• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

160 ሰዎች የሞቱበት፣ 360 ሰዎች የተጎዱበት፣ ከ4.6 ቢሊዮን ብር በላይ ንብረት የወደመበት የነጃዋር ክስ የወንጀል እንጂ የፖለቲካ እንዳልሆነ ተጠቆመ

September 29, 2020 09:05 pm by Editor 1 Comment

ከድምፃዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ ጋር በተያያዘ በቁጥጥር ሥር ውለውና ክስ ተመሥርቶባቸው የሚገኙ ግለሰቦች ፖለቲከኞች ቢሆኑም፣ የታሰሩት በፖለቲካ እንቅስቃሴያቸው አለመሆኑን ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ አስታወቀ።

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) መስከረም 14 ቀን 2013 ዓ.ም. በጠቅላይ ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤት ፕሬስ ሴክሬታሪያት የውጭ ቋንቋዎችና ሚዲያ ኃላፊዋ ቢልለኔ ሥዩም ጋር በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደገለጹት፣ የጉዳዮች መገናኘት ካልሆነ በስተቀር፣ የታሰሩ ግለሰቦች ፖለቲከኞች ቢሆኑም ከፖለቲካ አመለካከትቸና እንቅስቃሴያቸው የታሰሩ እንዳልሆነ አብራርተዋል።

ሰኔ 23 ቀን 2012 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ልዩ ስሙ ገላን ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በጥይት ተመትቶ የተገደለው ድምፃዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ ሞት ተከትሎ፣ በአዲስ አበባና በኦሮሚያ ክልል ከተከሰቱ አመፆችና ጥቃቶች ጋር ግንኙነት አላቸው በተባሉ 2,000 ተጠርጣሪዎች ላይ ክስ መመሥረቱን፣ ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) አስታወቁ።

ጠቅላይ ዓቃቤ ሕጉ ጌዲዮን (ዶ/ር) እና የውጭ ቋንቋዎችና የዲጂታል ሚዲያ ኃላፊዋ ቢልለኔ ሥዩም እንዳስታወቁት፣ ክስ የተመሠረተባቸው ግለሰቦች በነበረው አመፅና ጥቃት ውስጥ በተለያየ ደረጃ ተሳትፎ የነበራቸው ናቸው ብለዋል።

የድምፃዊ ሃጫሉ ግድያ ተከትሎ ከ9,000 ሰዎች በላይ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ታስረው የነበረ ሲሆን፣ ከእነዚህ ውስጥም እንደ አቶ ልደቱ አያሌው፣ አቶ ጃዋር መሐመድ፣ አቶ እስክንድር ነጋና አቶ በቀለ ገርባን የመሳሰሉ ፖለቲከኞችና ጋዜጠኞች፣ እንዲሁም የሚዲያ ኃላፊዎች ይገኙበታል። ከእነዚህ ታሳሪዎች መካከል በተለያዩ ጊዜያት የተፈቱ ግለሰቦች እንደነበሩ ሲነገር ነበር።

የድምፃዊውን ግድያ ተከትሎ በነበሩ አመፆችና ጥቃቶች በአንዳንድ አካባቢዎች አናሳ ቁጥር ያላቸውን ሰዎች ለይቶ የማጥቃት ድርጊት እንደነበር ያስታወቁት ጠቅላይ ዓቃቤ ሕጉ ጌዲዮን (ዶ/ር)፣ በዚህም ሳቢያ 160 ሰዎች እንደ ሞቱ፣ 360 ሰዎች ጉዳት እንደ ደረሰባቸው፣ እንዲሁም ከ4.6 ቢሊዮን ብር በላይ የንብረት ውድመት እንደተከሰተ ገልጸዋል።

ወንጀሎች የተፈጸሙበት መጠንና ግዝፈት በራሱ ለምርመራውና ለክስ ሒደቱ ትልቅ ፈተና እንደሆነ ያስረዱት ጠቅላይ ዓቃቤ ሕጉ፣ መንግሥት አጥፊዎችን ወደ ሕግ እያቀረበ ነው ብለዋል።

ምንም እንኳን የሰዎችን ሕይወት መቅጠፋቸው አሳዛኝ መሆኑንና መንግሥትም በዚህ ሐዘን እንደሚሰማው የተናገሩት ቢልለኔ፣ እንዲህ ያሉ የአመፅ ክስቶችን ግን መንግሥት የዜጎቹን ደኅንነት ለማስጠበቅ አቅም የለውም ለማለት አያስችልም ብለዋል። ይልቁንም ትኩረት ያላገኙና ያልተነገረላቸው በርካታ ተመሳሳይና የሽብር ጥቃቶችን መቀልበስ የተቻለ መሆኑ ከግምት ሊገባ ይገባል ሲሉ አክለዋል።

በዚህ ላይ ያከሉት ጌዲዮን (ዶ/ር) እንዳሉት፣ መንግሥት ተመሳሳይም ሆነ ሌሎች ጥቃቶችን ከመቀልበስ ባለፈ፣ የተለያዩ አጥፊዎችን ወደ ሕግ እያቀረበ መሆኑ፣ ወደፊት ሊፈጠሩ የሚችሉ ተመሳሳይ ጥቃቶችም ሆኑ ሙከራዎችን ለማስቀረት ይረዳል ብለዋል።

በተለይ አቶ ጃዋር መሐመድ በፍርድ ቤት መንግሥት እሳቸውንም ሆነ ሌሎች ፖለቲከኞችን ያሰረው ጥፋት ኖሮባቸው ሳይሆን፣ የፖለቲካ አመለካከታቸው የተለየ ስለሆነ መንግሥት የምርጫ ሜዳው ላይ ጠንካራ ተፎካካሪ እንዳይኖር እያደረገ ነው ሲሉ ያቀረቡትን መከራከሪያ በተመለከተ ምላሽ የሰጡት ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ጌዲዮን (ዶ/ር)፣ “የጉዳዮችን መገናኘትና ምክንያትነት መረዳት መቻል ይኖርብናል፤” በማለት፣ እነዚህ የታሰሩ ግለሰቦች ፖለቲከኞች ቢሆኑም፣ የታሰሩት ግን በፖለቲካ እንቅስቃሴያቸው እንዳልሆነ መታወቅ ይኖርበታል ሲሉ ተከራክረዋል።

2013 ዓ.ም. ከቀደመው ዓመት ይልቅ በሰላምና መረጋጋት ረገድ የተሻለ እንደነበረ ያስታወሱት ቢልለኔ፣ በመተከልና በሌሎች ሥፍራዎች በንፁኃን ዜጎች ላይ የተሰነዘሩ ጥቃቶችን መንግሥት ያወግዛል ብለው፣ በመንግሥትና በክልል መንግሥታት የፀጥታ መዋቅሮች ጠንካራ ትብብር በማድረግ ሰላምና ፀጥታን ለማስጠበቅ ቁርጠኝነት እንዳለ አስረድተዋል። (ብሩክ አብዱ፤ ሪፖርተር)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Law, Left Column, News Tagged With: chilot, jawar massacre, tplf, ችሎት

Reader Interactions

Comments

  1. ZTSM says

    September 30, 2020 01:20 pm at 1:20 pm

    Those are criminals by any definition, and must be tried as such; they are not political prisoners. It is time individuals/groups like them be dealt with in the style of North Korea (historically countries like China, Vietnam, South Korea, Cambodia, etc) attained their peace by confronting their own versions of Ethiopia’s thugs in the languages the thugs understood: quick elimination by any means available to the states. Thus like Mohammed and Geleba should be eliminated out of sight and sound in the middle of the night?

    Reply

Leave a Reply to ZTSM Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በሆሩ ጉዱሩ ወለጋ ዞን የጉደኔ ጫላ ሲበሬ ቀበሌ ነዋሪዎች በኦነግ ሸኔ ላይ ጀብዱ ፈፀሙ August 11, 2022 03:04 pm
  • በኢትዮጵያ ግብርና ላይ ግብጽ ለዓመታት የፈጸመችው ሤራ August 10, 2022 10:58 am
  • የስሪ ላንካው “FamilyCracy” – ከመዓቱ እስከ ተውኔቱ August 8, 2022 09:45 am
  • “አበበ እንጂ መቼ ሞተ!”          July 19, 2022 04:57 pm
  • ሸኔ አመራሮቹንና ጠንካራ ይዞታዎቹን እያጣ ነው July 19, 2022 01:55 am
  • የወልቃይት አማራ የተሰቃየባቸው የትህነግ 15 ድብቅ እስር ቤቶች! July 18, 2022 03:13 pm
  • ገቢ የማያስገኙ የዜና ርዕሶች July 17, 2022 05:36 pm
  • “ዛሬ ‘ኃያል ነን’ የሚሉ ሀገራት ኢትዮጵያ ላይ በሚዲያ /በመረጃ/፣ በዲፕሎማሲ፣ በሳይበር እና በተልእኮ የተቀነባበረ ‘ግራጫ ጦርነት’ እያካሄዱባት ነው” ጠ/ሚ ዐቢይ July 7, 2022 10:03 am
  • የኦሮሞ ልሂቃንና ፖለቲከኞች በአማራ ተወላጆች ላይ እየደረሰ ያለውን “የዘር ማጥፋት” ወንጀል እንዲያወግዙት አብን ጠየቀ July 6, 2022 01:38 pm
  • “አማራን ኦሮሚያ ውስጥ የመግደል እና የመጨፍጨፍ እቅድ የኦነግ ሳይሆን የኦሮሚያ ብልጽግና ነው” አቶ ሃንጋሳ July 6, 2022 01:53 am
  • “በኢትዮጵያዊያን የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ በመግባት ሀገሪቱን ማተራመስ አለብን” አይማን አብድልአዚዝ ግብጻዊው ፖለቲከኛ July 5, 2022 12:57 pm
  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule