• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አይ አበሻ! አበሻና ልመና፦ አንድ

December 16, 2013 08:49 am by Editor 14 Comments

በዓለም ሕዝቦች መሀከል ውድድር ቢደረግ ያለጥርጥር አበሻ አንደኛ ከሚወጣባቸው ነገሮች አንዱ ልመና ሳይሆን አይቀርም፤ ለአበሻ፣ ልመና የኑሮ ዘዴ ነው፤ እንዲያውም ከልመና ውጭ የሆነ ኢትዮጵያዊ ኑሮ የለም ለማለት የሚቻል ይመስለኛል፤ ስለዚህም ልመና ባህላዊ ጥበብ ሆኖአል፤ አንዳንድ አላዋቂዎች፣ አንዳንድ አዋቂዎችም አንዳንዴ እየተሳሳቱ ልመናን እንደነውር ይገልጹታል፤ ልመና ነውር አይደለም፤ ለጨዋ ልጆችማ አንዳንድ አጥንትን የሚያበላሽ ሥራ ከመሥራት ለምኖ መብላት ክብር ነው፤ ይህ ባህላዊ ጥበብ ያልገባቸው የድሬ ዳዋ ለማኞች ብቻ ናቸው፤ እጃቸውን እየዘረጉ ‹‹እስቲ አሥር ብር ስጠኝ!›› ይላሉ! በጫት ሞቅ ሲላቸው መቶ ብር ይጠይቃሉ፤ የድሬ ዳዋ ልመና መሆኑ ነው!

የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው፤ ቄሶቹ ምንም ይስበኩ በተግባር እንደሚታየው ጽድቅ የሚገኘው በልመና ነው እንጂ በሥራ አይደለም፤ ሥራኮ ለአበሻ ከእርግማን የመጣ ነው፤ አበሻ አልተረገመ፤ ታዲያ ለምን ብሎ ይሥራ! አሁን እንደሚሰማውና እንደሚመስለኝ አገዛዙም እንደተቀበለው የቻይና ሰዎችም እንደመሰከሩለት ከሥራ ጋር ጠብ አለው፤ ደግሞስ ለምን ይሥራ! ለአንድ እንጀራ? ለተራበ አብልተው ለመጽደቅ የሚፈልጉ ስንትና ስንት ሰዎች አሉ፤ ስለዚህም ደግ ሰዎች መጽውተው እንዲጸድቁ በግድ ለማኞች ያስፈልጋሉ፤ ለመጽደቅም መለመን ያስፈልጋል፤ ጸሎት ልመና መሆኑን አትርሱ፤ ስለዚህም ዋናውና ከፍተኛው ልመና ወደእግዚአብሔር ነው፤ ብልጦቹ እግዚአብሔርን የሚለምኑት ሥልጣን፣ ሀብትና ጉልበት ነው፤ አንድ ቀን ተነሥተው እግዚአብሔር ሥልጣን፣ ሀብትና ጉልበት እንደሰጣቸው ያውጃሉ፤ አውጀውም በሕዝብ ራስ ላይ ይወጣሉ፤ በራሱ ላይ ወጥተውም ይጨፍራሉ፤ ሰውን ከመሬቱ፣ መሬቱን ከሰው መለየት ይሳናቸዋል፤ ሰውን ከመሬቱ፣ መሬቱን ከሰው ያጣላሉ፤ እግዚአብሔር ለእናንተ ብቻ እንዴት ሰጣችሁ? እግዚአብሔር እኛን ለምን ነፈገን? ብሎ የሚጠይቃቸውን እየደበደቡና እያቃጠሉ፣ እየገረፉና እያራቆቱ በዝምታ እንዲገዛ ያደርጉታል፤ አልበቃው ካለም አካሉን ለውሻ ሰጥተው ነፍሱን ወደእግዚአብሔር ይወረውራሉ፤ እግዚአብሔር እየቆጠረ የማይመዘግብ ይመስላቸዋል፤ የጠጠረ ጉልበታቸው ዓይኖቻቸውን አውሮ፣ ኅሊናቸውን አፍኖ እግዚአብሔር በዕዳ እንደሚይዛቸውና በጥጋባቸው ያደሉትን መከራና ስቃይ፣ የወረደውን እንባና ደም ከነወለዱ እንደሚያስከፍላቸው መገንዘብ ያቅታቸዋል።

እግዚአብሔር ፍርዱን እስቲሰጥ ድረስ ሥልጣን፣ ሀብትና ጉልበት ተረክበናል የሚሉት የተለያዩ ስሞችን እየለጠፉ በተዋረድ የለማኞችን ሠራዊት ያደራጃሉ፤ ሕዝብ ሁሉ ከነዚህ የለማኞች ሠራዊት በአንዱ ውስጥ ለመግባት በፉክክር ይተላለቃል፤ ሠራዊቱ ውስጥ በመግባት የሚገኘው ጉርሻ ልጆቻቸውን እንኳን ከረሀብ የማያድን መሆኑን ሳይገነዘቡ መብታቸውን እያስረገጡ የሌሎችን መብት ለመርገጥ መሣሪያ ይሆናሉ፤ እነዚህ እንግዲህ ልመናን በማኅበረሰቡ ውስጥ ተክለው እየኮተኮቱ የሚያስፋፉት ናቸው፤ ልመናን ባህል የሚያደርጉት እነዚህ ናቸው፤ ልመናን ታሪካችን ያደረጉት እነዚህና ከነሱ የቀደሙት ገዢዎቻችን ናቸው።

በእኛ ባህል የራበውን በማብላት ጽድቅ ይገኛል፤ ስለዚህም ለምኖ መብላት ይቻላል፤ ስለዚህም ሰዎች መጽውተው እንዲጸድቁ በግድ ለማኞች ያስፈልጋሉ፤ እንግዲህ ለምነው እየበሉ መኖር ከተቻለና እግዚአብሔርን በመለመን ጽድቅ ከተገኘ፣ የመሬቱንና የሰማዩን ጣጣ በልመና መገላገል ከተቻለ ታዲያ ሥራ ለምን ያስፈልጋል! ለነገሩስ ሥራ በእርግማን የመጣ ነው፤ ስለዚህ የተረገሙት ሲሠሩ ያልተረገሙ የሚመስላቸው ይለምኑ፤ ለሌላው ዓለም ልመና የችግር ምልክት ነው፤ ለአበሻ ግን ልመና የጽድቅ ምልክት ነው፤ የጨዋ ልጅ፣ ማለት በልመና በሰዎች ላይ ሥልጣንን ከአግዚአብሔር አግኝቻለሁ ብሎ የሚያምን፣ አይሠራም፤ ቀን ቢጥለውም የጨዋ ልጅ በእጁ ሠርቶ ከሚበላ ለምኖ ቢበላ ይሻለዋል፤ ሆድ የተፈጥሮ ነው፤ ረሀብም የዕለት ከዕለት የተፈጥሮ ግዳጅ ነው፤ ስለዚህም ለአበሻ የተፈጥሮን ሆድና የተፈጥሮን ረሀብ በልመና መወጣት የተፈጥሮን ሥርዓት መከተል መስሎ ይታየዋል።

ሌላ ቀርቶ ተማሪ ለምኖ ካልበላ ትምህርት አይገባውም፤ ለተማሪ ሲሆን ልመና አይባልም፤ ቀፈፋ ነው፤ አበሻ በልመና ምን ይህል እንደተራቀቀ የሚያመለክተው ለተለያዩ ልመናዎች የተለያዩ ስሞች ማውጣቱ ነው፤ እንደተባለው ተማሪ ሲለምን ቀፈፋ ነው፤ በዘመናዊ ቋንቋ የትምህርት ታክስ ነው፤ ምግብ የሚቀርብበትን ሰዓት እየጠበቀ ከተፍ የሚለው ቀላዋጭ ነው፤  አብዛኛውን ጊዜ ለቀላዋጭ ቀላል ሰበብ የሚሆነው ቀላውጦ የሚያገኘው ወሬ ነው፤ ሌላም የልመና ዓይነት አለ፤ እርጥባን ይባላል፤ — ደርቄአለሁና አርጥቡኝ ማለት ነው! ‹ላሊበላዎች› የሚባሉት ለምነን ካልበላን እንቆመጣለን በማለት ልመናን የኑሮ መሠረት አድርገውታል፤ ሌላም የልመና ዘር አለ፤ ደጅ መጥናት ይባላል፤ ደጅ መጥናት ማለት ብርዱን ችሎና እንቅልፉን አቋርጦ በሌሊት እየተነሡ በመኳንንቱና በመሳፍንቱ፣ በንጉሡ፣ በንጉሠ ነገሥቱ ደጃፍ ላይ አጥር ወይም ዛፍ እየተደገፉ የተፈለገውም ሰው ብቅ ሲል በመሬት ላይ በመነጠፍ እጅ በመንሣት ፊት ለማስወጋት ለመታወቅና ለሹመት ለመታጨት የሚጠቅም የልመና ዘዴ ነው፡፡ በአበሻ አገር ሁሉም ነገር በልመና ነው፤ ምግብ በልመና፣ ትምህርት በልመና፣ መሬት በልመና፣ … በልመና፣ ግብር የሚከፈለው በልመና ነው፤ ሥልጣን የሚገኘው በልመና ነው፤ ንጉሥነትም የሚገኘው በልመና ነው፤ ባጭሩ ኑሮ ማለት ልመና ነው፤ ልመና ማለት ኑሮ ነው ።

ምንጭ: Mesfin Wolde-Mariam Blog

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Uncategorized Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. ezra says

    December 21, 2013 03:57 am at 3:57 am

    አዬ ፕሮፌሰር መስፍን! ሁሌ መቼም ኢትዮጵያዊ ውርደትን እንደ “ጨዋ” ተግባር አድረገው በማቅረብ ወዳጆቻችው የሆኑትን ነጭችን በጹፋቸው ያስፈንድቃሉ። ነገ ደግሞ ስርቆትንና የቡደን ዝርፊያን ፕሮፌሰር መሥፍን ባማዳነቅ አቦ ሲዘርፉ እንዴት ያስደንቃሉ ብለው …? ” ኖቬል” የሚያሸልም የ “አበሻ ጀብዱ” ብለው ይጽፉልናል። እሳቸው መቼም ዉርደትን በተቃራኒው ነው አሳመረው በጽሁፋቸው የሚያቀርቡት ። አሁን ማን ይሙት በዉነቱ ሥራ እንጅ “ልመና”፡ ያስክበራልን? ፕሮፌሰሩ “አጥንት ከሚሰብር ስራ” ልመና ይሻላል ብለው ወጣቱን አደራጅቶ ማታገሉ ሲያቅታቸው የለም “ለምኖ መኖርን የመሠለ የለም”፡ብለው አገር ተረካቢዉን ወጣት እንዲለምን ያበረታታሉ። ምን ይደረግ ነፍሱ አይማርና ልመናንን እንደ ትልቅ ክብር አደርጎ መለሠ ዜናዊ ለጌቶች የአውሮፓና አሜሪካ መንግስታት እንገዲህ ደረቅ በአገሪቱ እየገባ ነው ይኽው ነገሪያችኋለሁ፡፤ እኔ ኃላፊነት የለብኝም ባስችኳይ እርዳታ እንዳታደርጉልን ብሎ ጌቶቹን(ነጮችን) ሲማፀንና ሲለምን ልመናዉን እንደ ክበር ቆጥሮት ነበር የእነርሱ እዳ አድርጎት ። WHAT A SHAME! ፕሮፌሰር መሥፈን ወልደማርያም በዚህ እድሜያቸው ልመናን ኣድንቀው መፃፋቸው በጣም አሳፍሪ ብቻ ሳይሆን የሚያስገምታቸዉም ነውና- እባክዎን እድሜዎን ለመጥፎ ነገር አይጠቀሙበት።

    Reply
    • mindpeace says

      December 22, 2013 09:13 am at 9:13 am

      @ezra: I think you did not understand the message of this article. This article is written to discourage the culture of begging in Ethiopia. It further emphasized that begging/dependency is deep rooted in the culture, norms and history of Ethiopia. This article intended for the readers that they should understand the magnitude of of begging/dependency problem and to incite the readers fight against it. In conclusion, the way this article is written is known in Amharic as “Silak” that is the reverse is true.

      Reply
    • me says

      January 1, 2014 03:44 pm at 3:44 pm

      እኛ ሃበሾች ስንባል እውነቱን የሚያወራውን ሳይሆን የሚያባብለንን እናምናለን ለማኞች ነን አዎ ግጥም አርገን ለማኞች ነን ከንቱዎች ነን። ግን ብንሆንስ!!!

      Reply
  2. Demeke Yeneayhu says

    December 27, 2013 06:25 pm at 6:25 pm

    @Ezera

    I wonder about your reading level. Stupid, the least!

    Reply
  3. yekefaw says

    December 28, 2013 02:56 am at 2:56 am

    This so called professor is really out of realty. It is shame to hear such kind of categorization of Ethiopians. I believe this so called professor leaved for his stomach through out the past governments. I haven’t seen any Ethiopian who is begging in the western world. We Ethiopians are known for sharing during hard times and celebrating together when we have. My fellow Ethiopians, please watch out these kind of professors. They don’t have respect to themselves nor to their people. So don’t take every thing at face value because the professor said so. Long live Ethiopia and its people.

    Reply
  4. Nathyson says

    December 28, 2013 05:26 am at 5:26 am

    I was so surprised to have read such demeaning article from one of the best professors in Ethiopia. This is really an insult to the hardworking Ethiopians who have a longstanding bondage to one another. How on earth could one advocate begging as something
    that the Ethiopian People could live without? I wouldn’t consider the professor’s intent is to discourage begging as such.. With all due respect to the Professor, this is excruciatingly painful piece of article I can possibly imagine. Thanks to Dagnachew’s thoughtful response to the Professor on Ethio-Media (in Amharic) where he clearly showed us how the Professor dropped the ball regardless of his age, knowledge and authority on Ethiopian history and culture.

    Reply
  5. Chuchu says

    December 28, 2013 03:35 pm at 3:35 pm

    I see nothing wrong in this article,this is prevailing reality that we can’t deny.We don’t like when our weak sides are told this way forward.Tell the people their weak side so that they can learn from it.Don’t glorify with empty words and put them in a position they don’t suppose to be.Good article professor!!!

    Reply
  6. ezra says

    December 29, 2013 05:06 am at 5:06 am

    የሚገርም ነው የነ Demeke ኣስተያየት! ፕሮፈሰሩ ኣይሳሳቱም ፣ ከተሳሳቱም እንደተሳሳቱ አደርጎ መመልከት ወይም መተርጎም “ኣብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ሕገ-መንግስታዊነትን” እንደመንካት አስቆጥሮ ያስቀጥፋል ዓይነት መሰለኝ የነ DemeKe Yeneayehu አስተያየት። ይቅር ይበለህ Demeke

    Reply
  7. Thomas Ayalkebet says

    December 29, 2013 06:59 pm at 6:59 pm

    God Bless Professor Mesfin. He is the mirror that shows us who we are indeed… He uses his brain well and honors his GOD; take your time to really really really understand the message … make sure you all use your brains very well before you attack Professor Mesfin… How dare any logical person ? To really change, we need to openly talk about who we really are? Understanding our “Hodam” nature is like going 50% of our way to the solutions …for our country’s future.

    You know even the significant majority of our priests, pastors and Imams are hodam first ( just like our so called politicians) and worship their GOD last and their congregations are consistently fooled…
    GOD NEVER SAID DO NOT USE YOUR THINKINGKING ABILITIES. NEVER …

    May we all use our brains and HONOR OUR GOD and live in a free world where we could all think and ask questions of our so called religious leaders and so called politicians…We know God does not appreciate Hodams and people that do not use the brains HE Gave them… Peace!!!

    Reply
  8. Joo says

    December 30, 2013 07:17 pm at 7:17 pm

    Thank you Prof. You have showed us who we are.

    Reply
  9. Sabure says

    December 31, 2013 03:39 pm at 3:39 pm

    Professor Mesfin

    Abesha yemilew tshufwo meleekt rswonm slemichemir ene bizu alkefagnm. Yih yedeberewot yelmena bahel abebo endigomera kekotekotut sewoch mekakel erso be ginbar kedem yitekesalu. Yelmena eset meseretu saytal lemenad ewuketum hone gize fekdolwot neber. Ende edel hono yanen aladeregum. Begulbet yaladereguten beshibet binteketek ena bejimla bisadebu men waga alew. Degmo wushaw mindenew? woi reesun ABESHA ENA WUSHA YIBELUT. Ayyee… kareju aybeju ale yagere sew

    Reply
  10. weldemeskel says

    January 1, 2014 02:32 am at 2:32 am

    abet profeser seyasaznu endih aynet erkash ena tera sidib kerso ayitebekim. Lenegeru eraswon new yesedebut. betam yasafral yastemaruwachew betam yaznubotal erswo yethafut mehonunem yiterateralu. Tadia ene erswon bihon tolo biye mastebabeya eset neber alebelezia betesebocho saykeru yafrubotal. asafari astesaseb newna.

    Reply
  11. dereje says

    January 2, 2014 09:15 pm at 9:15 pm

    Beggis is really a part of our culture weather we admit or not. It is something that we inherited from the feudalist Ethiopia of the past. To identify , admit , get over it and try to change a percieved bad calture is not something to be ashamed of. I have heard many criticizing the proffesor for not magnifying the goodness of Ethiopian culture as something a static being that never go under any reform or a change. Self decieving is the worst kind of spiritual poverty.

    Reply
  12. Bewunetu says

    January 4, 2014 08:28 am at 8:28 am

    It is sad that most of commentators didn’t want to hear the truth, that among Ethiopian population, Habasha is known by it’s culture of begging. Even proud of it by saying “bileminim Amhara negne” to reflect false history about Amhara’s hierarchy over other peoples of Ethiopia. It is not secret that the sources of beggary and prostitution in Ethiopia is Abasha people. It is a time to accept the reality and try to eliminate for the future. Denying doesn’t change the history of these bad culture; instead, it is necessary to focus and work on to change once and for all than criticizing those who speak out the truth. Please don’t jump to insult eye witnesses of history who lived in it, but try to learn from them.
    PROFESSOR, THANK YOU AND GOOD LUCK!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የሲኖዶሱ ውዝግብ አካሄድና መጪው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ February 6, 2023 02:03 am
  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule