
ከድምፃዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ ጋር በተያያዘ በቁጥጥር ሥር ውለውና ክስ ተመሥርቶባቸው የሚገኙ ግለሰቦች ፖለቲከኞች ቢሆኑም፣ የታሰሩት በፖለቲካ እንቅስቃሴያቸው አለመሆኑን ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ አስታወቀ።
የኢፌዴሪ ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) መስከረም 14 ቀን 2013 ዓ.ም. በጠቅላይ ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤት ፕሬስ ሴክሬታሪያት የውጭ ቋንቋዎችና ሚዲያ ኃላፊዋ ቢልለኔ ሥዩም ጋር በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደገለጹት፣ የጉዳዮች መገናኘት ካልሆነ በስተቀር፣ የታሰሩ ግለሰቦች ፖለቲከኞች ቢሆኑም ከፖለቲካ አመለካከትቸና እንቅስቃሴያቸው የታሰሩ እንዳልሆነ አብራርተዋል።
ሰኔ 23 ቀን 2012 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ልዩ ስሙ ገላን ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በጥይት ተመትቶ የተገደለው ድምፃዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ ሞት ተከትሎ፣ በአዲስ አበባና በኦሮሚያ ክልል ከተከሰቱ አመፆችና ጥቃቶች ጋር ግንኙነት አላቸው በተባሉ 2,000 ተጠርጣሪዎች ላይ ክስ መመሥረቱን፣ ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) አስታወቁ።
ጠቅላይ ዓቃቤ ሕጉ ጌዲዮን (ዶ/ር) እና የውጭ ቋንቋዎችና የዲጂታል ሚዲያ ኃላፊዋ ቢልለኔ ሥዩም እንዳስታወቁት፣ ክስ የተመሠረተባቸው ግለሰቦች በነበረው አመፅና ጥቃት ውስጥ በተለያየ ደረጃ ተሳትፎ የነበራቸው ናቸው ብለዋል።
የድምፃዊ ሃጫሉ ግድያ ተከትሎ ከ9,000 ሰዎች በላይ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ታስረው የነበረ ሲሆን፣ ከእነዚህ ውስጥም እንደ አቶ ልደቱ አያሌው፣ አቶ ጃዋር መሐመድ፣ አቶ እስክንድር ነጋና አቶ በቀለ ገርባን የመሳሰሉ ፖለቲከኞችና ጋዜጠኞች፣ እንዲሁም የሚዲያ ኃላፊዎች ይገኙበታል። ከእነዚህ ታሳሪዎች መካከል በተለያዩ ጊዜያት የተፈቱ ግለሰቦች እንደነበሩ ሲነገር ነበር።

የድምፃዊውን ግድያ ተከትሎ በነበሩ አመፆችና ጥቃቶች በአንዳንድ አካባቢዎች አናሳ ቁጥር ያላቸውን ሰዎች ለይቶ የማጥቃት ድርጊት እንደነበር ያስታወቁት ጠቅላይ ዓቃቤ ሕጉ ጌዲዮን (ዶ/ር)፣ በዚህም ሳቢያ 160 ሰዎች እንደ ሞቱ፣ 360 ሰዎች ጉዳት እንደ ደረሰባቸው፣ እንዲሁም ከ4.6 ቢሊዮን ብር በላይ የንብረት ውድመት እንደተከሰተ ገልጸዋል።
ወንጀሎች የተፈጸሙበት መጠንና ግዝፈት በራሱ ለምርመራውና ለክስ ሒደቱ ትልቅ ፈተና እንደሆነ ያስረዱት ጠቅላይ ዓቃቤ ሕጉ፣ መንግሥት አጥፊዎችን ወደ ሕግ እያቀረበ ነው ብለዋል።
ምንም እንኳን የሰዎችን ሕይወት መቅጠፋቸው አሳዛኝ መሆኑንና መንግሥትም በዚህ ሐዘን እንደሚሰማው የተናገሩት ቢልለኔ፣ እንዲህ ያሉ የአመፅ ክስቶችን ግን መንግሥት የዜጎቹን ደኅንነት ለማስጠበቅ አቅም የለውም ለማለት አያስችልም ብለዋል። ይልቁንም ትኩረት ያላገኙና ያልተነገረላቸው በርካታ ተመሳሳይና የሽብር ጥቃቶችን መቀልበስ የተቻለ መሆኑ ከግምት ሊገባ ይገባል ሲሉ አክለዋል።
በዚህ ላይ ያከሉት ጌዲዮን (ዶ/ር) እንዳሉት፣ መንግሥት ተመሳሳይም ሆነ ሌሎች ጥቃቶችን ከመቀልበስ ባለፈ፣ የተለያዩ አጥፊዎችን ወደ ሕግ እያቀረበ መሆኑ፣ ወደፊት ሊፈጠሩ የሚችሉ ተመሳሳይ ጥቃቶችም ሆኑ ሙከራዎችን ለማስቀረት ይረዳል ብለዋል።
በተለይ አቶ ጃዋር መሐመድ በፍርድ ቤት መንግሥት እሳቸውንም ሆነ ሌሎች ፖለቲከኞችን ያሰረው ጥፋት ኖሮባቸው ሳይሆን፣ የፖለቲካ አመለካከታቸው የተለየ ስለሆነ መንግሥት የምርጫ ሜዳው ላይ ጠንካራ ተፎካካሪ እንዳይኖር እያደረገ ነው ሲሉ ያቀረቡትን መከራከሪያ በተመለከተ ምላሽ የሰጡት ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ጌዲዮን (ዶ/ር)፣ “የጉዳዮችን መገናኘትና ምክንያትነት መረዳት መቻል ይኖርብናል፤” በማለት፣ እነዚህ የታሰሩ ግለሰቦች ፖለቲከኞች ቢሆኑም፣ የታሰሩት ግን በፖለቲካ እንቅስቃሴያቸው እንዳልሆነ መታወቅ ይኖርበታል ሲሉ ተከራክረዋል።
2013 ዓ.ም. ከቀደመው ዓመት ይልቅ በሰላምና መረጋጋት ረገድ የተሻለ እንደነበረ ያስታወሱት ቢልለኔ፣ በመተከልና በሌሎች ሥፍራዎች በንፁኃን ዜጎች ላይ የተሰነዘሩ ጥቃቶችን መንግሥት ያወግዛል ብለው፣ በመንግሥትና በክልል መንግሥታት የፀጥታ መዋቅሮች ጠንካራ ትብብር በማድረግ ሰላምና ፀጥታን ለማስጠበቅ ቁርጠኝነት እንዳለ አስረድተዋል። (ብሩክ አብዱ፤ ሪፖርተር)
ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ
Those are criminals by any definition, and must be tried as such; they are not political prisoners. It is time individuals/groups like them be dealt with in the style of North Korea (historically countries like China, Vietnam, South Korea, Cambodia, etc) attained their peace by confronting their own versions of Ethiopia’s thugs in the languages the thugs understood: quick elimination by any means available to the states. Thus like Mohammed and Geleba should be eliminated out of sight and sound in the middle of the night?