• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ

May 9, 2022 08:17 am by Editor 2 Comments

የ12ኛ ክፍል የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪ ይድነቃቸዉ ተክሉ በወልቂጤ ከተማ በጉብሬ ክፍለ ከተማ አባፍሯንሷ ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ተማሪ ነዉ።

ከ10 በላይ የተለያዩ የሳይንሰና የፈጠራ ቴክኖሎጂዎች ስራ ባለቤት ሲሆን ከነዚህ የፈጠራ ስራዎች መካከል የእናቶች ጉልበትና ጊዜ ማስቀረት የሚያስችል የእንጀራ መጋገሪያ ቴክኖሎጂ ፈጥሯል።

ይህ የእንጀራ መጋገሪያ ቴክኖሎጂ እራሱ ያቦካል ፣ እራሱ ያሟሻል፣ እራሱ ይጋግራል እንዲሁም እንጀራዉ ሲደርስ እራሱ ከምጣዱ ላይ ያወጣል።

የጉራጌ ዞን ትምህርት መምሪያ ባዘጋጀዉ 3ኛዉ ዙር የሳይንስና የሒሳብ ትምህርቶች ቴክኖሎጂ ኤግዚቢሽንና ዉድድር ላይ እናቶችን ከጭስ የሚገላግለዉ የእንጀራ መጋገሪያዉና ሌሎችም በርካታ ቴክኖሎጂዎች ይዞ የቀረበዉ የአባ ፍሯንሷ ፈርጥ ይድነቃቸዉ ተክሉ በውድድሩ 1ኛ ደረጃ በመውሰድ አጠናቀዋል።

ታዳጊዉ በአዳዲስ የፈጠራ ስራዎች ላይ እና ማህበረሰቡ በስፋት የተቸገረበት ቴክኖሎጂ ለመቅረፍ ትኩረት አድርጎ በመስራት የፈጠራ እዉቀቱን እያሳደገ ይገኛል።

ከተማሪ ይድነቃቸዉ የፈጠራ ስራዎቹ መካከል አዉቶማቲክ የእንጀራ መጋገሪያ ማሽን በቅርቡ በተካሄደዉ ሀገር አቀፍ የፈጠራ ስራዎች ዉድድሮች ላይ ይዞ የቀረበ ሲሆን ይህ አዉቶማቲክ የእንጀራ መጋገሪያ ማሽኑ የ12 ሰዉን ስራ ተክቶ የሚሰራ፣ 12 ምጣድ ያለዉ ሲሆን በአንድ ሰአት ዉስጥ 460 እንጀራ መጋገር የሚችል ማሽን ነዉ።

ታዳጊዉ የፈጠራ ሰዉ 10 የአካባቢ ማህበረሰብ ችግር የሚቀርፉ የሳይንስና የፈጠራ ስራዎች ያሉት ሲሆን ከነዚህም ዉስጥ (water level indicator) በመሬት ላይ ሆነን ጣራችን ላይ ያለዉን የዉሃ ሮቶ መጠን የሚነግረን ቴክኖሎጂ ፣ አዉቶማቲክ የእንጀራ መጋገሪያ ፣ አዉቶማቲክ በር ሰዉ በሚመጣ ሰአት በራሱ ጊዜ የሚከፈት ሲሆን ሌላዉ ደግሞ ሮሆቦት ሲሆን ይህ ሮሆቦት አንድ ሰዉ የመኖሪያ ቤቱን ሴኪዩርድ ለማድረግ ቤት ዉስጥ በመቀመጥ ሮቦሆቱን በአንድ ስልክ እያንቀሳቀሰ በሌላ ስልክ ቪዲዮ ሮሆቦቱን የሚያየዉ ነገር በፎቶና በቪዲዮ መረጃ የሚሰጠን ነዉ።

ሌላዉ ከታዳጊ ይድነቃቸዉ የፈጠራ ስራዎች መካከል ቤት ዉስጥ ወይም ግቢ ዉስጥ ሰዉ ሲንቀሳቀስ የሚበራ መብራት እንዲሁም በዉሃ ዳቦ መጋገር የሚያስችል ማሽን ሲሆን ይህ ማሽን ከፍተኛ ሀይል ሳይፈልግ በዉሃ ሙቀት ዳቦ መጋገር የሚያስችል ቴክኖሎጂ ነው፣ ጸሃይ ባለ ጊዜ በሶላር በመብራትና በጎማዉ ቻርጅ የሚያደርግ መኪና ሲሆን ይህ መኪና ቤት ዉስጥ ስንሆን በመብራት፣ ጸሃይ ባለ ሰአት በሶላር እንዲሁም ረጅም መንገድ በምንጓዝበት ወቅት ከፍተኛ ፍጥነት ላይ በሚሆንበት ሰአት የፊት ጎማ መካኒካል ሲስተም ወደ ኤሌትሪካል ሲስተም በመቀየር መኪናዉን መልሶ ቻርጅ ያደርገዋል።

የእንጀራ መጋገሪያ ቴክኖሎጂ በሀገር አቀፍ ደረጃ በተካሄደዉ የፈጠራ ስራዎች ዉድድር 3ኛ ደረጃ በመያዝ አጠናቋል።

ታዳጊዉ እየሰራዉ ያለዉን የሳይንስና የፈጠራ ስራዎች የበለጠ ዉጤታማ እንዲሆን መንግስት ፣ ወላጆቹና የትምህርት ቤቱ ባለድርሻ አካላት የግብዓት ችግሮችን መቅረፍ ይኖርባቸዋል።

በመጨረሻም የእናቶች ጊዜ፣ ጉልበትና አይናቸዉ በጢስ እንዳይጠፋ የፈጠረዉን የእንጀራ መጋገሪያ ቴክኖሎጂና ሌሎችም የፈጠራ ስራዎቹ ወደ ምርት እንዲቀየር መንግስት፣ ባለሀብት፣ ዩኒቨርሲቲዎችና የተለያዩ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ትኩረት ሊሰጡት ይገባል መልክታችን ነው። (የጉራጌ ዞን ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Right Column Tagged With: mitad, ምጣድ, የእንጀራ መጋገሪያ ማሽን, ይድነቃቸዉ ተክሉ

Reader Interactions

Comments

  1. Semaneh T. Jemere says

    May 9, 2022 12:15 pm at 12:15 pm

    ውድ ጎልጉል፡

    በዛሬው እለት ይህን የፈጠራ ዜና ስታበስሩ የተሰማኝን ደስታ ስገልጽላችሁ በታላቅ ትህትና እና የኩራት ስሜት ነው። በዛሬው እለት ያልሁበት ምክንያት ትላንት May 8, 2022 የዓለም የናቶች ቀን በመሆኑ ከዚህ የበለጠ ስጦታ ለታታሪዋ እናት ምን ሊኖር ይችላል ስል እራሴን ጠየቅሁት። ለወጣቱ ፈጣሪና ተመራማሪ አድናቆተ እና ምስጋናዬን በእናቴ፤ በባለቤቴ፤በልጆቸና እህቶቼ ስም አቀርባለሁ።

    ከዚህ በማያያዝ የፈጠራው ስራ በኢትዮጵያ የሳይንስናን ቴክኖሎጂና የደረጃ መዳቢ ድርጅት እውቅና አግኝቶ ከሆነ መቸ ነው ወደ ተግባር፤ ሽያጭና ማከፋፈል የሚጀመረው እላለሁ።

    ይህ ፈጠራ የእናቶችን ድካም ብቻ ሳይሆን የሚቀንሰው፤ የደን መጨፍጨፍን የቀንሳል፤ የእናቶችን ጤንነት ያሻሽላል፤ ባህላዊ አስራርን ያዘምናልና ወደ ተግባር የሚውልበትን ቀንና ጊዜ ብታሳውቁን ደስ ይላል። የህዳሴው ግድብ ሃይል ማመንጨት በጀመረበት ጊዜ በመምጣቱ ፈጠራውን ወቅታዊ ያደርገዋል። በተለይ እኛ በዳያስፖራ የምንገኝ ሰዎች ማሽኑን እየገዛን አነስተኛ ገቢ ላላቸው እናቶች በስፖንሰርሽፕ መልክ ገዝተን ማበርከት የሚቻል ይመስለኛልና አጣርታችሁ አሳውቁን።

    ሌላው ይህ ወጣት ዓላማውን ተግባራዊ ለማድረግ የሚፈልገው እርዳታ ካለ ብታሳውቁን ብዙ መርዳት የሚፈልጉ ሰዎችና ግለሰቦች ሊኖሩ ይችላሉ። ይህ ፈጠራ በቀላሉ እንዳይታለፍና የአንድ ሳምንት ዜና ማሞቂያ ሆኖ እንዳይቀር አደራ እላለሁ። እነስታይን ፈጠራውን ወደ ተግባር በመቀየር ነው ዓለምን የቀየረው። የዚህ ወጣት ፈጠራም እንዲሁ ከተበረታታ ውጤቱና ጥቅሙ ለወጣቱ፤ ለሕዝባችንና ለሃገር ነውና እንደግፈው። እራስን በራስ የመቻል ማሳያም ነውና ቸለንዳይበላ አሁንም አደራ እላለሁ።

    ኢትዮጵያ ለማያስፈልግ ሰው ሰራሽ ጸጉር ከውጪ ለማስገባት የምታወጣውን የውጭ ምንዛሬ ሳስበው ሁሌም እቆጫለሁና ይህን ከንቱ ወጪ ወደዚህ ፈጠራ አዙራ ብታስፋፋውና በተግባር ብታውለው ምንያህል በተጠቀመች እላለህ። ይታሰብበት!
    ለጊዜው ወጣቱን እጅጉ እያደነቅሁ በርታልን እላለሁ። አመሰግናለሁ

    ሰማነህ ታምራት ጀመረ
    ኦታዋ ካናዳ May 9, 2022

    Reply
    • Editor says

      May 10, 2022 11:46 pm at 11:46 pm

      ውድ ሰማነህ ታምራት ጀመረ

      በቅድሚያ ጊዜዎን ወስደው ይህንን የመሰለ ምላሽ ስለላኩልን ከልብ እናመሰግናለን። እርስዎ እንዳሉትም ሁለቱም የዜና ዘገባዎች በጣም ጠቃሚና የሚያስደስቱ ናቸው።

      የሚያሳዝነው እጅግ መልካም እና የሚያስደስት እሴት ያላት አገራችን ብዙ ሊወራላት የሚገባ ነገር እያላት ጠላቶቻችን በሚሰጡን አጀንዳ እርስበርስ እየተናቆርን መጥፊችንን በግድ የምንደግስ መሆናችን ያሳዝናል። ሆኖ ደግሞ እንደ እርስዎ ያለ እሾኹን ብቻ ሳይሆን አበባውንም የሚያይ አንድ ሰው መገኘቱ እጅግ ተስፋ የሚሰጥ ነው።

      በእርግጥ እርስዎ በዚህ ልክ ጻፉልን እንጂ በዝምታ ደግሞ ያገራቸውን ሁኔታ የሚከታተሉና መልካሟን የሚመኙ እንደ እምነታቸው የሚጸልዩ በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠሩ እናቶች፣ አባቶች፣ እህቶችና ወንድሞች አሏት። ለዚህ ነው ኢትዮጵያ የተዓምር አገር የሆነችው።

      ለመልካሙ አስተያየትዎ በድጋሚ ልባዊ ምስጋናችንን እናቀርባለን።

      አርታኢ

      Reply

Leave a Reply to Editor Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule