• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ጥቁር ውሃ ላይ አስጨርሶ፣ እንደገና የፈረጠጠው ጄኔራል ከበደ ፈቃዱ ማን ነው?

August 16, 2021 12:46 am by Editor Leave a Comment

የህወሃቱ ታጋይ ጄ/ል ከበደ በ1988 ዓም  የ31ኛ ክ/ጦር 3ኛ ብርጌድ ፓራ ኮማንዶ፣ የ1ኛ ሻለቃ አዛዥ ሆኖ ሰርቷል።  በኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ወቅት በ31ኛ ክ/ጦር ምክትል ብርጌድ አዛዥ ሆኖ አገልግሏል። በ1992 ዓም 35ኛ ክ/ጦር ስትፈጠር የ35ኛ ክ/ጦር 3ኛ ብርጌድ አዛዥ ሆኖ ተሹሟል።

በ1997 ዓም ኮር የሚባለው አጀረጃጀት ፈርሶ ዕዝ የሚባል አደረጃጀት ሲቋቋም፣ ግለሰብ የ35ኛ ክ/ጦር ም/አዛዥ ቀጥሎም የ33ኛ ክ/ጦር ዋና አዛዥ ሆኖ እስከ 2006 ዓ/ም ሠርቷል።

በ2006 ዓ/ም እነ ጄኔራል አበባው ታደሰን ለማስወጣት በተደረገው ግምገማ፣ ግለሰቡ የአበባው አሽከር ነህ ተብሎ ተፈርጇል። ይህን ተከትሎም  ከክፍለ ጦር አዛዥነቱ ተነስቶ፣ የዕዙ ማሰልጠኛ ት/ት ቤት አዛዥ ሆኖ ተመድቧል።

የጡረታው ጊዜ ሲደርስ “ተጠቅሞ ይውጣ” ተባለና ወደ አብዬ በሚሊቴሪ “ኦብዘርቨርነት” ተላከ።  በአማራና ኦሮሞያ የነጻነት  ትግል ሲቀጣጠልና የህወሃት ህልውና አደጋ ላይ ሲወድቅ፣  ህወሃት በጡረታ ልታስወጣው ያሰበችውን ሰው መልሳ፣ በ2010 ዓ/ም አጋማሽ ላይ የብ/ጄኔራልነት  ማዕረግ ሰጥታ ለሌላ ተልዕኮ አጨችው።  ከዚያም የ31ኛ ክ/ጦር ዋና አዛዥ አድርጋ ሾመችው። 

ሰውዬው በጣም ጨካኝ ነው ይሉታል አብረውት የሰሩት ሰዎች ሲናገሩ። “በኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ወቅት፣ ወደ ኤርትራ በጥልቀት ገብተን እያለ፣  ወደኋላ እንድንመለስ ስንታዘዝ፣ ሻዕብያም መረጃው ደርሶት ሰለነበር፣ ከፍተኛ የከባድ መሳሪያ ድብደባ ማድረግ ጀመረ። በዚህ መሃል  አዲስ ከመጡት ምልምል ወታደሮች መካከል አንድ ወጣት ተደናግጦ ራሱን አቆሰለ። ስለልጁ ድርጊት ለከበደ ሪፓርት ሲደረግለት፣ ‘አምጡት’ አለና፣  ሽጉጡን አውጥቶ ግንባሩን ብሎ ገደለው።”

በ2013 ዓ/ም ደግሞ በመከላከያ ሰራዊት ላይ ድንገተኛ ጥቃት ሲፈጸም፣ የእሱ ምክትል የነበረውን ኮ/ል ሻምበል በየነን (ባለከዘራውን) ለማስገደል አቅዶ፣ የክ/ጦሩ ም/አዛዥ እቅዱን ባለመቀበሉ፣  ከተማ ቀጥሮ በሽጉጥ ግንባሩን ብሎ ገደለው።

የብርጌድ አዛዥነቱን ተጠቅሞ ከኤርትራ ያዘረፈውን የኮንስትራክሽን መሳሪያዎች፣ ስኳርና ከብት፣  ሽራሮ ላይ ሽጦ  አክሱም ላይ ፎቅ ሰርቶበታል። ከጭካኔውና ሌብነቱ በተጨማሪ በቀላሉ ሊገለጽ የማይችል ዘረኛም ነው።

በለውጡ ማግስት አምባሳደር ስዩም መስፍን  ከኮሎኔል ማዕረግ በላይ ያላቸውን ወታደራዊ አዛዦች በየሁለት ሳምንቱ እየሰበሰበ ግዳጅ ይሰጥ ነበር።  ጄ/ል ከበደ ደግሞ  ሽሬ ላይ ከፍተኛ መኮንኖችን እየሰበሰበ ከላይ ያመጣውን ተልኮ ወደታች በማውረድ ስራውን ይሰራ ነበር። ይህ ሁሉ ሲሆን ሰራዊቱ በተደጋጋሚ ለበላይ አለቆች ቢያሳውቅም፣ ምላሽ በማጣቱ፣ የጥቅምት 24ቱ እልቂት ተከሰተ። ከዚህ እልቂት ጀርባ ካሉት ቁልፍ ሰዎች መካከል አንዱ ይህ በተደጋጋሚ ታዳጊዎችን እያስጨፈጨፈ የሚፈረጥጠው ጄኔራል ነው።

ፋሲል የኔዓለም

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions, Right Column Tagged With: operation dismantle tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule