መግቢያ ሱባዔ፦ በሰው፤ በቦታና በሰአት ስለሚከናወን የሶስቱም ማለትም የሰአት፤ የሰባዊነትና የመካን ድምር ነው። ሱባዔ በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ጥልቅ፤ ረቂቅና ምጡቅ ግንዛቤ አለው። በመንፈሳችንና በሥጋችን መካከል ያለውን ሚዛን አለመሰበሩንና አለማጋደሉን፤ በፈጣሪያችንና በራሳችን መካከል፤ በህዝባችንና በራሳችን መካከል ያለንን ግንኙነት የምንፈትሽበት ነው። በሩቅና በቅርብ ያለውን አካባቢያችንን ማየት የምንችልበት ተራራ ነው። ውስጣዊ ህሊናችንን የምናይበት ረቂቅ መስታወት ነው። የራቀውን አቅርቦ የረቀቀውን አጉልቶ የሚያሳየን፤ እመቀ እመቃት፡ አየረ አየራት፡ ያሉትን ሁሉ ፍጥረታት የምንፈትሽበት ተራዛሚ መነጽር ነው። ሱባዔ፦ በሰው ብቻ የተወሰነ አይደለም። በደማቸው ሞቃትነትና ቀዝቃዛነት የሚለያዩ ፍጥረታት በየደረጃቸው ሱባዔ ይገባሉ። የፍጥረታትን ቅደም ተከተል በመጠበቅ … [Read more...] about የዘንዶ ሱባዔ?
Archives for August 2014
በዓሉን የበላው ደርግ “አይደለም”፣ የሰው ጅብ ነው!
እውኑን ቀርቶ ምስሉንም እንኳን አይቸው የማላውቀው[1] በዓሉ ግርማን አውቀዋለሁ። ህይወትን እና ሰውን የሚወደውን፣ ውብ ሰብዕና ያለውን በዓሉ ግርማን አውቀዋለሁ። በዓሉን፣ ሰብዓዊ እና ሞራላዊ ማንነቱን በጽሁፎቹ ውስጥ አይቻለሁ። በዓሉን አውቀዋለሁ። እናት አባት አያት፣ ቅማያት እና ቅንዝላቶቼ ሁሉ መጣፍ ቅዱስ ዳዊቱን፣ ቁራን ኪታቡን በነጋ በመሸ ቁጥር እየደገሙ እና እያነበቡ የኖሩትን ያህል፣ እኔ ደግሞ በዓሉን አንብቤያለሁ። በተለይ ኦሮማይን፣ ቢያንስ ከእጄ ከገባበት (ከ1978 ዓ.ም አጋማሽ ጀምሮ) ምናልባትም ከሶስት እና አራት ጊዜ በላይ ደጋግሜ ሙሉውን ያነበብኩትን ያህል፣ ለአምስት ወይም ስድስት አመት አካባቢ ደግሞ፣ ጧት ጧት ከእንቅልፌ ነቅቼ ከምኝታዬ በተነሳሁ እና ቤት ውስጥ በገባሁ በወጣሁ ቁጥር እንደሥሥት ልጅ ደጋግሜ እያነሳሁ በየቀኑ፣ ከጄ የገባውን አንድ ሁለት ገጽ … [Read more...] about በዓሉን የበላው ደርግ “አይደለም”፣ የሰው ጅብ ነው!
ጭቃና ውኃ
ጭቃ እያቦካ ጭቃ እየለወሰ ጭቃ እየጋገረ ጭቃ እየጎረሰ ያረፈደው አያ ከጭቃው ገበያ ያውና ብቅ አለ ከጭድ መሃል ወጣ በጨመለቅ እጁ ሊጨብጠኝ መጣ። 'መቼም ከጭቃ ነው ተፈጥሮ ስሪቴ' ብዬ እንዳልጨብጠው 'እምቢኝ!' አለኝ ቤቴ "ጭቃማ አይደለሁም! _ ነኝ እንጂ ውብ ሸክላ ታሽቶና ተቦክቶ በውቅ የተኮላ ይታጠብ በቅድሚያ አቅርብለት ውሃ ለጨቀየው ነፍሱ በነገር ቤት ዝሃ" ብሎ ይሞግተኛል ተላላው መንፈሴ ውሃውን ረስቼ ጭቃን በማንገሴ እነሆኝ በል እንካ አንተ ጭቃ ለዋሽ ኮዳዬን ዘቀዘቅኩ ለእድፍህ አባሽ። የመንፃት ቀንህን አታርቀው ጓዴ ውሃዬን ተጠቀም ላፍስልህ ላንዴ ከዚያም ልጨብጥህ ደርሳለሁ ዘመዴ ጭቃ እያቦካ ጭቃ እየለወሰ ጭቃ እየጋገረ ጭቃ እየጎረሰ ስንቱ ሰው መሰለህ ደግሞ የታደሰ ከመቡካት በኋላ ውበት የለበሰ። … [Read more...] about ጭቃና ውኃ
እኚህ ሰው ማናቸው? – ፲
ከአዘጋጆቹ፤ባለፈው ጊዜ “እኚህ ሴት ማናቸው? – ፱” በሚል ለቀረበው ምላሽ በድረገጻችን በመላክና በፌስቡክ ላይ በመለጠፍ የተሳተፋችሁትን በሙሉ እናመሰግናለን፡፡ በተለይ በግጥም ምላሻችሁን ለሰጣችሁ በሙሉ ከፍያለ ምስጋናችንን እናቀርባለን፡፡ የቅንብሩ አዘጋጅ ወለላዬ በቁጥር ዘጠኝ ለቀረበው ጥያቄ ምላሻቸውን በሚከተለው መልኩ በግጥም አስፍረዋል፡፡ (እንደተለመደው በየሳምንቱ መልሱን ተከታትለን ባለማቅረባችን ለአንባቢያንና መልሱን አዘጋጅተው ልከው ላቆየንባቸው ወለላዬ ታላቅ ይቅርታ እንጠይቃለን::) መልስ ትንሽም ቢሆኑ - ቁጥራቸው ባይበዛ የድሮ ዘፋኞች - ነበራቸው ለዛ ከነዛ መካከል - በድፍን ከተማ ታዋቂ ነበሩ - እሳቱ ተሰማ ምስጋና አቀርባለሁ - መልስ ለሰጣችሁ እሳቱን እወቁ - ደግሞ ሌሎቻችሁ ለዚህ ሳምንት “እኚህ ሰው ማናቸው? – ፲” ወለላዬ የሚከተለውን … [Read more...] about እኚህ ሰው ማናቸው? – ፲
ትኩረት – ከውጪ ቋንቋዎች ለተወረሱ ቃላት
የሀገራችን ቋንቋዎች ከውጪ ቋንቋዎች በርካታ ቃላትን ወርሰዋል፡፡ ይህም ከብሉይ ዘመን ጀምሮ ይታይ የነበረ ክስተት ነው፡፡ የመወራረሱ አድማስ ስፋቱን የጨመረው ግን በአስራ ዘጠነኛው ክፍለ ዘመን መጨረሻ ላይ ነው፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በቀጣዮቹ አንድ መቶ ሀያ ዓመታት ውስጥ የታዩት ሀገር አቀፍና ዓለም አቀፍ ክስተቶች የሀገራችን ቋንቋዎችን ለውጪ ቋንቋዎች ተጽእኖ የበለጠ ክፍት እንዲሆኑ አድርገዋቸዋል፡፡ ታዲያ ከሶስት ሺህ ከሚልቁት የውጪ ቋንቋዎች መካከል ለሀገራችን ቋንቋዎች ብዙ ቃላትን ለማውረስ የበቁት አራቱ ብቻ ናቸው፡፡ እነርሱም ዐረብኛ፣ ፈረንሳይኛ፣ ጣሊያንኛና እንግሊዝኛ ናቸው፡፡ የቱርክ እና የጀርመን ቋንቋዎችም ጥቂት ቃላትን ለሀገራችን ቋንቋዎች አበርክተዋል፡፡ ***** ዐረብኛ በሀገራችን ቋንቋዎች ላይ ተጽእኖ ለመፍጠር የቻለው በዋናነት የእስልምና ሀይማኖት የአምልኮና … [Read more...] about ትኩረት – ከውጪ ቋንቋዎች ለተወረሱ ቃላት
ከላይ ሆነን ስናይ
በቅርቡ የኣሜሪካ ፌደራል ኣቪየሽን ኣስተዳደር (FAA) በዓለም ላይ ለበረራ ኣደገኛ የሆኑትን መስመሮች በካርታው ላይ ከቦ ኣስጠንቅቆ የነበረ ሲሆን በሪፖርቱ ላይ እንደሚታየው እነዚህን ኣደገኛ ቦታዎች በሁለት ከፍሏቸዋል። ኣንደኛው መስመር ኣደገኛነት ያለው ክልል (potentially hostile region) ሲሆን ሁለተኛው ክልል ግን በረራን ጨርሶ የከለከለ(Flight prohibited) ክልል ነው። ኣደገኛነት ኣላቸው ተብለው ኣብራሪዎች ከግምት እንዲያስገቡ የተመከሩባቸው ክልሎች ኬንያ፣ ኣፍጋኒስታን፣ ኢራን፣ ሶሪያ፣ ማሊ፣ የመን፣ ኮንጎና ግብጽ ሲናይ ናቸው። የበረራ መስመር የተከለከለባቸው ኣካባቢዎች ደግሞ ዩክሬን ውስጥ ድኒፕሮፐትሮቭስክ (ይህ ኣካባቢ በሶቪየት ዮኒየን ጊዜ የኒውክሌር ማምረቻ ተቋም የነበረበትና በኣሁኑ ሰዓት ደግሞ በራሽያ የሚደገፉ ገንጣዮች የሚንቀሳቀሱበት ክልል … [Read more...] about ከላይ ሆነን ስናይ
የሴት ልጅ ግርዛት ጎጂ ወይስ ጠቃሚ?
ጥናታዊ ጽሑፍ! በዚህ ርእሰ ጉዳይ ላይ አንዳች ጥናት ቢጤ ማድረጌን አምና በግብረ ሰዶማዊያን ጉዳይ ላይ በጻፍኩት ጽሑፍ ሳይቸግረኝ ጠቆም በማድረጌ ብዙኃን መገናኛዎችን የሚከታተሉ ሰዎች በኢሜይልና በስልክ በአካልም ጭምር በዚህ ርእሰ ጉዳይ ላይ ያዘጋጀሁትን ጥናታዊ ጽሑፍ ለንባብ እንዳበቃላቸው እጅግ ወተወቱኝ፤ አይ ረጅም ነው ለመጽሐፍ እንጅ ለዚህ ዓይነት መስተንግዶ አይሆንም ረዘመ ትላላቹህ ብልም ሊቀበሉኝ አልቻሉም ጨቀጨቁኝ እንግዲህ ካልተውኝ ምን አደርጋለሁ ብየ አቀራረቡን ግን ለብዙኃን መገናኛ በሚሆን ቀየርኩትና ተዛማጅ የሆነ ጠቃሚና አስፈላጊ ጉጋይ አክየበት ጽፌላቹሀለሁ ያውላቹህ፡- ይሄንን ጥናት ያደረኩት ከስድስትና ከሰባት ዓመታት በፊት ነበር፡፡ በዚህ ጥናት ከ800 ያላነሱ ሰዎች በቀጥታ በሽዎች የሚቆጠሩ በተዘዋዋሪ የጥናቴ ግብአት በማድረግ ተጠቅሜያለሁ፡፡ ጥናቴን … [Read more...] about የሴት ልጅ ግርዛት ጎጂ ወይስ ጠቃሚ?
የዞን ዘጠኝ ጦማርያንና ጋዜጠኞችን ክስ አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ
አገራችን ኢትዮጵያ በጥሩ ልትጠራባቸው የምትችላቸው ጉዳዮች እንዳሉ ሆነው በድህነት በሰብዓዊመብት አያያዝ፣ በሙስና እና ሃሳብን ነጻነት በመግለጽ መብት የተለመዱ የምናፍርባቸው ጉዳዩች ሆነው መቀጠላቸው እሙን ነው፡፡ ሃሰብን በነጻነት መግለጽን አስመልክቶ ሶስት ወራትን ከፈጀ ምርመራ በኋላ በብዙ የፓሊስ ድብብቆሽ ሂደት የዞን9 ጦማርያን እና ጋዜጠኞች ላይ ባለፈው አርብ ክስ መመስረቱም አብሮ ይታወሳል፡፡ ጓደኞቻችን ከታሰሩ ጊዜ ጀምሮ መንግሰት ያቀረበውን ውንጀላ አስመልክቶ በተለያየ ወቅት ሃሳባችንን ለመግለጽ አስበን ምናልባት የምንሰጠው ሃሳብ አሁንም በመንግሰት እጅ የሚገኙት ጓደኞቻችን ላይ ሊኖረው የሚችለውን ተጽእኖ በመፍራት እነዲሁም ለመንግሰት እድሉን በመስጠት ኦፌሻል ክሱን እስክናይ ድረስ በጠቅላላ ሃሳቦች ላይ አስተያየት ከመስጠት ውጨ ብዙም ሳንል ቆይተናል፡፡ አሁን ግን ክሱ አንድ … [Read more...] about የዞን ዘጠኝ ጦማርያንና ጋዜጠኞችን ክስ አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ
አዲስ አበባን የተጫናት ፍልሰት
ዕቃ የጫኑ ታክሲዎችና ሌሎች መኪናዎች በሚያራግፉባቸው ማቆሚያዎች ሰብሰብ ብለው ሮጠው ዕቃ ማውረድ፣ ከሚጫንበት ስፍራም መጫን የለት ተዕለት ሥራቸው ነው፡፡ አሠሪዎች በተለይም በግንባታው ዘርፍ ያሉት የቀን ሠራተኞችን ከሚወስዱበት መገናኛ፣ ሃያሁለት፣ መሪ ሳሪስ አየር ጤናና ሌሎችም ሥፍራዎች በጠዋቱ ተሰባስበው መታየታቸው አመሻሽ ላይም በየሃይገሩና ባሱ ተጨናንቀው ወደየማደሪያቸው መጓዛቸውም እንዲሁ፡፡ ታዳጊ አዋቂ ሳይል በየገበያ ስፍራው የሸክም አገልግሎት ለመስጠት የሚሯሯጡትም ጥቂት አይደሉም፡፡ በመልካም አስተዳደር እጦትም ይሁን ከራስ በመነጨ ፍላጐት ትምህርት አቋርጠውና በእርሻውም ሆነ በሌላው የሚያግዙዋቸውን ቤተሰቦቻቸውን ትተው ወደ አዲስ አበባ የሚነጉዱት የየክልሉ ነዋሪዎች ተበራክተዋል፡፡ በዋና ዋና መንገዶች፣ በአደባባዮችና በትራፊክ መብራቶች፣ በእምነት ሥፍራዎች በማሳለጫ … [Read more...] about አዲስ አበባን የተጫናት ፍልሰት
“ፋክት መጽሔት”
ከሁለት ሳምንታት በፊት በ9-11-2006ዓ.ም. አንድ የፋክት መጽሔት ደንበኛ የሰፈር ሰው አንድ ጸሐፊ በፋክት መጽሔት ላይ አንድ ጽሑፌን መነሻ አድርጎ ያልኩትንም ያላልኩትንም እየቀላቀለ አብጠልጥሎኝ ኖሮ ይሄ ቁጭት ፈጥሮባቸው ስለነበር ባገኙኝ ጊዜ “ባይ ባይ ምንም የለም ለምንድን ነው መልስ የማትሰጠው?” ሲሉ ጠየቁኝ፡፡ ለማን? ስል መለስኩላቸው ፋክት መጽሔት ላይ ስምህን ላጠፋው ሰው ነዋ! አሉኝ፤ ማን ነው ስሜን ያጠፋው? ስላቸው እንዴ! አላየኸውም ማለት ነው? አንዱ እኮ ጻፈብህ አሉኝና ወደ ቤታቸው ገብተው መጽሔቱን ይዘው መጡ ያሉትን ጽሑፍ አነበብኩት ልክ ወያኔ ዜጎችን “የቀድሞ ሥርዓት ናፋቂ” እያለ እንደሚያሸማቅቀው ሁሉ ይሄም ሰው እኔን “ባረጀውና ባፈጀው መንገድ ስለ ኢትዮጵያ አንድነት የሚታገል ሰው፣ የብሔረሰቦችን እኩልነት የማይቀበል” ምንትስ እያለ እንደ ወያኔ በፈጠራ ክስ … [Read more...] about “ፋክት መጽሔት”