• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የዛፍ ላይ እንቅልፍ!” ስደት

August 25, 2016 01:33 am by Editor Leave a Comment

የመረጃ መረቡ ከሃገር ቤት በሚሰማው የህዝብ እንቢተኝነት አመጽ ተጨናንቆ እኛንም አጨናንቆን ከርሟል። በዚህ የመረጃ ቅብብሎሽ መካከል ወደ ምሥራቅ ሳውዲ ለስራ ጉዳይ አቅንቸ ነበር። ርያድ፤ ደማም፡ ጁቤል፤ ሃፍር አልበጠንን ለአንድ ሳምንት ሳካልል ከሃገር ቤት ከሚሰማው መረጃ  እኩል በሳውዲ ዙሪያ ያሉ በርካታ ወገኖቸ የተለያዩ መረጃዎች በስልክ አድርሰውኛል። በተዘዋዎርኩባቸው ከተሞች ያገኘኋቸው ኢትዮጵያውያን ወገኖቸም የሚያመውን የስደት ህመም ሳይደምቁ አጫውተውኛል። ሁሉም አሳሳቢ ናቸው፣ ሁሉም ቢያንስ መፍትሔ ይሻሉና ዝም የማይባለውን የወገንን ድረሱልኝ ጥሪ አሳውቃችኋላሁ!

ዛሬም በተለያዩ የሳውዲ ከተሞች የተበተኑ ችግር የገጠማቸው ዜጎች መብት አስከባሪ አጥተው ሲንከራተቱ፣ ሲንገላቱና የድረሱልኝ ጥሪ እያሰሙ ነው! በአንጻሩ አዲስ ኮንትራት ውል ከሳውዲ አረቢያ ጋር ለመስማማት ደጋግሞ ሞክሮ ያልተሳካለት የኢህአዴግ መንግስት ኮንትራት ውሉን ለማሳካት እየተሯሯጠ መሆኑን ከሪያድ ኢምባሲ ሁነኛ መረጃ ደርሶኛል። ይህ እየተሰራ ባለበት በሳውዲ በባህር መጥተው ለከፍተኛ አደጋ የተጋለጡትን መከራ መስማት ይከብዳል፣ ጋዜጠኛ ግሩም ተ/ኃይማኖት ከየመን በየመን በኩል በሚደረገው በሳውዲ መዳረሻ በመንገዱ ያለውን አሰቃቂ ሁኔታ እፍታ እፍታውን ደጋግሞ ገልጾታልና ደግሜ አላሰለቻችሁም! ብቻ መከረኞቸን መታደግ ሳይቻለን በመቀረቱ አልመች ብሏቸው እንጀራ ፈልገው በየመን የሚጎርፉት ዜጎች “መከራውን እያወቁት መርጠው የመጡት ነው! ይበላቸው!” የሚል ሰብዕና የጎደለው የጨካኝ ምክንያት እየሰጠን ለመርዳት ከመደገፍ መሸሽን መርጫችን አድርገናል! … ያሳዝናል!

የባህርተኞቹ ጉዳይ ይሁን ቢባል፣ ህጋዊ በተባለው በኮንትራት ስራ ሳይደራጁ “በተደራጁት” ኤጀንሲዎች መጥተው በተለያዩ የሳውዲ ከተሞች የተበተኑት እህቶች ጉዳይ አሳሳቢ ከሆነ ከራርሟል። በኮንትራት በሚሰሩባቸው የአረብ ቤቶች በስራ ጫና፣ በሚደርስባቸው በደል፣ በሕመምና በጭንቀት፣ ብሎም “የተሻለ እናገኛለን” ብለው ከአሰሪዎች የጠፉና “የተሻለ ስራ እናስገባለን!” በሚሉ ሆድ አደር ደላሎች የተፈናቀሉ አብዛኛው እህቶች ቁጥር እጅግ በጣም ከፍተኛ እንደሆነ ይነገራል! አንድ በኩባንያው ስራዬ በኩል በቅርብ የማውቀው ለፖስፖርት ጽ/ቤት መረጃ ቅርብ የሆነ ሳውዲ ከፍተኛ ኃላፊ በኮንትራት መጥተው ከአሰሪዎቻቸው የጠፉ “ሁሩብ” ተብለው የተመዘገቡ ኢትዮጵያን ቁጥር ወደ 60 እና 70 ሽህ እንደሚገመት አጫውቶኛል። ለእኒህ ከአሰሪዎቻቸው የጠፉ  ወገኖች መካከል በጠፉበት ሆነው ኑሮን በስደት ሲገፉ ጥቂት የማይባሉ “ህገወጥ” መሆናቸው ሳያስፈራቸው ቤት ይዘው፣ ትዳር መስርተው፣ ልጅ ወልደው የሚገኙት ቁጥር ቀላል አይደለም ።

“የዛፍ ላይ እንቅልፍ!” ስደት

አደጋው የደላ ቤት ይዘው፡ ትዳር መስርተው፤ ቀን መዳር መኳሉ ልጅ መውለዱ አይደለም። የሞቀው ሲበርድ፤ አፍላው አልፎ፤ የእውነቱ ኑሮ ሲጀመር ኑሮን በሃላፊነነት የመግፋቱ ክብደት የመጣ ጊዜ ነው ፍተናው! ሞልቶ የማይሞላው “የዛፍ ላይ እንቅልፍ” callየስደቱን ኑሮ እንዳሰቡት አልሰምር ሲል ደግሞ ከላጤዎች ይልቅ ቤተሰብ መስርተውና በስደቱ  የልጅ ፍሬ በረከት ለታደሉት መከራው የከፋ ይሆናል። በስቃይ፣ መከራው፣ በእምነት ክህደት፣ ውስብሰቡ ህይወት ያመጧልቸው የስደት ፍሬ ልጆቻቸው ደግሞ የመከራው ገፈት ቀማሽ ይሆናሉ! ነገሮች ይወሳቡባቸዋል! … ታዲያ  “የመጣ ይምጣ ወደ ሃገር እንግባ፣ የስደቱን ኑሮ ይብቃን!” ብለው ወደ ሐገር መግባት የፈለጉ ቀን ለከፋ ስቅየት ይዳረጋሉ …!

በተለይም ከአስሪዎቻቸው ጠፍተው ከርመዋልና ጠፉ ወይም “ሁሩብ” ተብለው በፓስፖርት መ/ቤት የሚፈለጉት ወደ ሐገር ለመግባት ሲፈልጉ ጣጣው የከፋ ሆኗል። በተለያዩ የሳውዲ ከተሞች ወደ ሃገር ለመግባት ፈልገው የሚይዛቸው እና የሚሸኛቸው አካል አጥተው ወደ እስር ቤት አስገብተን ወደ ሃገር እንልካለን በሚሉ የራሳችን ዜጎች ደላሎች ከፍተኛ ገንዘብ ከስክሰው እስር ቤት ከገቡ በኋላ ለወራት በእስር ቤት እየማቀቁ ያሉት ቁጥር ቀላል አይደለም። ከዚ በታጓዳኝ ለደላላ የሚሰጥ ገንዘብ የሌላቸው ይዞ በእስር ቤት በኩል ወደ ሃገር ቤት የሚልካቸው ፖሊስ አጥተው የሚንክተቱ ቁጥር እጅግ ከፍ ያለ መሆኑን ተመለክቻለሁ። በሌላ በኩል ከአሰሪዎቻቸው ሳይጠፉ “ኑሮው በቃኝ” ያሉ ጊዘ ወደ ሃገር ለመግባት ፈልገው ፈቃድ ከአሰሪዎቻቸው የማይሰጣቸው፤ የመውጫ ቪዛ ለማስመታት ከፍተኛ ገንዘብ በመጠየቃቸው እጃቸው ለፖሊ ሰጥተው መያዙ የቀናቸው እስር ቤት ከገቡ በኋላ በወህኒ መጉላላት እ ደሚደርስባቸው መረጃዎች ደርሰውኛል። ወደ ሃገር ቤት ለመግባት ፈልገው የተያዙት እና ሳይፈልጉ በቤት ለቤት ሰበራ ፍተሻ ተይዘው እስር ቤት የተወረዎሩት ከወራት በኋላ እንኳ ወደ ሀገረቸው ለመግባት የከፋ  እንግልት እንደሚደርስባቸው በዝርዝር አጫውተውኛል!

በከፋ አደጋ ላይ ስለመሆናቸው የገለጹልኝ ህጻናትን የያዙ እናቶች ወደ ሀገር ለመግባት ቢፈልጉም ከነገ ዛሬ እየተባሉ ለወራት በወህኒ ሲቆዩ በስቃይ ላይ መሆኑን አጫውተውኛል። ወ ደ ሃገር ቤት እንግባ ብለው እጃቸው የሰጡ በማናቸውም መንገድ ወደ እስር ቤት የገቡ የኮንትራት ሰራተኞች በተደጋጋሚ ባደረሱኝ  መረጃ ህጻናት ፤ ነፍሰ ጥሩዎችና አቅመ ደካማ የአእምሮ ህመምተኞች የሚቀይሩት የረባ ልብስ፤ ምግብና ንጹህ መጠጥ በበቂ ሁኔታ እንደማያገኙ ገልጸውልኛል። ነፍሰ ጥሩዎችና የአእምሮ መታዎክ የደረሰባቸው እህቶች መኖራቸውን ከእስር ቤት መረጃ ያቀበሉኝ እኒህ ወገኖች ሌላው ቀርቶ የጅዳ ቆንስልና የሪያድ ኢንባሲ ተወካዮች ልባቸው ለህጻናቱ ራርቶ ወተትና መጸዳጃ እንዲያገኙ እንደማያደርጉ ጠቁመው የተገፊ ድምጻቸውን እንዳሰማ አደራ ብለውኛል! ሙሉና ዘርዘር ያለውን በድምጽና ምስል የተላከልኝን ጠልቆ የሚያመውን የድረሱልኝ መልዕክት መረጃ ዛሬ አላቀርበውም ፤ ብቻ ድምጻቸው ይሰማ ዘንድ እነሆ ደረሰብን የሚሉትን መረጃው እንዲህ አቀብላቸኋለሁ!

ቸር ያሰማን!

ነቢዩ ሲራክ
ነሐሴ 18 ቀን 2008 ዓም

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions, Social Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule