የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ወርቅነህ ገበየሁ በፓልቶክ ክፍል ቀርቦ የኦሮሞ ተወላጅ መሆኑን አስረግጦ ተናግሯል። ካፈርኩ አይመልሰኝ ነገር። አንድ ሰው ከመሬት ተነስቶ ከዚህ ዘር ነኝ የማለት የተጠበቀ ነው። የዘር ቆጠራን ያመጡት ራሳቸው ስልጣን ላይ ያሉት ዘረኞች ናቸው እንጂ እኛ አይደለንም። ዛሬ የራሳቸው ቃል እስረኛ የሆኑ ይመስላል። ጥያቄው ዘሩን በገዛ ፈቃዱ የመቀየር ጉዳይ አይደለም። ተቃውሞው ሹመቱ ላይም አይደለም። በዘር ያመጡት የስልጣን ኮታ ዘሩ ባልሆነ ግለሰብ ሲደለደል - ጉዳዩን ለሚያውቁት ንቀት እና ስድብ ይሆናል። ወርቅነህ የኦሮሞ የገዳ ሥርዓት በሚፈቅደው "ጉዲፈቻ" እና "ሞጋሳ" ባህል መሰረት ወደ ኦሮሞነት ተቀይሮ ከሆነ ግልጽ ይሁን። ካልሆነ ግን የእሱን ማንነት የሚገልጸው ዶክመንት ተመልክቶ ፍርድ መስጠቱ ይበጃል። ለስድስት ዓመታት በድህንነት ሲሰራ በርካታ ንጹሃን … [Read more...] about የወርቅነህ ገበየሁ ወልደኪዳን “ነገዎ” ማንነት
Archives for November 2016
የኢትዮጵያን ወቅታዊ ችግርና የመፍትሄ አቅጣጫ በሚመለከት የተሰጠ መግለጫና የሰላም ጥሪ
የኢትዮጵያን ችግር የመፍትሄ መንገድ በሚመለከት "ኢትዮጵያን ለማዳን እንነጋገር" በሚል ርእስ ቀደም ሲል አንድ የሰላም ጥሪ ማቅረባችንን እናስታውሳለን። መልእክቱም ባጭሩ ይህች ታላቅ ሀገር የገጠማት ችግር ሊፈታ የሚችለው በመሪዎቿና በልዩ ልዩ የተቃውሞ ጎራ በተሰለፉ የራሷ ልጆች ብቻ መሆኑን፤ መፍቻ መንገዱም ውይይትና ንግግር መሆኑን፤ ጊዜውም አሁን መሆኑን የሚያመላክት ነበር። ለዚህም ሁሉም ወገኖች ቢያንስ በችግሩ ላይ ለመነጋገር መስማማት እንዳለባቸው በመጠቆም ለሰላማዊ ውይይት እንዲተባበሩና ሃሳባቸውን እንዲገልፁልን አሳስበንም ነበር። ጥሪውን የተመለከቱ ድርጅቶችና ግለሰቦች የሰጡንን በጎ ምላሽና ማበረታቻ በምስጋናና በአክብሮት ተቀብለናል፤ ደስ ብሎናልም። የሰላም ውይይት ወደሰላም በር የሚወስድ ጠቃሚ ስልት መሆኑን በማመን ድርጅታችን ላቀረበው የውይይት መድረክ ዝግጅት ሃሳብ … [Read more...] about የኢትዮጵያን ወቅታዊ ችግርና የመፍትሄ አቅጣጫ በሚመለከት የተሰጠ መግለጫና የሰላም ጥሪ
“የታሪክ ሂሳብ ማወራረዱን አቁሙ!” ፕ/ር መረራ ጉዲና
"በውይይት የማይፈታ ችግር የለም። ስትወያዩ ግን የታሪክ ሂሳብ ማወራረዱ ላይ አታተኩሩ። ትኩረታችሁን አሁን የተጋፈጥናቸው ችግሮች ላይ አድርጉ።" ሲሉ ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና አስታወቁ። ፕሮፌሰሩ ይህንን የገለጹት በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ በኔዘርላንድ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያ ጋር በትላንትናው እለት 20 November 2016 በአምስተርዳም ባደረጉት ውይይት ላይ ነው። በውይይቱ የኦሮሞ አክቲቪስቶችም ተገኝተው ሃሳባቸውን አካፍለዋል። ስለ ሃገሪቱ ፈታኝ ሁኔታ እና ስለወደፊቱ እጣ ፈንታ በስፋት ያብራሩት የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ መሪ - ፕ/ር መረራ ጉዲና ከተሰብሳቢው ለቀረቡላቸው በርካታ ጥያቄዎችም ምላሽ ሰጥተዋል። "አዋጁ እና ኮማንድ ፖስቱ ሕዝባዊ አመጹን ያበርደዋል ወይ?" ተብለው ሲጠየቁ፣ ሃገሪቱ አሁን በመስቀለኛ መንገድ ላይ መሆንዋን ገልጸው አሁን ያለው ሁኔታ ላይ እንዲህ … [Read more...] about “የታሪክ ሂሳብ ማወራረዱን አቁሙ!” ፕ/ር መረራ ጉዲና
ጎሠኛነት በባዶ ሜዳ!
በተለያዩ የኢትዮጵያ አንገብጋቢ ጉዳዮች ላይ ሁሉ የሚደረገው ውይይትና ክርክር እንደተጠናቀቀ ተቆጥሮ የአማራና የኦሮሞ ጎሠኛነት ትልቁ አንገብጋቢ ጉዳይ እየሆነ ነው፤ (ስለ ኢትዮጵያ ለማያውቅ ሰው በኢትዮጵያ ውስጥ ከጠሩና ከጸዱ አማራና ኦሮሞዎች በቀር በአገሪቱ ውስጥ ሌላ ሰው ያለ አይመስልም!) ጎሠኛነት ጉዳያችን ያልሆነው ኢትዮጵያውያን የዳር ተመልካች መሆኑ እየሰለቸን ነው፤ ምንም እንኳን አማራና ኦሮሞ የተባሉት ጎሣዎች በብዛት ከሁሉም ቢበልጡም ከሰማንያ በላይ የሚሆኑ ጎሣዎች እንደሌሉና በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ ቃል እንደሌላቸው ተደርጎ የሚጎነጎነው የሚስዮናውያንና የስለላ ድርጅቶች ታሪክ ለኢትዮጵያውያን ባዕድ ነው፡፡ ሌላው የሚያስደንቀውና ዓይን ያወጣው ነገር እነዚህ ኢትዮጵያን በጠዋቱ ለመቃረጥ እየተነታረኩ ያሉ በአማራና በኦሮሞ ጎሣዎች ስም መድረኩን የያዙት ሰዎች በውጭ አገር … [Read more...] about ጎሠኛነት በባዶ ሜዳ!
የአሜሪካ ምርጫ:- ዶናልድ ትረምፕ ወይስ ሂለሪ ክሊንተን?
መግቢያ የዛሬ ስምንት ዐመት ባራካ ኦባማ ለፕሬዚደንትነት ምርጫ ለውድድር ሲቀርቡ፣ ከፕሪመሪው ጀምሮ የነበረውን የምርጫው ሂደት እዚህ አውሮፓ ሆነን በየሰዓቱ ሁኔታውን በጥብቅ እንከታተል ነበር። በማያጠራጥር መልኩ የብዝዎቻችን ፍላጎትና አድልዎ ለባራክ ኦባማ ቢሆንም፣ ባራክ ኦባማ ያንን አስቸጋሪ የፕሪመሪ ውድድር አልፈውና ተፎካካሪዎቻቸውን አሸንፈው የዲሞክራቲክ ፓርቲውን በመወከል ለፕሬዚደትነት ምርጫ ይቀርባሉ ብሎ የገመተ አልነበረም። የመጨረሻ መጨረሻ ወይዘሮ ሂለሪ ክሊንተን በአሸናፊነት በመውጣት ፓርቲያቸውን በመወከል የሪፓብሊካን ፓርቲን ከሚወክለው ጋር ለውድድር ይቀርባሉ የሚል ግምት ነበረን። አሁንም ቢሆን የኢንስቲቱሽናል ሬሲዝምነትና አጠቃላይ ሬሲዝምነት በነገሰበት በአሜሪካን ህብረተሰብ ውስጥ አንድ ጥቁር አሜሪካዊ ለፕሬዜደንትነት ምርጫ በመወዳደር በአሸናፊነት ይወጣል ብሎ … [Read more...] about የአሜሪካ ምርጫ:- ዶናልድ ትረምፕ ወይስ ሂለሪ ክሊንተን?
The changing face of Ethiopia
The US elections are over and I have not met anyone happy with the outcome. All the dirty linen was washed in public and the winner was the one with the most stain. The opinion polls malfunctioned spectacularly. I followed the election process as told by what is called the ‘liberal’ media. Huffington Post, Slate, The New Yorker among many convinced me it was going to be a ride in the park for Secretary Clinton. HP even gave the Democrats a 91.5% percent of winning the Presidency. In case you … [Read more...] about The changing face of Ethiopia
“ነጻነት ሰው ከመሆን የሚገኝ መብት ነው”
ግዛው ለገሰ በጣም መሠረታዊና አንገብጋቢ፣ ጊዜያዊም ጉዳዮችን አንሥቷል፤ በበኩሌ ጉዳዮቹን በማንሣቱ በጣም እያመሰገንሁት አስተያየቴን በአጭሩ እንደሚከተለው አቀርባለሁ፡፡ ‹‹ህወሓት የተቋቋመው በአማራ ጥላቻ ነው፡፡ ይህን ሀቅ ሳይቀበሉ ስለነፃነት ማታገል አይቻልም፡፡ ነፃነት ደግሞ የዜግነት መበት እንጂ የወል መብት አይደለም፡፡ ነፃነት በማንነት ትግል አይገኝም፡፡›› ግዛው በጣም መሠረታዊ ነጥብና ሀሳብ አቅርበሃል፤ ነገር ግን ድብልቅልቁ ወጣብኝ! መነሻ፡--‹‹ሕወሀት የተቋቋመው በአማራ ጥላቻ (ላይ?) ነው፤›› ከዚህ ትነሣና፡-- ‹‹ይህንን ሀቅ ሳይቀበሉ ስለነጻነት ማታገል (መታገል?) አይቻልም፤›› ትላለህ፡፡ እንደምረዳው ግልጽ ያልሆነልኝ ግዛው ሁለቱን ዓረፍተ ነገሮች እርስበርሳቸውና እያንዳንዳቸውን ከነጻነት ጋር ያቆራኛቸው እንዴት ነው? የሚል ነው፤ በእኔ አስተሳሰብ ምንም … [Read more...] about “ነጻነት ሰው ከመሆን የሚገኝ መብት ነው”
ኢህአዴግ ሲጨንቀው “አደገኛ ቦዘኔዎችን” ለስለላ እየመለመለ ነው
ሕዝባዊ ቁጣ ያንቀጠቀጠው ህወሃት/ኢህአዴግ በተለምዶ “የሰፈር ጉልበተኛ” የሚባሉ ወጣቶችን ለስለላ ስራ እየመለመለ እንደሆነ ተሰማ። ጥያቄውን ተቀብለው በየሰፈሩ ያሉትን የለውጥ አራማጆች ለመሰለል ፈቃደኛ ያልሆኑ እንደሚታሰሩ ለማወቅ ተችሏል። ከታሰሩት መካከል ከማዕከላዊ የተሰወረው ወጣት ጉዳይ በጥበቃ የተሰማሩትን ችግር ውስጥ ከቷቸዋል። አዲሱ ምልመላ የቀበሌ የስለላ መዋቅር መሰበሩን አመላካች እንደሆነ ተጠቁሟል። የጎልጉል የአዲስ አበባ ዘጋቢ ዋቢዎቹን ጠቅሶ እንደዘገበው ኢህአዴግ ቀደም ሲል “አደገኛ ቦዘኔ” ሲላቸው የነበረውን ወጣቶች ለስለላ ተግባር እየመለመለ ነው። የሚመለመሉት በሰፈር ውስጥ በተደባዳቢነት፣ በጉልበተኛነት የሚታወቁ ናቸው። በየሰፈሩ በተለምዶ “ጉልቤ” የሚባሉትን ወጣቶች የሚመለምሉት የህወሃት ሰዎች ናቸው። አመላመሉ በድንገት ከሚያዘወትሩበት ቦታ ወይም ከመንገድ … [Read more...] about ኢህአዴግ ሲጨንቀው “አደገኛ ቦዘኔዎችን” ለስለላ እየመለመለ ነው
“HILLARY WINS” መስፍን በዙ
* የጅብ ችኩል … መቸም ይህ የአሜሪካ ምርጫ ከቅስቀሳው እስከ ትራምፕ ምርጫ ትዝታው ብዙ ነው፣ በመጨረሻው ቀንና በምርጫው ውጤት ቀን የሆንነው ግን በጣም ያጓጓና ልዩ ትዝታ ይዞ ያለፈ አጋጣሚ ነው፣ ለብዙዎቻችን ... የማልረሳውን የእኔን ትዝታ ከትዝብት ጋር ላጋራችሁ ... "እውነትን እንጂ ውሸትን አናስተናግድም!" የሚል መርህን ይዘው ከሚንቀሳቀሱት የቲጂ ቲቪ አዘጋጅ ጋዜጠኛ መስፍን በዙ "HILLARY WINS" "ሄለሪ አሸነፈች!" የሚል አንድ አስገራሚ ሰበር መረጃ ከሌሊት 3:34 Am ተሰራጭቶ ደረሰኝ። HILLARY WINS ከሚለው መረጃ ስር "ቲጂ ቴሌቪዥን ጠዋት ላይ የምርጫ ጣቢያዎቹን ጎብኝቶ ባገኘው መረጃ መሰረት ሄለሪ የአሜሪካ 45ኛ ፕሬዚደንት ሆነው ተመርጠዋል" በሚል የሚያትተው መረጃ አስገራሚ ነበር፣ መረጃው ለሄለሪ ደጋፊ ደስታ፣ ለትራምፕ ደጋፊ ሀዘንም ነበር ... … [Read more...] about “HILLARY WINS” መስፍን በዙ
ይድረስ ለጀዋር መሃመድ
Brotherly advice to Ethiopian Friends በሚል ርእስ በፌስቡክ ገጽህ ለኢትዮጵያውያን ወንድሞችህ የሰጠህውን ምክር አነበብኩት። ጽሁፍህን ሳነብ የመጀመሪያ ባለመሆኑና በፌስቡክ አስተያየቶችህ ላይ ስለምከታተልህም ሃሳብህን ለመረዳት ብዙም አልቸገረኝም። በተለይ ወጣት ኢትዮጵያውያን ወደ ከፍተኛ የፖለቲካ አስተሳሰብ መድረክ መምጣት ለሃገራችን የሚኖረውን ዘላቂ ጠቀሜታ የምገነዘብ በመሆኑ ጀዋር የፖለቲካ ተንታኙ ወጣት እየተባለ በተለያዩ ሚዲያዎች ላይ ቀርበህ ሃሳብ ስትሰጥ ከአምስትና ስድስት አመት በላይ አውቅሃለሁ። ወጣቱ ጀዋር በዚሁ ከቀጠለ በሃገራችን ኢትዮጵያ ጥሩ ፖለቲከኞችን ልናፈራ እንችላለን የሚል ጽኑ እምነት ነበረኝ። በተለይም የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦች ችግር የሚፈታው በኢትዮጵያ ዲሞክራሲ ፍትህ እና እኩልነት የሚያመጣ ስርአት በመገንባት ነው። የኦሮሞም … [Read more...] about ይድረስ ለጀዋር መሃመድ