• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የመሬት ባላባቱን” አባይ ማን ይድፈራቸው?

March 4, 2016 09:36 am by Editor 4 Comments

ከተለያዩ አቅጣጫዎች በተቃውሞና ዓመጽ የተወጠረው ህወሃት/ኢህአዴግ በአስሩም ክፍለከተሞች የሚገኙ እስከ 600 የሚደርሱ የመሬት ባለሙያዎችን ካገደ በኋላ የአዲስ አበባ የመሬት አስተዳደር ሞሳኞች ያላቸውን 85 አመራሮችና ሠራተኞችን በቁጥጥር ሥር አውሏል፡፡ “የመሬት ከበርቴውን” አባይ ጸሃዬንስ ማን ይደፍራቸው ይሆን የሚለው የብዙዎች ጥያቄ ሆኗል፡፡

በአባይ ጸሃዬ “ልክ እናስገባለን” ተግባራዊ እንዲሆን የታሰበው የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን በገጠመው ከፍተኛ ተቃውሞ ከተስተጓጎለ በኋላ ህወሃት/ኢህአዴግ ማስተር ፕላኑን “ትቼዋለሁ” ቢልም የኦሮሞ ሕዝብ ያስነሳው ተቃውሞ ግን እስካሁን አልበረደም፡፡

“መልካም አስተዳደርን አሰፍናለሁ” በሚል ኢህአዴግ የሕዝቡን ቀልብ ለመሳብ ከላይ ታች እየተራወጠ ነው የሚሉ ለጎልጉል አስተያየታቸውን የሰጡ እንደሚሉት ኪራይ ሰብሳቢነት ለመዋጋት በሚል የሚደረገው ድራማ ሙስናን በማንኪያ የመንካት ያህል ነው፡፡ ምክንያቱም ከመሬት ጋር በተያያዘ በሙስናው እና በመሬት ዘረፋው የተጠመዱት ከፍተኛ የህወሃት ሹሞች ናቸው ይላሉ፡፡

“በየትኛውም ደረጃ ያሉ ከፍተኛ ባለስልጣናት፣ በደህንነት ውስጥ ያሉ ባለስልጣናትና መካከለኛ ደረጃ ሃላፊዎች በግልጽ ሙስና ውስጥ መዘፈቃቸው በመረጃ ቢቀርብም ጸረ ሙስና ኮሚሽን እርምጃ የማይወስደው ሙስና አንዱ የስርዓቱ እድሜ ማራዘሚያ መንገድ በመሆኑ ነው፤ ኢህአዴግን እያገለገሉ ያሉ ባለስልጣኖች ህወሃትን በሚገባ መከራከር የማይችሉትና በታዛዥነት እያጎበደዱ ለመኖር የሚገደዱት የገቡበትን የሙስና ማጥ ስለሚያውቁት ከተቃወምን እንታሰራለን” በሚል ፍርሃቻ መሆኑን የኮሚሽኑ ባልደረባ ለጎልጉል መናገራቸውን ከዚህ በፊት ዘግበን ነበር፡፡

በጥርስ አልባው የጸረ ሙስና ኮሚሽን መርማሪዎች ዘንድ “የመሬት ባላባት/ከበርቴ” እየተባሉ የሚጠሩት አባይ ጸሃዬ ከሙሰኞቹ በቅድሚያ ተጠቃሽ ናቸው፡፡ ጎልጉል በመስከረም 2005ዓም ባተመው “የመሬት ባላባቱ” ሚኒስትር!! በሚለው ዜና ላይ አባይ ጸሃዬ በዘመዶቻቸው ስም በርካታ መሬቶችን መውሰዳቸውን፤ በተለይ በቦሌ ክፍለከተማ በመሬት አስተደዳር ሥልጣን የነበራቸው የአቶ አባይ የቅርብ ዘመድ መሆናቸውን፤ ከመሬት ጋር በተያያዘ የተፈጸመ ከፍተኛ ሙስና አለ በሚል ጸረ ሙስና በደረሰው ጥቆማ ምርመራ ጀምሮ ጉዳዩ “ወዳልተፈለገ” አቅጣጫ ሊያመራ ሲል ከበላይ በተላለፈ ትዕዛዝ ምርመራው እንዲቆምና በቁጥጥር ሥር ውለው የነበሩት መሃንዲሶች እንዲፈቱ መደረጉን ለጎልጉል ከደረሱት መረጃዎች ጋር በማጣቀስ ዘግበን ነበር፡፡

ሪፖርተር ጋዜጣ ረቡዕ ባወጣው ዜና 85 የመሬት አመራሮችና ሠራተኞች ሙስና ፈጽመዋል በሚል በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን፤ ከዚሁ የመሬት አስተዳደር ጋር በተያያዘ ከአዚህ በፊት 600 ሠራተኞች ላይ ዕርምጃ መወሰዱን ዘግቦ ነበር፡፡

ሰሞኑን የጎልጉል እማኝ ዘጋቢ (ireporter) በላኩልን መረጃ መሠረት እነዚህ 600 ያህል የሚሆኑት “ኪራይ ሰብሳቢነትን” እና “ሙስናን” ለመዋጋት በሚል “ዕርጃ የተወሰደባቸው” በትንሹ ለሰባት ዓመታት በመሬት አስተዳደር በመሃንዲስነትና ተመሳሳይ ሙያ ያገለገሉ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ በተለይ ደመወዛቸው አይነካም በሚል በዝቅተኛ የሥራ መደብ ላይ እንዲመደቡ የተደረጉት በራሳቸው ፈቃድ ሥራቸውን እንዲለቁና በምትኩ አንድን ወገን ያማከለ የታማኞች ቅጥር ለመፈጸም የተሰበ እንደሆነ እማኝ ዘጋቢው ያስረዳሉ፡፡

ከመሬት አስተዳደር ጋር በተያያዘ የሚፈጸሙ ወንጀሎችና የሙስና ተግባራት እንዳሉ የሚናገሩት ዘጋቢው ውሳኔው ወገንተኛና የሥርዓቱን ቁንጮዎች የማይነካ መሆኑ አግባብነት የሌለው ብቻ ሳይሆን ሕዝብን አፍ ማስዘጊያ የማባበያ ጥገናዊ ለውጥ እንደሆነ ይጠቁማሉ፡፡

ከዚህም ሌላ ሁለት መሠረታዊ ነጥቦችን እማኝ ዘጋቢው ይጠቅሳሉ፤ አንደኛው በሚነሱት ሠራተኞች ምትክ ባለሙያ ለመመደብ በቂ ዝግጅት አለመደረጉና በቅጥር ቦታቸውን ለመተካት የሚደረገው ሙከራ ኅብረተሰቡን ለተጨማሪ እንግልት የሚዳርገው ሲሆን በሁለተኛ ደረጃ ብዙ ሚሊዮን ብር ወጪ ተደርጎበት “የካይዘን መመሪያ (ፕሪንስፕል)” ለመተግበር በሚል በየክፍለከተማው የተሰጠው ሥልጠና ለነዚሁ ከሥራቸው የተነሱት ባለሙያዎች መሆኑ ሥልጠናውን ዋጋቢስ የሚያደርግ ሲሆን በሠራተኞቹ ላይ ተወሰደ የተባለው እርምጃ ግብታዊና ፖለቲካዊ ውሳኔ እንደሆነ ይናገራሉ፡፡

ከዚህ ሁሉ በላይ የእማኝ ዘጋቢውም ሆነ የሌሎች አስተያየት ሰጪዎች ዋና ጥያቄ በሙስና የተዘፈቁትን የህወሃት ቁንጮ ባለሥልጣናትን ማነው የሚደፍራቸው የሚል ነው፡፡ “እነሱው ሙሰኛ፤ እነሱው የጸረ ሙስና ሕግ አውጪ፤ እነሱው የሕግ ተርጓሚ፤ እነሱው ፈራጅ፤ እነሱው አሳሪ፤ …” በሆኑበት አገር ዋንኞቹ የመሬት ነጣቂዎችና ከበርቴዎች ምንም ሳይሆኑ ከላይ ከላይ የሚወሰደው እርምጃ ጊዜያዊ ጥገናዊ መሻሻል እንጂ ተሃድሶአዊ ለውጥ እንደማያመጣ ይናገራሉ፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. gud says

    March 4, 2016 12:58 pm at 12:58 pm

    Abay is always clean of any corruption .

    Reply
  2. Yikir says

    March 6, 2016 06:38 pm at 6:38 pm

    Abayin yedefere jegina Meles ;Melesin yedefere ;ABEBE GELLAW SIHON ;ABEBE GELLAWIN YETEKAW ABEBE BIKILA NEW.

    Reply
  3. Solomon says

    March 24, 2016 05:41 pm at 5:41 pm

    Gud,

    I see now you are one of those members of the TPLF…. Why are you so coward to hide yourself say your name Tecklay or Kiflay no body is going to hunt you. I can tell that you are a 4th grader soldier but now a Minister.

    Reply
  4. Nimona Lammi says

    April 3, 2016 06:22 pm at 6:22 pm

    አባይ ፀሐይ ማለት የአመራር ብቃት ፣ የሥነልቦና ዝግጁነት ፣ የአካዳሚክ ዕውቀት ሳይኖረው በጫካ ውስጥ የውንብድና ተግባራት በመፈፀሙ በማሀይሞች ቡድን ላይ የነገሰ ሽፍታ እንጅ በምንም ታሀምር በኢትዮጵያ ውስጥ ወደ ሥልጣን የሚያመጣ ብቃትም ፣ ዕውቀትንም ሞራልም የሌለው መሐይም ነው ።በዚህ በዘገምተኛ እና በባዶ ጭንቅላቱ የሚፈፅማቸው የሚናገራቸው ነገሮች ከመናቅ ውጭ ምንም ልንለው አይገባንም ሰውዬው retarded (Ideot) ነው ።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule