• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ለአገር ሰላም መፍትሔው …

September 24, 2016 01:18 am by Editor 1 Comment

እኔም እንደ ዜጋ ለአገር ሰላም  አለኝ!!

ኢትዮጵያ የምትባል አገር የሁላችንም እንጂ የተወሰኑ ግለሰቦች፣ ብሔሮች፣ ጎሳ፣ ዘር፣ …. አይደለችም፡፡ የተወለድኩት በንጉሡ ዘመን ሲሆን፣ ነፍስ ያወኩትና ፊደል የቆጠርኩት በደርግ ዘመነ መንግሥት ነው፡፡ ደርግ እጅግ ክፉና ጨካኝ ወታደራዊ መንግሥት እንደ ነበር አስታውሳለሁ፡፡ ያለ ፍርድ ቤት ትእዛዝ ብዙዎች ተገድለዋል፤ ተረሽነዋል፡፡

በአንጻሩ አሁን ያለው መንግሥት ከደርግ በምን ይሻልል? ተብሎ ሊጠየቅ ይችላል፡፡

ደርግ በአርሶ አደሩና በከተሜው ሕዝብ ዘንድ አንጻራዊ በሆነ መልኩም ቢሆን ተቀባይነት ነበረው፡፡ በተለይ አገራዊ አጀንዳን በሚመለከት ሕዝቡ ከመንግሥት ጎን ቆሞአል፡፡ በ1969 ዓ.ም ትዕቢተኛው የሶማሊያ ወራሪ መንግሥት ኢትዮጵያን በወረረችበት ጊዜ ሕዝቡ አዎንታዊ ምላሽ ሰጥቶአል፡፡ ወረራውን ለመቀልበስ የሕዝቡ ድጋፍ ከደርግ መንግሥት ጋር ስለነበር በአጭር ጊዜ ውስጥ ወራሪውን ጦር ከአገር ጠራርጎ ያስወጣ ጀግና  ሠራዊት ሆ! ብሎ ተነሥቶ ገድሉን ለዓለም ሕዝቦች አሳይቶአል፡፡

ይሁን እንጂ በደርግ ዘመን የነበሩ የሠራዊቱ አባላት በጦርነት የመሰልቸት ጉዳይ እንደነበር አይካድም፡፡ በደርግ ውስጥ በነበረው ሽኩቻና መሰልቸት ምክንያት ወያኔ አጋጣሚውን ተጠቅሞ መላውን ኢትዮጵያ መቆጣጠር ቻለች፡፡ ወያኔ ለአገዛዝ እንዲመቻት በፌደራሊዝም ሰበብ ኢትዮጵያን በክልል ከፋፈለች፡፡ ዓላማው የብሔር ብሔረሰቦችን ጥያቄ መመለስ የሚል መርሐ ግብር ነበር፡፡ ሆኖም የብሔር ብሔረሰቦች ጥያቄ ተመልሶአል ማለት አያስደፍርም፡፡ የብሔሮች ጥያቄ ቢመለስ ኖሮ በአማራ፣ በኦሮሚያ፣ በደቡብ፣ በጋምቤላ እና በሌሎችም ክልሎች አሁን እየታየ ያለው ሁኔባልተከሰተ ነበር፡፡

ስለዚህ በግልፅ እንደሚታየው በወያኔ መንግሥት እና በሕዝቡ መካከል መጠነ ሰፊ ክፍተት ታቶአል፡፡ ኢትዮጵያም በአደጋ ላይ ትገኛለች፡፡ ሕዝቡ ጥያቄ አንግቦ ሆ! ብሎ ተነሥቶአል፡፡ የሕዝቡን ጥያቄ የወያኔ መንግሥት መመለስ አልቻለም፤ ወይም ደግሞ ለመመለስ ፈቃደኛ አልሆነም፡፡

ስለዚህ እኔም እንደ ዜጋ ለአገሪቱ ሰላም የመፍትሔ ሐሳብ እንደሚከተለው አቀርባለሁ፡፡

1. ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ በሁሉም የአገሪቷ ክፍሎች የታሰሩት እንዲፈቱ፤

2. የትግራይ ነጻ አውጪ ድርጅት የሚለው የወያኔ ፓርቲ ስም በአስቸኳይ መቀየር አለበት፤ ምክንያቱም ነፃ የመውጣት ዓላማ ከማን ነው? መቼ ነው? ይህ የሚያሳየው ወያኔ የራሱ ብቻ የሆነ ድብቅ ዓላማና አጀንዳ እንዳለው
አመላካች ነው፡፡

3. ወያኔ እኔ ከለሌሁ አገር ትፈርሳለች፤ ኢትዮጵያ ልክ እንደ ሶማሊያ፣ ሊቢያ፣ ሶሪያ፣ … የሽብርተኞች መፈንጫ ትሆናለች የሚለው ፕሮፓጋንዳ መቆም አለበት፤

4. ወያኔ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ መደራደር አለበት፤

5. ወያኔ የትጥቅ ትግል ላይ ከሚገኙት ጋር በድርድር ሰላም የሚፈጠርበትን መፍትሔ መፈለግ አለበት፤

6. ወያኔ እኔ ብቻ አገር አመራለሁ፤ አስተዳድራለሁ … ማለት ትክክል አይደለም፡፡ ሁሉም ኢትዮጵያዊ እንጂ ባዕድ
በአገራችን የለም፤

7. ፌደራሊዝም ለኢትዮጵያ መልካም እንደሆነ ይታመናል፡፡ ሆኖም ብሔር ተኮር የፌደራሊዝም ሥርዓት ፈርሶ መልክዓ ምድራዊ ይዘት ያለው የፌደራሊዝም ሥርዓት እንዲካሄድ መፈቀድ አለበት፤

8. አሁን ያለው የምርጫ ቦርድ ፈርሶ ገለልተኛ የሆነ የምርጫ አስፈጻሚ ኮሚሽን መቋቋም አለበት፤

9.  ወያኔ በሰላማዊ መንገድ ሥልጣኑን መልቀቅ አለበት፤

10. ሁሉንም የሚያሳትፍ የሽግግር መንግሥት መቋቋም አለበት፤ ይህ ማለት በሰላማዊ እና በትጥቅ ትግል ለሚታገሉ ሁሉ በር መከፈት አለበት፡፡ አገራዊ አጀንዳ ያላቸው ሁሉ መሳተፍ አለባቸው፡፡ ለኢትዮጵያ ሰላም ሲባል ዝቅ ማለት ያስፈልጋል፡፡

11.  አሁን በሥልጣን ላይ ለሚገኙ የወያኔ ባለ ሥልጣናት በሰላማዊ መንገድ፣ ለአገር ሰላም ሲባል ሥልጣን በመልቀቅ የሽግግር መንግሥት እንዲቋቋም ካመቻቹና ፈቃደኛ ከሆኑ ከዚህ በፊት ለፈጸሙት ወንጀል ተጠያቂ እንዳይሆኑ የደህንነት ዋስትና ሊሰጣቸው ይገባል፡፡ እስከ መቼ እየተጣላን፣ እየተብላላን፣ አንዱ ሥልጣን ሲይዝ ሌላው ወህኒ የሚጣልበት ዘመን ማብቃት አለበት፡፡

በቃ! በኢትዮጵያ ጦርነት፣ ረሃብ፣ ጥላቻ፣ የዘር ልዩነት፣ ጎሰኝነት፣ …. ታሪክ መሆን አለበት፡፡

እውነቱን ለመናገር እነዚህን ነጥቦች ተግባራዊ ማድረግ ከተቻለ ጥቅሙ ይበልጥ ለወያኔ ባለ ሥልጣናት ነው፡፡ ምክንያቱም እነዚህ ሰዎች ከአርባ ዓመታት በላይ ያለ እረፍት በፖለቲካ ሕይወት ሲሳተፉ የቆዩ ስለሆኑ ዕረፍት ያስፈልጋቸዋል፡፡ ባለትዳርና የልጆች አባት /እናት/ ናቸው፡፡ ሰላማዊ ኑሮ በመኖር ልጆቻቸውን አሳድገው ወግ ማዕረጋቸውን ማየት አለባቸው፡፡ ሥልጣንን የሙጥኝ ብሎ መያዝ አስፈላጊ አይደለም፡፡ የአምባገነን የአፍሪካ መንግሥታት የጭካኔ አሠራር በኢትዮጵያ መታየትና መደገም የለበትም፡፡ ሰላማዊ ሕይወት መኖር አለብን፡፡ የትጥቅ ትግል ያነሱ ሰዎች ጥያቄአቸው በሰላማዊ መንገድ ከተመለሰላቸው ከጫካ ምን ይሠራሉ? ይምጡ፤ ከተማ ይግቡ፡፡

ከወዳጅ ዘመድ ጋር ይቀላቀሉ፡፡

በመሠረቱ ወያኔዎች ለአስራ ሰባት ዓመታት የታገሉት ትግራይን ለመገንጠል ነበር፡፡ የትግራይ ነፃ መንግሥት የማቋቋም ሕልም ነበራቸው፡፡ ሆኖም ትግራይን ሙሉ በሙሉ ከተቆጣጠሩ በኋላ ትግራይን ብቻ መገንጠል አላረካቸውም ነበር፡፡ ለካስ መላውን ኢትዮጵያ መቆጣጠር ይቻላል የሚል አዲስ ራእይ ተከሰተላቸው፡፡ በዚህ ዓይነት ሁኔታ ተሳካላቸው፡፡

ነገር ግን ምን ለውጥ መጣ? እንጠይቅ!

ምንም ዓይነት ለውጥ አልመጣም፡፡ ወያኔ ደርግን አስወግዶ እራሱ ሌላኛው ደርግ ሆኖ መጣ! ኢትዮጵያ የምትባለውን አገር በዘር ከፋፍሎና ሰነጣጥቆ በሕዝቦች መካከል ከፍተኛ የሆነ ጥላቻ እንዲነግሥ አደረገ፡፡

እንግዲህ የቀረበውን የመፍትሔ ነጥቦች ተግባራዊ ካልሆነ በመጨረሻ ሕዝብ ማሸነፉ አይቀሬ ይሆናል፡፡ ለሚደርሰው ጥፋትና ውድመትም ተጠያቂው የወያኔ  ባለሥልጣናት ይሆናሉ፡፡ የመጨረሻ ዕድላቸው ወህኒ ቤት እንደሚሆን ምንም ጥርጥር የለኝም፡፡ ከዚህ ውጪ ግን ሥልጣን በሞኖፖል ይዤ ዘላለም እኖራለሁ ብሎ ማሰብ እጅግ ሞኝነት ነው፡፡

ሕዝቦችን አፍኖ ለዘላለም መግዛት አይቻልም፡፡ የሕዝቦች ጥያቄ በበቂ ሁኔታ መመለስ አለበት፡፡ ወያኔዎች  ይህን የመፍትሔ ሐሳብ ቢሰሙና ቢቀበሉ፣ አገር ሰላም ትሆናለች፤ ትረጋጋለች፡፡ ከዚህ ውጭ የክልል መሪዎችን መቀየር ሥር ነቀል ለውጥ አያመጣም፤ እንዲህ ማድረግ የሕዝቦችን ጥያቄ አይመልስም፡፡ ጉልቻ ቢለወዋጥ ወጥ አያጣፍጥ እንደሚባለው ዓይነት ብቻ ይሆናል፡፡

ነገር ግን ያለ ምንም ለውጥ የኢትዮጵያ ሁኔታ አሁን ባለው መልኩ እንዲቀጥል ከተፈለገ እጅግ አደገኛ ሁኔታ እንደሚከሰት ከወዲሁ እንደ ነቢይ መተንበይ ይቻላል፡፡

የመፍትሔ ሐሳቡ ተቀባይነት እንዲያገኝ ምኞቴ ነው፡፡

ደጉ ዘመን

ከአዲስ አበባ – ኢትዮጵያ

E-mail: deguzemen@gmail.com


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Takele says

    September 28, 2016 06:20 pm at 6:20 pm

    Degu Zemen

    Your opinion is appreciated . We need people like you who have positive attitude to find means and ways of aborting the worst situation created in our country . As you know this serious situation should not leave for a certain group of individuals , we all have to cooperate and unite to bring those antagonistic groups together and have valuable discussion . Let us wish our country to have a better future and good name . Our beautiful country is naturally gifted from the Almighty God . Let us make the people of Ethiopia lead a better life and see a better tomorrow . Let us make the new generation be wise , healthy and wealthy , avoid atrocity , narrowness( confined in a thin ethnic group ) selfishness , above all power monger . There are a couple of organization’s who are trying to bring peace and justice for Ethiopia , so cooperate with Peace and Justice for Africa (PJA)
    and share ideas .

    Reply

Leave a Reply to Takele Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule