• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

160 ሰዎች የሞቱበት፣ 360 ሰዎች የተጎዱበት፣ ከ4.6 ቢሊዮን ብር በላይ ንብረት የወደመበት የነጃዋር ክስ የወንጀል እንጂ የፖለቲካ እንዳልሆነ ተጠቆመ

September 29, 2020 09:05 pm by Editor 1 Comment

ከድምፃዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ ጋር በተያያዘ በቁጥጥር ሥር ውለውና ክስ ተመሥርቶባቸው የሚገኙ ግለሰቦች ፖለቲከኞች ቢሆኑም፣ የታሰሩት በፖለቲካ እንቅስቃሴያቸው አለመሆኑን ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ አስታወቀ።

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) መስከረም 14 ቀን 2013 ዓ.ም. በጠቅላይ ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤት ፕሬስ ሴክሬታሪያት የውጭ ቋንቋዎችና ሚዲያ ኃላፊዋ ቢልለኔ ሥዩም ጋር በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደገለጹት፣ የጉዳዮች መገናኘት ካልሆነ በስተቀር፣ የታሰሩ ግለሰቦች ፖለቲከኞች ቢሆኑም ከፖለቲካ አመለካከትቸና እንቅስቃሴያቸው የታሰሩ እንዳልሆነ አብራርተዋል።

ሰኔ 23 ቀን 2012 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ልዩ ስሙ ገላን ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በጥይት ተመትቶ የተገደለው ድምፃዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ ሞት ተከትሎ፣ በአዲስ አበባና በኦሮሚያ ክልል ከተከሰቱ አመፆችና ጥቃቶች ጋር ግንኙነት አላቸው በተባሉ 2,000 ተጠርጣሪዎች ላይ ክስ መመሥረቱን፣ ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) አስታወቁ።

ጠቅላይ ዓቃቤ ሕጉ ጌዲዮን (ዶ/ር) እና የውጭ ቋንቋዎችና የዲጂታል ሚዲያ ኃላፊዋ ቢልለኔ ሥዩም እንዳስታወቁት፣ ክስ የተመሠረተባቸው ግለሰቦች በነበረው አመፅና ጥቃት ውስጥ በተለያየ ደረጃ ተሳትፎ የነበራቸው ናቸው ብለዋል።

የድምፃዊ ሃጫሉ ግድያ ተከትሎ ከ9,000 ሰዎች በላይ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ታስረው የነበረ ሲሆን፣ ከእነዚህ ውስጥም እንደ አቶ ልደቱ አያሌው፣ አቶ ጃዋር መሐመድ፣ አቶ እስክንድር ነጋና አቶ በቀለ ገርባን የመሳሰሉ ፖለቲከኞችና ጋዜጠኞች፣ እንዲሁም የሚዲያ ኃላፊዎች ይገኙበታል። ከእነዚህ ታሳሪዎች መካከል በተለያዩ ጊዜያት የተፈቱ ግለሰቦች እንደነበሩ ሲነገር ነበር።

የድምፃዊውን ግድያ ተከትሎ በነበሩ አመፆችና ጥቃቶች በአንዳንድ አካባቢዎች አናሳ ቁጥር ያላቸውን ሰዎች ለይቶ የማጥቃት ድርጊት እንደነበር ያስታወቁት ጠቅላይ ዓቃቤ ሕጉ ጌዲዮን (ዶ/ር)፣ በዚህም ሳቢያ 160 ሰዎች እንደ ሞቱ፣ 360 ሰዎች ጉዳት እንደ ደረሰባቸው፣ እንዲሁም ከ4.6 ቢሊዮን ብር በላይ የንብረት ውድመት እንደተከሰተ ገልጸዋል።

ወንጀሎች የተፈጸሙበት መጠንና ግዝፈት በራሱ ለምርመራውና ለክስ ሒደቱ ትልቅ ፈተና እንደሆነ ያስረዱት ጠቅላይ ዓቃቤ ሕጉ፣ መንግሥት አጥፊዎችን ወደ ሕግ እያቀረበ ነው ብለዋል።

ምንም እንኳን የሰዎችን ሕይወት መቅጠፋቸው አሳዛኝ መሆኑንና መንግሥትም በዚህ ሐዘን እንደሚሰማው የተናገሩት ቢልለኔ፣ እንዲህ ያሉ የአመፅ ክስቶችን ግን መንግሥት የዜጎቹን ደኅንነት ለማስጠበቅ አቅም የለውም ለማለት አያስችልም ብለዋል። ይልቁንም ትኩረት ያላገኙና ያልተነገረላቸው በርካታ ተመሳሳይና የሽብር ጥቃቶችን መቀልበስ የተቻለ መሆኑ ከግምት ሊገባ ይገባል ሲሉ አክለዋል።

በዚህ ላይ ያከሉት ጌዲዮን (ዶ/ር) እንዳሉት፣ መንግሥት ተመሳሳይም ሆነ ሌሎች ጥቃቶችን ከመቀልበስ ባለፈ፣ የተለያዩ አጥፊዎችን ወደ ሕግ እያቀረበ መሆኑ፣ ወደፊት ሊፈጠሩ የሚችሉ ተመሳሳይ ጥቃቶችም ሆኑ ሙከራዎችን ለማስቀረት ይረዳል ብለዋል።

በተለይ አቶ ጃዋር መሐመድ በፍርድ ቤት መንግሥት እሳቸውንም ሆነ ሌሎች ፖለቲከኞችን ያሰረው ጥፋት ኖሮባቸው ሳይሆን፣ የፖለቲካ አመለካከታቸው የተለየ ስለሆነ መንግሥት የምርጫ ሜዳው ላይ ጠንካራ ተፎካካሪ እንዳይኖር እያደረገ ነው ሲሉ ያቀረቡትን መከራከሪያ በተመለከተ ምላሽ የሰጡት ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ጌዲዮን (ዶ/ር)፣ “የጉዳዮችን መገናኘትና ምክንያትነት መረዳት መቻል ይኖርብናል፤” በማለት፣ እነዚህ የታሰሩ ግለሰቦች ፖለቲከኞች ቢሆኑም፣ የታሰሩት ግን በፖለቲካ እንቅስቃሴያቸው እንዳልሆነ መታወቅ ይኖርበታል ሲሉ ተከራክረዋል።

2013 ዓ.ም. ከቀደመው ዓመት ይልቅ በሰላምና መረጋጋት ረገድ የተሻለ እንደነበረ ያስታወሱት ቢልለኔ፣ በመተከልና በሌሎች ሥፍራዎች በንፁኃን ዜጎች ላይ የተሰነዘሩ ጥቃቶችን መንግሥት ያወግዛል ብለው፣ በመንግሥትና በክልል መንግሥታት የፀጥታ መዋቅሮች ጠንካራ ትብብር በማድረግ ሰላምና ፀጥታን ለማስጠበቅ ቁርጠኝነት እንዳለ አስረድተዋል። (ብሩክ አብዱ፤ ሪፖርተር)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Law, Left Column, News Tagged With: chilot, jawar massacre, tplf, ችሎት

Reader Interactions

Comments

  1. ZTSM says

    September 30, 2020 01:20 pm at 1:20 pm

    Those are criminals by any definition, and must be tried as such; they are not political prisoners. It is time individuals/groups like them be dealt with in the style of North Korea (historically countries like China, Vietnam, South Korea, Cambodia, etc) attained their peace by confronting their own versions of Ethiopia’s thugs in the languages the thugs understood: quick elimination by any means available to the states. Thus like Mohammed and Geleba should be eliminated out of sight and sound in the middle of the night?

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule