• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የመሬት ባላባቱን” አባይ ማን ይድፈራቸው?

March 4, 2016 09:36 am by Editor 4 Comments

ከተለያዩ አቅጣጫዎች በተቃውሞና ዓመጽ የተወጠረው ህወሃት/ኢህአዴግ በአስሩም ክፍለከተሞች የሚገኙ እስከ 600 የሚደርሱ የመሬት ባለሙያዎችን ካገደ በኋላ የአዲስ አበባ የመሬት አስተዳደር ሞሳኞች ያላቸውን 85 አመራሮችና ሠራተኞችን በቁጥጥር ሥር አውሏል፡፡ “የመሬት ከበርቴውን” አባይ ጸሃዬንስ ማን ይደፍራቸው ይሆን የሚለው የብዙዎች ጥያቄ ሆኗል፡፡

በአባይ ጸሃዬ “ልክ እናስገባለን” ተግባራዊ እንዲሆን የታሰበው የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን በገጠመው ከፍተኛ ተቃውሞ ከተስተጓጎለ በኋላ ህወሃት/ኢህአዴግ ማስተር ፕላኑን “ትቼዋለሁ” ቢልም የኦሮሞ ሕዝብ ያስነሳው ተቃውሞ ግን እስካሁን አልበረደም፡፡

“መልካም አስተዳደርን አሰፍናለሁ” በሚል ኢህአዴግ የሕዝቡን ቀልብ ለመሳብ ከላይ ታች እየተራወጠ ነው የሚሉ ለጎልጉል አስተያየታቸውን የሰጡ እንደሚሉት ኪራይ ሰብሳቢነት ለመዋጋት በሚል የሚደረገው ድራማ ሙስናን በማንኪያ የመንካት ያህል ነው፡፡ ምክንያቱም ከመሬት ጋር በተያያዘ በሙስናው እና በመሬት ዘረፋው የተጠመዱት ከፍተኛ የህወሃት ሹሞች ናቸው ይላሉ፡፡

“በየትኛውም ደረጃ ያሉ ከፍተኛ ባለስልጣናት፣ በደህንነት ውስጥ ያሉ ባለስልጣናትና መካከለኛ ደረጃ ሃላፊዎች በግልጽ ሙስና ውስጥ መዘፈቃቸው በመረጃ ቢቀርብም ጸረ ሙስና ኮሚሽን እርምጃ የማይወስደው ሙስና አንዱ የስርዓቱ እድሜ ማራዘሚያ መንገድ በመሆኑ ነው፤ ኢህአዴግን እያገለገሉ ያሉ ባለስልጣኖች ህወሃትን በሚገባ መከራከር የማይችሉትና በታዛዥነት እያጎበደዱ ለመኖር የሚገደዱት የገቡበትን የሙስና ማጥ ስለሚያውቁት ከተቃወምን እንታሰራለን” በሚል ፍርሃቻ መሆኑን የኮሚሽኑ ባልደረባ ለጎልጉል መናገራቸውን ከዚህ በፊት ዘግበን ነበር፡፡

በጥርስ አልባው የጸረ ሙስና ኮሚሽን መርማሪዎች ዘንድ “የመሬት ባላባት/ከበርቴ” እየተባሉ የሚጠሩት አባይ ጸሃዬ ከሙሰኞቹ በቅድሚያ ተጠቃሽ ናቸው፡፡ ጎልጉል በመስከረም 2005ዓም ባተመው “የመሬት ባላባቱ” ሚኒስትር!! በሚለው ዜና ላይ አባይ ጸሃዬ በዘመዶቻቸው ስም በርካታ መሬቶችን መውሰዳቸውን፤ በተለይ በቦሌ ክፍለከተማ በመሬት አስተደዳር ሥልጣን የነበራቸው የአቶ አባይ የቅርብ ዘመድ መሆናቸውን፤ ከመሬት ጋር በተያያዘ የተፈጸመ ከፍተኛ ሙስና አለ በሚል ጸረ ሙስና በደረሰው ጥቆማ ምርመራ ጀምሮ ጉዳዩ “ወዳልተፈለገ” አቅጣጫ ሊያመራ ሲል ከበላይ በተላለፈ ትዕዛዝ ምርመራው እንዲቆምና በቁጥጥር ሥር ውለው የነበሩት መሃንዲሶች እንዲፈቱ መደረጉን ለጎልጉል ከደረሱት መረጃዎች ጋር በማጣቀስ ዘግበን ነበር፡፡

ሪፖርተር ጋዜጣ ረቡዕ ባወጣው ዜና 85 የመሬት አመራሮችና ሠራተኞች ሙስና ፈጽመዋል በሚል በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን፤ ከዚሁ የመሬት አስተዳደር ጋር በተያያዘ ከአዚህ በፊት 600 ሠራተኞች ላይ ዕርምጃ መወሰዱን ዘግቦ ነበር፡፡

ሰሞኑን የጎልጉል እማኝ ዘጋቢ (ireporter) በላኩልን መረጃ መሠረት እነዚህ 600 ያህል የሚሆኑት “ኪራይ ሰብሳቢነትን” እና “ሙስናን” ለመዋጋት በሚል “ዕርጃ የተወሰደባቸው” በትንሹ ለሰባት ዓመታት በመሬት አስተዳደር በመሃንዲስነትና ተመሳሳይ ሙያ ያገለገሉ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ በተለይ ደመወዛቸው አይነካም በሚል በዝቅተኛ የሥራ መደብ ላይ እንዲመደቡ የተደረጉት በራሳቸው ፈቃድ ሥራቸውን እንዲለቁና በምትኩ አንድን ወገን ያማከለ የታማኞች ቅጥር ለመፈጸም የተሰበ እንደሆነ እማኝ ዘጋቢው ያስረዳሉ፡፡

ከመሬት አስተዳደር ጋር በተያያዘ የሚፈጸሙ ወንጀሎችና የሙስና ተግባራት እንዳሉ የሚናገሩት ዘጋቢው ውሳኔው ወገንተኛና የሥርዓቱን ቁንጮዎች የማይነካ መሆኑ አግባብነት የሌለው ብቻ ሳይሆን ሕዝብን አፍ ማስዘጊያ የማባበያ ጥገናዊ ለውጥ እንደሆነ ይጠቁማሉ፡፡

ከዚህም ሌላ ሁለት መሠረታዊ ነጥቦችን እማኝ ዘጋቢው ይጠቅሳሉ፤ አንደኛው በሚነሱት ሠራተኞች ምትክ ባለሙያ ለመመደብ በቂ ዝግጅት አለመደረጉና በቅጥር ቦታቸውን ለመተካት የሚደረገው ሙከራ ኅብረተሰቡን ለተጨማሪ እንግልት የሚዳርገው ሲሆን በሁለተኛ ደረጃ ብዙ ሚሊዮን ብር ወጪ ተደርጎበት “የካይዘን መመሪያ (ፕሪንስፕል)” ለመተግበር በሚል በየክፍለከተማው የተሰጠው ሥልጠና ለነዚሁ ከሥራቸው የተነሱት ባለሙያዎች መሆኑ ሥልጠናውን ዋጋቢስ የሚያደርግ ሲሆን በሠራተኞቹ ላይ ተወሰደ የተባለው እርምጃ ግብታዊና ፖለቲካዊ ውሳኔ እንደሆነ ይናገራሉ፡፡

ከዚህ ሁሉ በላይ የእማኝ ዘጋቢውም ሆነ የሌሎች አስተያየት ሰጪዎች ዋና ጥያቄ በሙስና የተዘፈቁትን የህወሃት ቁንጮ ባለሥልጣናትን ማነው የሚደፍራቸው የሚል ነው፡፡ “እነሱው ሙሰኛ፤ እነሱው የጸረ ሙስና ሕግ አውጪ፤ እነሱው የሕግ ተርጓሚ፤ እነሱው ፈራጅ፤ እነሱው አሳሪ፤ …” በሆኑበት አገር ዋንኞቹ የመሬት ነጣቂዎችና ከበርቴዎች ምንም ሳይሆኑ ከላይ ከላይ የሚወሰደው እርምጃ ጊዜያዊ ጥገናዊ መሻሻል እንጂ ተሃድሶአዊ ለውጥ እንደማያመጣ ይናገራሉ፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. gud says

    March 4, 2016 12:58 pm at 12:58 pm

    Abay is always clean of any corruption .

    Reply
  2. Yikir says

    March 6, 2016 06:38 pm at 6:38 pm

    Abayin yedefere jegina Meles ;Melesin yedefere ;ABEBE GELLAW SIHON ;ABEBE GELLAWIN YETEKAW ABEBE BIKILA NEW.

    Reply
  3. Solomon says

    March 24, 2016 05:41 pm at 5:41 pm

    Gud,

    I see now you are one of those members of the TPLF…. Why are you so coward to hide yourself say your name Tecklay or Kiflay no body is going to hunt you. I can tell that you are a 4th grader soldier but now a Minister.

    Reply
  4. Nimona Lammi says

    April 3, 2016 06:22 pm at 6:22 pm

    አባይ ፀሐይ ማለት የአመራር ብቃት ፣ የሥነልቦና ዝግጁነት ፣ የአካዳሚክ ዕውቀት ሳይኖረው በጫካ ውስጥ የውንብድና ተግባራት በመፈፀሙ በማሀይሞች ቡድን ላይ የነገሰ ሽፍታ እንጅ በምንም ታሀምር በኢትዮጵያ ውስጥ ወደ ሥልጣን የሚያመጣ ብቃትም ፣ ዕውቀትንም ሞራልም የሌለው መሐይም ነው ።በዚህ በዘገምተኛ እና በባዶ ጭንቅላቱ የሚፈፅማቸው የሚናገራቸው ነገሮች ከመናቅ ውጭ ምንም ልንለው አይገባንም ሰውዬው retarded (Ideot) ነው ።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule