶች ደግሞ በቁማቸው ካሉ ማማዎች ተፈትተው መወሰዳቸውን ገልጸዋል። ከወደቁትና በቁማቸው ከተዘረፉት ማማዎች 756 ቶን ብረት መሰረቁን የተናገሩት ዳይሬክተሩ፤ በዚህም በገንዘብ ሲሰላ … [Read more...] about ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ

Filed Under: News, Right Column Tagged With: corruption, electric towers, operation dismantle tplf, theft

በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ

December 13, 2022 09:20 am by Editor Leave a Comment

በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ

በሰላም ንግግሩ በተደረሰው ስምምነት መሠረት ተዓማኒ የሆነና ግልጽነት ያለው የሽግግር ፍትሕ የሚፈፀም መሆኑን የፍትሕ ሚኒስቴር ገለጸ። በሰላም ስምምነቱ በተደረሰው ስምምነት መሠረት ተዓማኒ የሆነና ግልጽነት ያለው የሽግግር ፍትሕ ከአፍሪካ ኅብረት የሽግግር ፍትሕ የፖሊሲ ማዕቀፍ ጋር በተጣጣመ መልኩ የሚፈፀም መሆኑን የፍትሕ ሚኒስቴር ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶክተር) ገልፀዋል። በተደረሰው ስምምነት መሠረት ግልፅ እና ተዓማኒ የሆነ የሽግግር ፍትሕ ለማስፈን እንደሚሠራ የገለፁት ሚኒስትሩ፤ ለዚህም ከያዝነው ወር ጀምሮ ሰፊ የሆኑ ሥራዎች ሁሉንም አካላት ባሳተፈ መልኩ እንደሚሠራ ነው የገለጹት። ሁሉም ባለድርሻ አካላት ሃሳባቸው በሚሰማበት እና ወደ ሽግግር ፍትሕ ለሚደረገው ሂደት የበኩላቸውን ተሳትፎ በሚያደርጉበት ሁኔታ በሚያረጋግጥ መልኩ ተዓማኒነት ያለውና ሁሉን አቀፍ … [Read more...] about በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ

Filed Under: News, Right Column Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ

December 13, 2022 09:06 am by Editor Leave a Comment

ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ

ከ30 ሚሊየን ብር በላይ ለግል ጥቅማቸው አውለዋል የተባሉ የብሄራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎት የኮንስትራክሽን እና ሎጂስቲክስ ም/ዳይሬክተር የሆኑት ተስፋዬ ደሜን ጨምሮ በአራት የአገልግሎቱ ሰራተኞች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ። በኢፌዲሪ ፍትሕ ሚኒስቴር የጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ዘርፍ የሙስና ወንጀል ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ጀነራል ዐቃቤ ሕግ በብሄራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎት ስም 29 ሺሕ 200 ኩንታል ሲሚንቶ ከኹለት ፋብሪካዎች ገዝተው ለግለሰቦች በመሸጥ ከ30 ሚሊየን ብር በላይ ለግል ጥቅማቸው ባዋሉ የአገልግሎቱ የኮንስትራክሽን እና ሎጂስቲክስ ም/ዳይሬክተርን ጨምሮ በአራት ሰራተኞች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ መስርቶባቸዋል፡፡ የዐቃቤ ህግ የክስ መዝገብ እንደሚያስረዳው፤ ተከሳሾች በብሄራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎት ውስጥ 1ኛ ተስፋዬ ደሜ … [Read more...] about ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: anti-corruption campaign, operation dismantle tplf

የኢትዮጵያ ወርቅ የት ገባ?

December 8, 2022 03:35 pm by Editor Leave a Comment

የኢትዮጵያ ወርቅ የት ገባ?

ኢትዮጵያ ባለፉት ሶስት ወራት የወርቅ ምርት “በከፍተኛ መጠን” መቀነሱን የብሔራዊ ባንክ ገዢ ዶ/ር ይናገር ደሴ ተናገሩ። የባንኩ ገዢ በሀገሪቱ ነባራዊ ሁኔታ ምክንያት ጥብቅ የፊስካል እና የገንዘብ ፖሊስ መከተል አለመቻሉን ገልጸዋል። ዶ/ር ይናገር ይህን ያሉት የብሔራዊ ባንክን የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድ እና የሩብ ዓመት አፈጻጸም ሪፖርት፤ ለፓርላማ የፕላን፣ በጀት እና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ዛሬ ሐሙስ ህዳር 29 ባቀረቡበት ወቅት ነው። የባንኩ ገዢ በዚሁ ሪፖርታቸው፤ በሩብ ዓመቱ የነበረውን የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ሁኔታ ዳስሰዋል። የሩብ ዓመቱ የወጪ ንግድ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር “መጠነኛ ጭማሪ” ማሳየቱን ያነሱት ዶ/ር ይናገር፤ ገቢው “በተወሰኑ ዘርፎች ላይ” የተገኘ መሆኑን ጠቁመዋል። ሀገሪቱ ላገኘችው ገቢ “ከፍተኛውን ድርሻ” የያዙት አበባ እና ቡና መሆናቸውን … [Read more...] about የኢትዮጵያ ወርቅ የት ገባ?

Filed Under: Middle Column, News, Slider Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, takele umma, tplf terrorist

በበርካታ ዩኒቨርሲቲዎች ከ30 በመቶ በላይ የሚሆኑት መምህራን አያስፈልጉም

December 5, 2022 09:36 am by Editor 1 Comment

በበርካታ ዩኒቨርሲቲዎች ከ30 በመቶ በላይ የሚሆኑት መምህራን አያስፈልጉም

የትምህርት ሚኒስቴር አካሄዱኩት ባለው የዳሰሳ ጥናት፣ በበርካታ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ከ30 በመቶ በላይ መምህራን እንደማያስፈልጉ መታወቁን ሚኒስትሩ አስታወቁ፡፡ የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) የተቋማቸውን የ2015 ዓ.ም. ሩብ ዓመት አፈጻጸም ማክሰኞ ኅዳር 20 ቀን 2015 ዓ.ም. ለፓርላማ ሲያቀርቡ፣ ዩኒቨርሲቲዎች በአማካይ በሴሚስተር አራት ኮርስ ወይም 12 ክፍለ ጊዜ መያዝ እንዳለባቸው ቢጠበቅባቸውም፣ ብዙዎቹ መምህራን በሴሚስተር አንድ ኮርስ አስተምረው የሙሉ ጊዜ መምህራን ተብለው እንደሚጠሩ ተናግረዋል፡፡ በዚህም የተነሳ የዩኒቨርሲቲዎች ራስ ገዝ መሆን ከበጀታቸው ጋር አብሮ ሊሄድ የሚችል የመምህራን ቁጥር በመያዝ፣ በልካቸው ሊራመዱ እንደሚገባ ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪ ዩኒቨርሲቲዎች ከሌሎች የገንዘብ ምንጮች በሚያገኙዋቸው ገቢዎች ተወዳዳሪና ተመራጭ … [Read more...] about በበርካታ ዩኒቨርሲቲዎች ከ30 በመቶ በላይ የሚሆኑት መምህራን አያስፈልጉም

Filed Under: News, Right Column Tagged With: berhanu nega, minister of education

ሌባ እንዲይዝ ተሹሞ የነበረው ሌባ ሆኖ ተያዘ

December 2, 2022 03:00 pm by Editor 2 Comments

ሌባ እንዲይዝ ተሹሞ የነበረው ሌባ ሆኖ ተያዘ

የፖለቲካው መዋቅር ውስጥ ያሉትን ሌቦች የመያዙ ተግባር ይጠናከር የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ቴዎድሮስ በቀለን ጨምሮ በሙስና ወንጀል የተጠረጠሩ ባለስልጣናት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የፍትህ ሚኒስትሩ ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ ተናገሩ። ይህ የተገለፀው በቅርቡ የተቋቋመው የፀረ ሙስና ብሔራዊ ኮሚቴ ስራውን በይፋ መጀመሩን አስመልክቶ የኮሚቴው አባላት ዛሬ መግለጫ በሰጡበት ወቅት ነው። በአዲስ አበባም የአርሶ አደር ልጆች ወይም የልማት ተነሽ ሳይሆኑ የሆኑ በማስመሰል በሐሰት ሙስና የሰሩ ግለሰቦችም ተለይተዋል ብለዋል የብሔራዊ ኮሚቴው አባል ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ። 175 ሺህ ካሬ ሜትር ቦታና የኮንዶሚኒየም ቤት ምዝበራ የፈፀሙ እንዲሁም በፍትህ ዘርፉ ስልጣናቸውን በመጠቀም ከግለሰቦችና ከንግድ ተቋማት ጋር ለግል ጥቅማቸው ሲሰሩ የነበሩ ተጠርጣሪዎችም … [Read more...] about ሌባ እንዲይዝ ተሹሞ የነበረው ሌባ ሆኖ ተያዘ

Filed Under: News, Slider Tagged With: anti-corruption campaign, corruption, operation dismantle tplf

ይህ ሌብነት ሲፈጸም መዐድን ሚኒስቴር የት ነው?

December 2, 2022 12:03 pm by Editor 1 Comment

ይህ ሌብነት ሲፈጸም መዐድን ሚኒስቴር የት ነው?

በህገወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ 4 ነጥብ 18 ኪግ የሚመዝን ‹‹አኳ ማራይን ››የተባለ ማእድን ተያዘ። በጉምሩክ ኮሚሽን የድሬድዋ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ህዳር 22 ቀን 2015 ዓ.ም በድሬድዋ ከተማ ባደረገው ክትትል በተለምዶ ሶስት ኪሎ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ 4 ነጥብ 1 ኪ.ግ የሚመዝን ‹‹አኳ ማራይን›› የተባለ ማዕድን በቁጥጥር ስር አውሏል። ህገ ወጥ አዘዋዋሪዎቹ ማእድኑን ወደ ውጭ ሀገር ለማስወጣትና ለመሸጥ በዝግጂት ላይ እንዳሉ በድሬዳዋ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አመራሮች፣ ሰራተኞችና በብሄራዊ መረጃ ባለሙያዎች በቁጥጥር ስር ሊውሉ መቻላቸውን ኢፕድ ዘግቧል። በዚህ ህግ የማስከበር ስራ ይህንን የሃገር ሐብት ሲያዘዋውሩ የተገኙ አራት ተጠርጣዎች የተያዙ ሲሆን የተያዘው ማእድንም በድሬዳዋ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ገቢ በማድረግ ቀጣይ … [Read more...] about ይህ ሌብነት ሲፈጸም መዐድን ሚኒስቴር የት ነው?

Filed Under: Left Column, News Tagged With: anti-corruption campaign, olf shanee, olf shine, operation dismantle tplf

  • « Previous Page
  • Page 1
  • Page 2
  • Page 3
  • Page 4
  • Page 5
  • …
  • Page 363
  • Next Page »

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule