• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከትህነግ ጋር ግንኙነት እንዳላቸው የተጠረጠሩ 1,642 ሰዎች ተያዙ

August 27, 2021 11:42 am by Editor 1 Comment

በ1,616 የንግድ ድርጅቶች ላይ ዕርምጃ መወሰዱን ፖሊስ አስታውቋል

ከአሸባሪው ትህነግ ጋር ግንኙነት አላቸው ተብለው የተጠረጠሩ 1,642 ሰዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ፖሊስ አስታወቀ።

የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን የወንጀል ምርመራ ቢሮ ኃላፊ ምክትል ኮሚሽነር ጄነራል ዘላለም መንግሥቴ እንደገለጹት፣ ከትህነግ ጋር ግንኙነት እንዳላቸው የተጠረጠሩ ሰዎችን በማደን በቁጥጥር ሥር እንዲውሉ እየተደረጉ ናቸው።

እስካሁን ድረስ በተካሄደው የተቀናጀ ምርመራ ከትህነግ ጋር ግንኙነት አላቸው ተብለው የተጠረጠሩ 1,642 ሰዎች፣ በተለያዩ አካባቢዎች በቁጥጥር ሥር ውለው ተጨማሪ ምርመራ እየተደረገባቸው እንደሆነ አስታውቀዋል።

ከተጠረጠሩት ሰዎች በተጨማሪ ለትህነግ ቡድን ሕገወጥ ተልዕኮ መጠቀሚያ ናቸው ተብለው የተጠረጠሩ የንግድ ድርጅቶች ተዘግተው ምርምራ በመካሄድ ላይ እንደሆነ ገልጸዋል።

ለትህነግ ቡድን መጠቀሚያ የነበሩ ሆቴሎች፣ ሕንፃዎች፣ መጋዘኖች፣ የኢንቨስትመንት እርሻዎች፣ ፋብሪካዎችና ሪል ስቴቶችን ጨምሮ 1,616 ያህል የንግድ ድርጅቶች እንዲዘጉ መደረጉን ጠቅሰዋል።

ፖሊስ ባከናወነው ሥራ 58 ሚሊዮን ብር በላይ ጥሬ ገንዘብ በቁጥጥር ሥር መዋሉን፣ በተጨማሪም 93 የባንክ ሒሳቦች እንዳይንቀሳቀሱ በማሳገድ የባንክ ሒሳቦቹ ምን ያህል ገንዘብ እንደያዙ በማጣራት ላይ እንደሚገኝም ተገልጿል።

በቀጣይም ከትህነግ ጋር ግንኙነት ያላቸውንና ተልዕኮ ተቀብለው የሚንቀሳቀሱ አካላትን ለማደን የተቀናጀ የምርመራ ሥራና ክትትል የሚደረግ መሆኑን የገለጹት ኃላፊው፣ ለዚህም ተግባር አገር አቀፍ የሆነ የፖሊስ ምርመራ የጋራ ግብረ ኃይል እንዲቋቋም መደረጉን ተናግረዋል።

ግብረ ኃይሉ በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ የሚመራ እንደሆነ፣ሁሉንም ክልሎች ከሌሎች አጎራባች ክልሎች ከሚገኙ የወንጀል ምርመራ ዘርፎች ጋር በአንድ ያጣመረ መሆኑ ተገልጿል። ግብረ ኃይሉ በፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ እንደሚመራና በአገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች ትህነግ ያሰማራቸውን ሽብርተኞች በመያዝ ለሕግ ከማቅረብ ባሻገር፣ በተደራጁ ወንጀሎችና በሌሎች የሕግ ጥሰቶች ላይ የሚሳተፉ አካላትን በመቆጣጠር የሕግ የበላይነት የሰፈነባትን አገር ለማስቀጠል ከፍተኛ ፋይዳ እንደሚኖረው ተገልጿል። (ሪፖርተር)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Law, Middle Column, News Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Comments

  1. GI.haile says

    August 28, 2021 07:30 pm at 7:30 pm

    ሁሉም የቢዝነስ በለቤቶች መነሻ ገንዘቡነረ ያገኙት ከሕወኣት ነው። ስለዚህ ከሚያገኙት ገንዘብ ለድርጅቱ የሚያገቡተሰ ገቢ ኣላቸው። ኣሁን በውጭ የንግድ ዝውውርኑ በማድረገሰ ኣብዛኛው የሕወኣት ቤተሰቦችና የውስጥ ቅርበት ያላቸው በውጭው ዓለም ከአገር ቤት ኣስመጪ ላኪ ጋር ይሰራሉ። ሰዎቹ ዓለም አቀፍ መረብ ዘርግተዋል።

    Reply

Leave a Reply to GI.haile Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule