• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የዛፍ ላይ እንቅልፍ!” ስደት

August 25, 2016 01:33 am by Editor Leave a Comment

የመረጃ መረቡ ከሃገር ቤት በሚሰማው የህዝብ እንቢተኝነት አመጽ ተጨናንቆ እኛንም አጨናንቆን ከርሟል። በዚህ የመረጃ ቅብብሎሽ መካከል ወደ ምሥራቅ ሳውዲ ለስራ ጉዳይ አቅንቸ ነበር። ርያድ፤ ደማም፡ ጁቤል፤ ሃፍር አልበጠንን ለአንድ ሳምንት ሳካልል ከሃገር ቤት ከሚሰማው መረጃ  እኩል በሳውዲ ዙሪያ ያሉ በርካታ ወገኖቸ የተለያዩ መረጃዎች በስልክ አድርሰውኛል። በተዘዋዎርኩባቸው ከተሞች ያገኘኋቸው ኢትዮጵያውያን ወገኖቸም የሚያመውን የስደት ህመም ሳይደምቁ አጫውተውኛል። ሁሉም አሳሳቢ ናቸው፣ ሁሉም ቢያንስ መፍትሔ ይሻሉና ዝም የማይባለውን የወገንን ድረሱልኝ ጥሪ አሳውቃችኋላሁ!

ዛሬም በተለያዩ የሳውዲ ከተሞች የተበተኑ ችግር የገጠማቸው ዜጎች መብት አስከባሪ አጥተው ሲንከራተቱ፣ ሲንገላቱና የድረሱልኝ ጥሪ እያሰሙ ነው! በአንጻሩ አዲስ ኮንትራት ውል ከሳውዲ አረቢያ ጋር ለመስማማት ደጋግሞ ሞክሮ ያልተሳካለት የኢህአዴግ መንግስት ኮንትራት ውሉን ለማሳካት እየተሯሯጠ መሆኑን ከሪያድ ኢምባሲ ሁነኛ መረጃ ደርሶኛል። ይህ እየተሰራ ባለበት በሳውዲ በባህር መጥተው ለከፍተኛ አደጋ የተጋለጡትን መከራ መስማት ይከብዳል፣ ጋዜጠኛ ግሩም ተ/ኃይማኖት ከየመን በየመን በኩል በሚደረገው በሳውዲ መዳረሻ በመንገዱ ያለውን አሰቃቂ ሁኔታ እፍታ እፍታውን ደጋግሞ ገልጾታልና ደግሜ አላሰለቻችሁም! ብቻ መከረኞቸን መታደግ ሳይቻለን በመቀረቱ አልመች ብሏቸው እንጀራ ፈልገው በየመን የሚጎርፉት ዜጎች “መከራውን እያወቁት መርጠው የመጡት ነው! ይበላቸው!” የሚል ሰብዕና የጎደለው የጨካኝ ምክንያት እየሰጠን ለመርዳት ከመደገፍ መሸሽን መርጫችን አድርገናል! … ያሳዝናል!

የባህርተኞቹ ጉዳይ ይሁን ቢባል፣ ህጋዊ በተባለው በኮንትራት ስራ ሳይደራጁ “በተደራጁት” ኤጀንሲዎች መጥተው በተለያዩ የሳውዲ ከተሞች የተበተኑት እህቶች ጉዳይ አሳሳቢ ከሆነ ከራርሟል። በኮንትራት በሚሰሩባቸው የአረብ ቤቶች በስራ ጫና፣ በሚደርስባቸው በደል፣ በሕመምና በጭንቀት፣ ብሎም “የተሻለ እናገኛለን” ብለው ከአሰሪዎች የጠፉና “የተሻለ ስራ እናስገባለን!” በሚሉ ሆድ አደር ደላሎች የተፈናቀሉ አብዛኛው እህቶች ቁጥር እጅግ በጣም ከፍተኛ እንደሆነ ይነገራል! አንድ በኩባንያው ስራዬ በኩል በቅርብ የማውቀው ለፖስፖርት ጽ/ቤት መረጃ ቅርብ የሆነ ሳውዲ ከፍተኛ ኃላፊ በኮንትራት መጥተው ከአሰሪዎቻቸው የጠፉ “ሁሩብ” ተብለው የተመዘገቡ ኢትዮጵያን ቁጥር ወደ 60 እና 70 ሽህ እንደሚገመት አጫውቶኛል። ለእኒህ ከአሰሪዎቻቸው የጠፉ  ወገኖች መካከል በጠፉበት ሆነው ኑሮን በስደት ሲገፉ ጥቂት የማይባሉ “ህገወጥ” መሆናቸው ሳያስፈራቸው ቤት ይዘው፣ ትዳር መስርተው፣ ልጅ ወልደው የሚገኙት ቁጥር ቀላል አይደለም ።

“የዛፍ ላይ እንቅልፍ!” ስደት

አደጋው የደላ ቤት ይዘው፡ ትዳር መስርተው፤ ቀን መዳር መኳሉ ልጅ መውለዱ አይደለም። የሞቀው ሲበርድ፤ አፍላው አልፎ፤ የእውነቱ ኑሮ ሲጀመር ኑሮን በሃላፊነነት የመግፋቱ ክብደት የመጣ ጊዜ ነው ፍተናው! ሞልቶ የማይሞላው “የዛፍ ላይ እንቅልፍ” callየስደቱን ኑሮ እንዳሰቡት አልሰምር ሲል ደግሞ ከላጤዎች ይልቅ ቤተሰብ መስርተውና በስደቱ  የልጅ ፍሬ በረከት ለታደሉት መከራው የከፋ ይሆናል። በስቃይ፣ መከራው፣ በእምነት ክህደት፣ ውስብሰቡ ህይወት ያመጧልቸው የስደት ፍሬ ልጆቻቸው ደግሞ የመከራው ገፈት ቀማሽ ይሆናሉ! ነገሮች ይወሳቡባቸዋል! … ታዲያ  “የመጣ ይምጣ ወደ ሃገር እንግባ፣ የስደቱን ኑሮ ይብቃን!” ብለው ወደ ሐገር መግባት የፈለጉ ቀን ለከፋ ስቅየት ይዳረጋሉ …!

በተለይም ከአስሪዎቻቸው ጠፍተው ከርመዋልና ጠፉ ወይም “ሁሩብ” ተብለው በፓስፖርት መ/ቤት የሚፈለጉት ወደ ሐገር ለመግባት ሲፈልጉ ጣጣው የከፋ ሆኗል። በተለያዩ የሳውዲ ከተሞች ወደ ሃገር ለመግባት ፈልገው የሚይዛቸው እና የሚሸኛቸው አካል አጥተው ወደ እስር ቤት አስገብተን ወደ ሃገር እንልካለን በሚሉ የራሳችን ዜጎች ደላሎች ከፍተኛ ገንዘብ ከስክሰው እስር ቤት ከገቡ በኋላ ለወራት በእስር ቤት እየማቀቁ ያሉት ቁጥር ቀላል አይደለም። ከዚ በታጓዳኝ ለደላላ የሚሰጥ ገንዘብ የሌላቸው ይዞ በእስር ቤት በኩል ወደ ሃገር ቤት የሚልካቸው ፖሊስ አጥተው የሚንክተቱ ቁጥር እጅግ ከፍ ያለ መሆኑን ተመለክቻለሁ። በሌላ በኩል ከአሰሪዎቻቸው ሳይጠፉ “ኑሮው በቃኝ” ያሉ ጊዘ ወደ ሃገር ለመግባት ፈልገው ፈቃድ ከአሰሪዎቻቸው የማይሰጣቸው፤ የመውጫ ቪዛ ለማስመታት ከፍተኛ ገንዘብ በመጠየቃቸው እጃቸው ለፖሊ ሰጥተው መያዙ የቀናቸው እስር ቤት ከገቡ በኋላ በወህኒ መጉላላት እ ደሚደርስባቸው መረጃዎች ደርሰውኛል። ወደ ሃገር ቤት ለመግባት ፈልገው የተያዙት እና ሳይፈልጉ በቤት ለቤት ሰበራ ፍተሻ ተይዘው እስር ቤት የተወረዎሩት ከወራት በኋላ እንኳ ወደ ሀገረቸው ለመግባት የከፋ  እንግልት እንደሚደርስባቸው በዝርዝር አጫውተውኛል!

በከፋ አደጋ ላይ ስለመሆናቸው የገለጹልኝ ህጻናትን የያዙ እናቶች ወደ ሀገር ለመግባት ቢፈልጉም ከነገ ዛሬ እየተባሉ ለወራት በወህኒ ሲቆዩ በስቃይ ላይ መሆኑን አጫውተውኛል። ወ ደ ሃገር ቤት እንግባ ብለው እጃቸው የሰጡ በማናቸውም መንገድ ወደ እስር ቤት የገቡ የኮንትራት ሰራተኞች በተደጋጋሚ ባደረሱኝ  መረጃ ህጻናት ፤ ነፍሰ ጥሩዎችና አቅመ ደካማ የአእምሮ ህመምተኞች የሚቀይሩት የረባ ልብስ፤ ምግብና ንጹህ መጠጥ በበቂ ሁኔታ እንደማያገኙ ገልጸውልኛል። ነፍሰ ጥሩዎችና የአእምሮ መታዎክ የደረሰባቸው እህቶች መኖራቸውን ከእስር ቤት መረጃ ያቀበሉኝ እኒህ ወገኖች ሌላው ቀርቶ የጅዳ ቆንስልና የሪያድ ኢንባሲ ተወካዮች ልባቸው ለህጻናቱ ራርቶ ወተትና መጸዳጃ እንዲያገኙ እንደማያደርጉ ጠቁመው የተገፊ ድምጻቸውን እንዳሰማ አደራ ብለውኛል! ሙሉና ዘርዘር ያለውን በድምጽና ምስል የተላከልኝን ጠልቆ የሚያመውን የድረሱልኝ መልዕክት መረጃ ዛሬ አላቀርበውም ፤ ብቻ ድምጻቸው ይሰማ ዘንድ እነሆ ደረሰብን የሚሉትን መረጃው እንዲህ አቀብላቸኋለሁ!

ቸር ያሰማን!

ነቢዩ ሲራክ
ነሐሴ 18 ቀን 2008 ዓም

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions, Social Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule