ሻዕቢያና ትህነግ ጽምዶ ሲመሠርቱ ሻዕቢያ ለትህነግ ሰዎች እንደ ቅድመ ሁኔታና እንደ ትዕዛዝ የሰጠው ሁለት ነጥቦች ያካተተና አፋችሁን ዝጉ የሚል ነበር። አንደኛው ሻዕቢያ በትግራይ ሕዝብ ላይ የዘር ፍጅት ወይም ጄኖሳይድ ፈጽሟል ብላችሁ መናገር አቁሙ፤ ሁለተኛው የሻዕቢያ ታጣቂ የትግራይን ሴቶች ደፍሯል የሚለውን ትንፍሽ ስትሉ እንዳንሰማ የሚሉ ነበር። ሌሎችም አሉ፤ እነዚህ ግን ዋንኞቹ ናቸው። ትህነጋውያንም ጌታና ፈጣሪያቸው ለሆነው ሻዕቢያ መታዘዝ ተፈጥሮአዊ ግዴታቸው ነውና “ጌታ ሻዕቢያ ሆይ! ፍላጎትህ ለኛ ትዕዛዝ ነው፤ እንደ ፈቃድህ ይሁንልህ” ብለው "ጄኖሳይድ" የሚለው ቃል ትግሪኛ እስኪመስል ድረስ ሲጮኹበት የነበረው ልሳናቸው ተዘጋ፤ ሚዲያቸው ጸጥ እረጭ አለ፤ ሻዕቢያም መልካም ነው፤ አሁን ወደ ጽምዶ እንቀጽል አለ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በትላንቱ የፓርላማ ውሎ ከዚህ … [Read more...] about ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …”
አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ
* በስጋት ከቀያቸው የተፈናቀሉት የትግራይ ተወላጆች ቤታቸው ሳይፈርስ፣ ንብረታቸው ሳይጎድል ለዓመታት ጠብቋቸዋል በትላንትናው የፓርላማ ውሎ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በኢሉባቦር ዞን ሁሩሙ ወረዳ ይኖሩ የነበሩ የትግራይ ተወላጆችን አስመልክቶ የተናገሩ የብዙዎችን ልብ የነካና ኢትዮጵያዊነትን አድምቆ ያሳየ መረጃ ነበር። “ለምሳሌ ጦርነት ሲጀመር” አሉ ዐቢይ “ከኢሉባቡር ሸሽተው ትግራይ የሄዱ አርሶ አደሮች ነበሩ። ከዛ የመጣችሁ ሰዎች አጥኑ ይሄን ጉዳይ ትክክለኛ መረጃ ነው። “ሰዎቹ ሸሽተው ትግራይ ገብተዋል፤ ኢሉባቡር ያሉ አርሶአደሮች ከእነርሱ ማሳ ቡና ለቅመው ሸጠው ገንዘቡን በአካውንታቸው ያስገባሉ፤ ሰዎቹ የሉም። ከእርሻቸው ላይ የተመረተ ምርት ሸጠው ገንዘቡን በራሳቸው አካውንት ያስገባሉ። “ሰዎቹ 'የኛ ሰዎች በሌለንበት ሰርተው አካውንታችን እያስገቡ ነውና በቃ … [Read more...] about አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ
የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን
የሪፖርተርን እና የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የ“በሬ ካራጁ” አዋዋል በአንድ ታሪክ እናብራራው … አንድ አውራ ዶሮ የነበረው አንድ ሰነፍ ገበሬ ነበር፤ ገበሬው ይህንን አውራ ዶሮ ከገዛበት ቀን ጀምሮ ዶሮውን ለመብላት የሚመኝ አንድ ኮሳሳ ቀበሮ በገበሬው ቤት ሁልጊዜ ያንዣብባል፤ በሰፈሩ እየዞረም “ዶሮው ታምሟል፤ ጠዋት ይሞታል” እያለ ቀበሮው ለሰፈረተኛው በሙሉ ያወራል፤ የሚወራበትን ያልሰማው ወይም ጆሮ ዳባ ያለው ሰነፍ ገበሬም ጉዳዩን ከመጠየቅና ከማጣራት ይልቅ “ቀበሮው መዞር ከጀመረ አንድ ቀን ሆነው፤ አንድ ሳምንት ሆነው፤ 15 ቀን ሆነው፤ … መቼም ቢርበው ነው” እያለ ያገኘውን ሥጋ ሲመግበውና የዙረቱን “በዓል” ሲያከብርለት ከሰነበተ በኋላ ቀበሮው በደንብ ሲጠበድል ዶሮውንም ያበላውን ገበሬም ሰለቀጣቸው። በኢትዮጵያ በነጻ ሚዲያ ስም በነጻነት እየተንቀሳቀሰ የሚገኘው ሪፖርተር … [Read more...] about የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን
በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ
በአሜሪካ የኦሃዮ ጠቅላይ ግዛት ሴናተር የሆኑት ሪፓብሊካኑ በርኒ ሞሬኖ ጣምራ ዜግነት እንዲቀር ለሕግ መወሰኛው ምክር ቤት Exclusive Citizenship Act of 2025 በሚል ርዕስ ረቂቅ ሕግ አቅርበዋል። አዋጅ ሆኖ ከጸደቀ ዜጎች በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ የሚፈልጉትን እንዲመርጡ ይደረጋሉ። አሜሪካ በስደተኞች የተመሠረተች አገር እንደመሆኗ የኢሚግሬሽን ሕጓ ከአውሮጳውያኑ በተለየ ለስደተኞች የሚያደላ ነው። ለምሳሌ አሜሪካ መጥቶ ጥገኝነት የጠየቀ ሰው ጉዳዩ ከጸደቀለት ከአምስት ዓመት በኋላ ዜጋ መሆን ይችላል። በአሜሪካዊ ዜግነቱ ከሌላ ሀገር ሚስት ቢያመጣ አሜሪካዊ ስላገባች በሚል እሷ በሦስት ዓመት ዜጋ መሆን ትችላለች። ጉዳዩ ሳያልቅለት ወይም ሕጋዊ ሳይሆን ቢቀርና በመካከል ግን ልጅ ቢወልድ ልጁ ዜጋ ይሆናል። ዜግነትንም በተመለከተ ጣምራ ዜግነት በሕግ የሚፈቀድ … [Read more...] about በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ
“ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው
"ጫካ ስንገባ ምክንያታዊ ነበርን አሁንም የሰላምን አማራጭ ተቀብለን ስንመጣ በምክንያት ነው" - ኮሎኔል ፈንታው ሙሀባ "በሰላማዊ መንገድ የአማራን ህዝብ ጥያቄ እናስመልሳለን" - ረ/ፕ እያሱ አባተ ከዚህ ቀደም በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት እና በአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) መካከል የዘላቂ ሰላም ስምምነት መፈረሙ ይታወሳል። ሐሙስ ዕለት ደግሞ ስምምነቱን ውጤታማ ለማድረግ የማስፈፀሚያ ስምምነት ተፈርሟል። ስምምነቱን የአማራ ክልል የሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ እሸቱ የሱፍ (ዶ/ር) እና የአፋሕድ ወታደራዊ አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ ረዳት ፕሮፌሰር ኢያሱ አባተ ነው የተፈራረሙት። በስምምነት ፊርማ ስነስርዓቱ ላይ የሰላም ሚኒስትር አቶ መሐመድ ኢድሪስን ጨምሮ ፣ የመከላከያ አመራሮች፣ የአማራ ክልል አመራሮች የሰላም ጥሪ ተቀብለው የገቡ አካላት ተገኝተው … [Read more...] about “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው
የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም
90ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን በማክበር ላይ የሚገኘው የኢትዮጵያ አየር ኃይል ለምዕተ ዓመት በተጠጋ ጉዞው የሀገርን ሉዓላዊነት ከማስከበር ባለፈ ለአፍሪካ ሀገራት የአየር ኃይል ምስረታ ያበረከተው ታሪካዊ አስተዋጽኦ በኩራት የሚታወስ ነው። በተለይም በ1960ዎቹ አጋማሽ አፍሪካውያን ከቅኝ አገዛዝ ነፃ ለመውጣት በሚታገሉበት ወቅት፣ የኢትዮጵያ አየር ኃይል ለአህጉሪቱ ቀዳሚው እና ብቸኛው የሥልጠና ማዕከል ሆኖ ማገልገሉ የምንኮራበት የታሪካችን አንድ አካል ነው። በወቅቱ የአየር ኃይል ለማቋቋም ፍላጎት የነበራቸው ናይጄሪያ፣ ታንዛኒያ እና ኡጋንዳ የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች እና ቴክኒሻኖቻቸውን በአፍሪካ የተደራጀ ዘመናዊ አየር ኃይል ወደ ነበራት ወደ ኢትዮጵያ በመላክ እንዲሰለጥኑ አድርገዋል። እነዚህ ሰልጣኞችም ወደየመጡበት በመመለስ የየሀገራቸውን አየር ኃይል … [Read more...] about የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም
የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ
በ1930ዎቹ የጀርመን ወግ አጥባቂ ልሒቃን በሀገራቸው እያቆጠቆጠ ያለው ኮሙኒዝም አስፈራቸውና አንድ “መላ” ዘየዱ። በሕዝብ ዘንድ ዝና እያገኘ የመጣውን አዶልፍ ሒትለርን ወደ ሥልጣን ማምጣትና ኮሙኒዝምን ድባቅ መምታት። ውሳኔ ተላለፈ፤ ሒትለርም የፓርቲው ካዝና፣ ቁልፍ፣ ወንበር፣ … ሁሉም ተሰጠው። አጅሬውም ወዲያውኑ የራሱን መስተጋብር በመፍጠር ያበላውን ፓርቲ መልሶ መውጋት ጀመረ። የናትዚው “አውሬ” ሒትለር የዴሞክራሲ መዋቅሮችን አፈራረሰ፣ የተቃዋሚ እንቅስቃሴዎችን አገደ፣ የቀድሞ አጋሮቹን በሙሉ አጸዳና ሥልጣኑን በኪሱ አስገባ። ነፍሰበላ አውሬ እየቀለቡ መሆናቸውን ያልተገነዘቡት ወግ አጥባቂዎቹ ባሳደጉት “ውሻ” ተበሉ። ኢትዮጵያ ውስጥ እንደ ሒትለር እየተቀለቡ ያሉና አንድ ቀን ሊበሉን ያሰፈሰፉ፤ የበሉበትን ወጭት ሰባሪዎች ብቻ ሳይሆኑ ያበላቸውን የሚበሉ ወይም ሊበሉ እያደቡ ያሉ … [Read more...] about የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ
የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች
* ውሳኔው ለአብያተ ክርስቲያናት ኅብረት መንገድ ጠራጊ ነው ተብሏል የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ከዚህ በፊት ለማርያም ተሰጥተዋት የነበሩት “የመድኃኒዓለም ረዳት” (Co-Redemptrix) እና “ሴት አማላጅ” (እናት አማላጅ) (Mediatrix) የሚሉት ስሞች ለማርያም እንዳይውሉ ውሳኔ አስተላለፈች። ውሳኔው በአብያተ ክርስቲያናት መካከል ሊመሠረት ለታቀደው ኅብረት ድጋፍ ሰጪ እንደሆነም ተነግሮለታል። የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያንን የአስተምህሮና ሥነ-ስርዓት የሚመራው “በጳጳሳዊ ምክር ቤት የእምነት አስተምህሮ ጽ/ቤት” (Dicastery for the Doctrine of the Faith (DDF)) በኅዳር ወር መጀመሪያ “የእግዚአብሔር ታማኝ ሕዝብ እናት” (Mater Populi Fidelis) በሚል ርዕስ ስለ ማርያም ሰፊ ማብራሪያ ይፋ አድርጓል። ሰነዱ “የመድኃኒዓለም ረዳት … [Read more...] about የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች
ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር?
* የተዘነጋው የኢህአፓ ነጭ ሽብርና የወቅቱ ኢህአፓ አካሄድ ነጭ ሽብርም ሆነ ቀይ ሽብር በቀለም መጠሪያቸው ካልተለያዩ በቀር ሁለቱም ሽብር ናቸው። መስከረም 21 ቀን 1969 ዓ.ም. አዲስ አበባ ሞርጌጅ ህንጻ ውስጥ ትሠራ የነበረችውን ባለቤታቸውን መኪናቸው ውስጥ ሆነው በመጠባበቅ ላይ እያሉ አድብተው ይጠብቁ በነበሩ የኢሕአፓ ነፍሰ ገዳዮች በቅርብ ርቀት በተተኮሰ ጥይት ሕይወታቸው ያለውፈው በወቅቱ በሕዝብ ድርጅት ጉዳይ ጊዜያዊ ጽ/ቤት የጊዜያዊ ጉዳዮች ሰብሳቢ የነበሩት ዶ/ር ፍቅሬ መርዕድ ነጭ ሽብር ከበላቸው ዜጎች አንዱና ነጭ ሽብር ራሱን ያስተዋወቀበት ኦፕሬሽኑ ነው። ሚስታቸውን ጋንዲ ሆስፒታል ጠይቀው ሲወጡ ቀይ መስቀል አካባቢ አድፍጠው ሲጠብቋቸው በነበሩ የኢህአፓ ነፍሰ ገዳዮች የተገደሉት ሌላው ነጭ ሽብር የበላቸው ዜጋ የወቅቱ የኢሰማኮ ሊቀመንበር የነበሩት ተመስገን … [Read more...] about ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር?
EOC Bans Haile Gebrselassie Over Areqie Comments Linked to Doping
The Ethiopian Olympic Committee (EOC) has imposed an indefinite ban on legendary athlete Haile Gebrselassie following remarks he made about the locally distilled alcoholic beverage areqie and its use among some athletes. The decision, originally reached in late September 2025, also includes the formation of a committee to monitor potential consequences arising from the controversy. Repeated attempts by Addis Reporter to reach Haile for comment were unsuccessful. Haile’s comments appear in … [Read more...] about EOC Bans Haile Gebrselassie Over Areqie Comments Linked to Doping










