የመድረክና የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ፓርቲ መሪ ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና ዛሬ ረቡእ ማምሻውን በደህንነት ሃይሎች ታፍነው መወሰዳቸውን ለማረጋገጥ ችለናል። በዛሬው እለት ፕ/ር መረራ ጉዲና መኖርያ ቤት በደህንነቶች እና ከባድ መሳርያ በታጠቁ የአጋዚ አባላት ተከብቦ መዋሉን የአይን እማኞች ገልጸዋል። ብእር ብቻ ለያዘ አንድ ሰላማዊ ሰው ይህን ሁሉ ሃይል ማሰማራት ስርዓቱ ምን ያህል እንደተብረከረከ የሚያሳይ መሆኑን እማኞቹ ጨምረው ገልጸዋል። በአውሮፓ ህብረት ጥሪ ተደርጎላቸው ሃገሪቱ ስላለችበት መስቀለኛ መንገድ ገለጻ አድርገዋል። ከዚያም በሆላንድ፣ በጀርመን እና በስዊዘርላንድ ከሚገኙ ኢትዮጵያውያን ጋር ስለ ሃገሪቱ ሁኔታ መወያየታቸው ይታወሳል። የኢትዮጵያ ችግር በሰላማዊ መንገድ መፍትሄ ያገኛል ብለው በምርጫ እና በሰላማዊ አግባብ ሲታገሉ የነበሩት ፕ/ር መረራ ጉዲና ለምን እንደታፈኑ … [Read more...] about ፕ/ር መረራ ጉዲና ታፍነዋል
Archives for November 2016
ዲያስጶራዎቻችን
ዲያስፖራ (ዲያስጶራ) የሚለው ቃል ትርጉም ‹‹ብትን /የተበተነ›› ወይም በአጪር አነጋገር ከትውልድ አገሩ ውጭ ተበታትኖ ያለ ሕዝብ ማለት ነው፡፡ በዚህ ትርጓሜ ከኢትዮጵያ መቶ ሜትርም ይሁን አንድ ሺሕ ማይል ይራቅ ከድንበር ማዶ ያለ ሁሉ ዲያስፖራ ነው፡፡ የምንገኝበት አገር፣ የትምህርት ደረጃችን፣ የወጣንበት መንገድ፣ ሃይማኖታችን ወይም ብሔራችን ዲያስፖራ ከመሆን (ከመበትን) አያድነንም፡፡ ስለዚህ አንድ ሰው በአውሮፕላንም ይሁን በመርከብ፣ ጥገኝነት ጠይቆም ይሁን አግብቶ፣ ፊደል የቆጠረም ይሁን ፕሮፌሰር የሆነ፣ እስላምም ይሁን ክርስቲያን፣ ዐማራም ይሁን ኦሮሞ ወይም ጉራጌ ወይም ሌላ ከድንበር ወጥተን ወደ ሌላ ሉዓላዊ አገር ከገባን ተበትነናል ማለት ነው፡፡ የምንገኝበት አገርም መመዘኛ አይደለም፡፡ አፍሪካ፣ አውሮፓ፣ አሜሪካ፣ ኤዥያ ወይም ኦሽኒያ መሆናችን ምንም ልዩነት አያመጣም፡፡ … [Read more...] about ዲያስጶራዎቻችን
“የኦሮሞ ህዝብ ሙስሊም ነው…” “BBN (አቶ አብዲረሂም አህመድ)
በኦሮሞ ስም እየተደረጉ ያሉትን አብዛኛዎቹን ስብሰባዎች ላስተዋለ ሰው፣ የኦሮሞ ጎሳ ብቻ ሳይሆን በአመዛኙ የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች ስብስብ እየመሰለም (“ሆኗል” አለማለታችን ይያዝልን) ሄዷል። አቶ ጃዋር ሙስሊም ከመሆኑ እና ራሱን የኦሮሞ የፖለቲካ ተወካይ/ተጠሪ አድርጎ በየመድረኩ ብቅ ካለበት ጊዜ ጀምሮ፤ ቁጥራቸው ቀላል የማይባል የኦሮሞ ተውላጅ ልሂቃን፣ አቶ ጃዋርን “በሜጫ አንገት የመቁረጥ” ፉከራው ጋር አዝለው፣ አንድም ጊዜ በአደባባይ ይቅርታ እንዲጠይቅ ማድረግ ሳይችሉ እና እነሱም ሳያወግዙ፣ እስካሁን ድረስ ተሸክመው የመዝለቃቸውም ነገር እኛ በ“ኢትዮጵያ ሴኩላር ሰብዓዊያን” ስር የተሰባሰብነውን ግለሰቦች እጅግ አሳዝኖናል፣ አሳስቦናልም። እሱ ሲገርመን አሁን ደግሞ በቅርቡ BBN በሚባል ስም የሚታወቀው፣ በጸረ-ህወሃት የፖለቲካ አቋሙ እና በእስልምና ሃይማኖት አራማጅነቱ … [Read more...] about “የኦሮሞ ህዝብ ሙስሊም ነው…” “BBN (አቶ አብዲረሂም አህመድ)
የኢትዮጵያን ፍላጎት ያልተረዳ መንግስት ኢትዮጵያን ሊመራ አይችልም
በቅርቡ ፋና ብሮድካስት ባዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ “ኢሕአዴግን” የወከሉት የኢትዮጵያ ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ምክትል ኃላፊ አቶ በረከት ስምኦን ባቀረቡት ጥናታዊ ፅሁፍ ላይ ጥቂት ለመወያየት ነው የዛሬው አሳቤ። በዚህ የውይይት መድረክ ላይ እኚህ ሰው የተናገሩት ብዙው ነገር ከተለመደው የተለየ ባይሆንም በተለይ የኢትዮጵያን ፍላጎት በተመለከተ የፓርቲያቸው አመለካከትና ጥናትና ምርምር ምን መሰረታዊ ችግር እንዳለበት መመርመር የዚህን መንግስት መሰረታዊ ችግሮች እንደገና ለማሳየት ይጠቅማል። በመጀመሪያ ይህ ውይይት ለምን ተዘጋጀ? ካልን ምን አልባትም በሃገሪቱ የተነሳውን ግዙፍ ህዝባዊ ተቃውሞ ተከትሎ የተለያዩ ሃይሎች መንግስት ዲያሎግ እንዲያደርግ ግፊት ማድረጋቸውን ተከትሎ የተዘጋጀ ይመስላል። ታዲያ የግብር ይውጣ ነገር ብቻ መሆኑን የሚያሳየው የህዝብ ልብ ያረፈባቸው ተቃዋሚ ፓርቲዎች … [Read more...] about የኢትዮጵያን ፍላጎት ያልተረዳ መንግስት ኢትዮጵያን ሊመራ አይችልም
የኦሮሞ ብሔረ-ሰብ ቁጥር
መግቢያ ያለፉትን 40 ዓመታት ፖለቲካችንን ለመረመረ አገርን በሚመለከት የሚሰነዘሩት አስተያየቶች ወይም የሚሰጡት ትንተናዎች ሁሉ ሳንይሳዊ ይዘት ይኑራቸው አይኑራቸው የሚጠይቅ የለም። በተለይም ፖለቲካ ፍልስፍናዊ መሰረት ያለው ታላቅ ፅንሰ-ሃሳብ መሆኑ ግንዛቤ በሌለበት አገርና፣ ማንኛውም ህብረተሰብንና የአገርን አጠቃላይ ሁኔታ በሚመለከት ረገድ የግዴታ ሳይንሳዊ ትንተና መስጠት አስፈላጊ መሆኑ ቀርቶ ስሜት ዋናው መመሪያ በሆነበት አገር የሚሰነዘሩ አስተያየቶች ትክክል መሆናቸውንና አለመሆናቸውን ቁጭ ብሎ በሰከነ መንፈስ ለመመርመር የሚቃጣ ሰው በፍጹም የለም። እንደሚታወቀው በተለይም በአብዮቱ ወቅት ሳይንስና ፍልስፍና መመሪያ መሆናቸው ቀርቶ ስሜት የፖለቲካውን መድረክ በመያዙ እንደተከታተልነው ለብዙ መቶ ሺህ ህዝብ መሞትና ለአገር ውድመት የራሱን አስተዋፅዖ አበርክቶ አልፏል። ዛሬ … [Read more...] about የኦሮሞ ብሔረ-ሰብ ቁጥር
የሽግግር ሃሳብ
". . . ገብረሕይዎት በመንግሥት እና የህዝብ አስተዳደር መፅሃፉ መቅድም ላይ እንዲህ ይላል፤ «ሕዝቦችን ሁሉ የሚፈጥር አንድ አምላክ ነው። ይህም አምላክ የምንለው የሕዝቦች ፈጣሪ ሕዝቦችን ሁሉ ትክክል አንድ አድርጎ ፈጥሮ ላኗኗራቸውና ለልማታቸው የሚያስፈልጋቸውን ነገር ሁሉ ከሙሉ ፈቃድና ስልጣን ጋር በእጃቸው ሰጥቷቸዋል። ስለዚህ ማናቸውም ህዝብ ቢለማም ቢጠፋም በገዛ እጁ ነው። ሕዝብ የሚጠፋበት አንዳንድ ምክንያት ቢያገኝ ያውም ምክንያት በአንዳንድ ሰው ቢመካኝ ትክክል አይደለም። የልማትን መንገድ ለማግኘት የሚጥር ሕዝብ ቢገኝ በአንዳንድ ክፉ ሰው ምክንያት ሊጠፋ አይችልም። እንዲሁም ደግሞ የልማትን መንገድ ለማግኘት የማይጣጣር ሕዝብ በአንዳንድ ደህና ሰው ኃይል ልማት ሊያገኝ አይችልም።» ይህ የገብረሕይዎት ተጠይቃዊ ሀሳብ ኢትዮጵያ ያለችበትን ወቅታዊ ሁኔታ ለመመርመር ሲጠቀመን … [Read more...] about የሽግግር ሃሳብ
የዐማራ ድምፅ ሬድዮን እንርዳ
በአሁኑ ዘመን በኢትዮጵያ ውስጥ ሁሉ ነገር እያለው ሁሉንም ያጣ ዜጋ ዐማራው ነው ቢባል የተጋነነ ነው ሊባል አይችልም። በግልጽ እንደሚታወቀው፣ ዐማራው ቋንቋው አማርኛ ነው። ይህንን ቋንቋውን ከሌሎች የኢትዮጵያ ጎሣዎች ቋንቋዎች ጋር አጣጥሞ በማሳደግ ለሁሉም ኢትዮጵያዊ የጋራ መግባቢያ እንዲሆን አበርክቷል። ይሁን እንጂ፣ በአሁኑ ጊዜ የአማርኛ ቋንቋ ለዐማራው ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ተለይቶ መከበሪያው መሆኑ ቀርቶ መጠቂያው ሆኗል። በአማርኛ ቋንቋ የሚጻፉት፣ በሬድዮ እና በቴሌቪዥን የሚቀርቡት ዝግጅቶች በአብዛኛው ማለት ይቻላል፣ ዐማራው የሚወገዝባቸው፣ የሚዋረድባቸው እና የሚኮነንባቸው እየሆኑ ከመጡ ዓመታትን ተሻግረው ዘመናት ተቆጥረዋል። ስለሆነም ዐማራን እና አማርኛን በጠላትነት ፈርጀው የጥፋት ተግባራቸውን ለፈጸሙና ለሚፈጽሙ ኃይሎች አጸፋውን በመስጠት፣ የአማርኛ ቋንቋም ሆነ የዐማራ ነገድ … [Read more...] about የዐማራ ድምፅ ሬድዮን እንርዳ
የግርማ ይፍራሸዋ ፒያኖ ኮንሰርት በዋሺንግተን ዲሲ
ከ25 ዓመታት በላይ የፒያኖ ድርሰቶችን በመጻፍና በመጫወት የአገራችንን ስም በማስጠራት የቆየው ኢትዮጵያዊው ዜማ ደራሲ እና ፒያኒስት ግርማ ይፍራሸዋ በአሁኑ ቅዳሜ November 26 ምሽት ከ6:30 ጀምሮ በዋሺንግተን ዲሲ እና በአካባቢዋ ለሚገኙት አድናቂዎቹ ግሩም የሆነ የፒያኖ ሙዚቃ ትርኢት Washington Ethical Society አዳራሽ ለማቅረብ ተዘጋጅቷል። ግርማ የሙዚቃ ትምህርቱን የጀመረው በልጅነቱ ክራር በመጫወት ነበር። በመቀጠልም በያሬድ ሙዚቃ ት/ቤት (1975-1978 ዓ.ም)፣ Sofia State Conservatory of Music (1978-1986 ዓ.ም)፣London Royal Academy of Music (1989 ዓ.ም)፣ እናLeipzig Hochschule für Music und Theater (1991 ዓ.ም) ክላሲካል ሙዚቃን በመማር የድርሰትና የትርኢት ችሎታውን ለማዳበር … [Read more...] about የግርማ ይፍራሸዋ ፒያኖ ኮንሰርት በዋሺንግተን ዲሲ
ህወሃት እጅ ላይ የንጹሃን ደም እየተንተከተከ ነው!! የምትኮሩ በዚህ ኩሩ
ህወሃት የታሪኩ ካስማና ማገር ከአስከሬን ጋር የተጣበቀ ስለመሆኑ የሚመሰክሩበት የሩቅ ሰዎች አይደሉም። አብረውት በበረሃ የነበሩ፣ አብረውት አመራር ሲሰጡ የኖሩ፣ “በሚያራምዱት አቋም” ከድል በፊትና በኋላ የተለዩት በተለያዩ ሚዲያ ላይ እንደመሰከሩት ህወሃት ደም ምሱ፣ አስከሬን ትራሱ ነው። በነዚሁ የቅርብ ሰዎቹ የተሰሙት ምስክርነቶች ስም፣ ቦታ፣ ጊዜ በመጥቀስ በወቀቱ እዚያው እንደነበሩ በማረጋገጥ እንጂ እንዲሁ በመላ አልነበረም። እነሱ ለአብነት ተነሱ እንጂ ሰለባዎች በየጊዜው አዳዲስ መረጃ ይዘው ብቅ ማለታቸው የተለመደ ነው። እዚህ ላይ ሌሎችም አይረሱም። ቅድሚያ ስለ ሌሎቹ። በቦታው የነበረ የዓይን እማኝ፤ ደደር 1983 የጅጅጋ ሆቴል ባለቤት ዓለምዘውድ እንዴት ሞተች? ዓለምዘውድ ቁመቷ ረጅም፣ ሰውነቷ ሙሉ፣ አሣ የምትመስል ጠይም፣ ደግና ርኅሩኅ እንደነበረች የሚያውቋት … [Read more...] about ህወሃት እጅ ላይ የንጹሃን ደም እየተንተከተከ ነው!! የምትኮሩ በዚህ ኩሩ
በጅዳ ሽሜሲ በር ላይ ወድቃለች የተባለችው እህት ጉዳይ!
ከትናንት ጅዳ ውስጥ በጠና ታማ እሷና ልጇ አደጋ ላይ አሉ ስለተባ ለችው እህት እየተሰራጨ ያለው መረጃ ደርሶኛል። መረጃውን በዝርዝር ያገኘሁት ከሊያ ሾው ነበር፣ ታመመች የተባለችውን እህት በቪዲዮ የተደገፈ መረጃ እንደደረሰኝ ወደ ጅዳ ቆንስል ደውዬ ለማጣራት ሞክሬ ነበር! በጅዳ ቆንስላ መረጃ ለማግኘት ከባድ እየሆነ መጥቷ ል፣ አንዳንዶች ኃላፊዎች ከዚህ ቀደም በማቀርባቸው ተጨባጭ ሂሶች አኩርፈው መረጃ ላለመስጠት ስልካቸውን ይዘጉብኛል፣ አንዳንዶች ደግሞ መረጃም ሆነ ጥያቄ ለመመለስ ፈቃደኛ አይደሉም! እጅ አዙር በሆነ መንገድ የጅዳ ቆንስል መረጃው እንዳልደረሰው ተነግሮኛል! ይህች እህት በሽሜሲ ጊዜያዊ እስር ቤት በር ላይ ተጥለላች መባሉን ሰምቸ ወደ ቦታው የሚያጣራልኝ የስራ ባልደረባዬን ልኬም ነበር፣ ዛሬ ረፋድ ላይ በር ላይ ተዟዙሮ የወደቀ ሰው አለመኖሩን አረጋግጦልኛል! ይህን … [Read more...] about በጅዳ ሽሜሲ በር ላይ ወድቃለች የተባለችው እህት ጉዳይ!